የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
9.67K subscribers
9.61K photos
133 videos
1 file
1.55K links
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።

"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
Download Telegram
በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ አዲስ አበባ እና አካባቢው ክልል የወንጌል መስካሪዎች የአንድነት ፕሮግራም ተካሄደ።

ነሐሴ 6/2017 ዓ.ም በሴሚሲ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ በተካሄደው የወንጌላውያን እና የወንጌል መስካሪ አገልጋዮች የአንድነት ፕሮግራም ላይ 118 አገልጋዮች ተገኝተዋል። በዘማሪ አላምረው ኢያሱ ዝማሬ ቀርቦ ጉባኤው እግዚአብሔርን አምልኳል።

በመቀጠል በክልሉ የወጣቶች ቤተሰብ አገልግሎት ፣ የወንጌል ስርጭት አገልግሎት ሃላፊ በሆኑት በመጋቢ ኤልያስ አየለ "መቼ እንደ ሐዋርያቶችሁ" በሚል ርዕስ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት አቅርበዋል።

የፕሮግራሙ አላማ አመቱን ሙሉ ወንጌልን ሲሰብኩ የቆዩትን አገልጋዮች ጌታ ስለረዳቸው ለማመስገን እና ለማበረታታት መሆኑን ታውቋል።

መረጃው የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ነው።

ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
3