የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከዊክሊፍ ኢትዮጵያ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ማህበር ጋር በጋራ ለመስራት ተፈራረመ።
ነሐሴ 7/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናትን ታሪክ በመጽሐፍ ሰንዶ ከማስቀመጥ አንጻር የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል እና ዊክሊፍ ኢትዮጵያ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ማህበር በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳይ ላይ ስምምነት አድርገዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ታሪክን መጻፍ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እንደሆነ በማንሳት ታሪክን ጠብቆ በታማኝነትና በጥራት መጻፍ አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ደረጄ ጀምበሩም የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት በሀገራችን ኢትዮጵያ ከአንድ መቶ አመታት በላይ እድሜ እንዳላቸው እና በወንጌልና በማህበራዊ አገልግሎት ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንዳበረከቱ በመገለጽ "የሚጻፈው ታሪክ እግዚአብሔር በቤተክርስቲያኑ በኩል የሰራው ስራ ስለሆነ ታሪኩ የእርሱ ነው።” በማለት ተናግረዋል።
የዊክሊፍ የቦርድ ስብሳቢ ፓስተር ግሩም ሞላም “ የታሪክ ጀማሪ እግዚአብሔር ነው። ታሪክንም የሚሰጠው እግዚአብሔር ነው። ስለተሰጠን ታሪክ አግዚአብሔር ይመስገን። ከ30 ሚሊዮን በላይ የሆነው የወንጌል አማኞችን ታሪክ ጽሕፎና ሰንዶ ለማስቀመጥ ካውንስሉ ከእኛ ጋር ለመስራት በማቀዱ ደስ ብሎናል።” ብለዋል።
የካውንስሉ የውጪ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ መጋቢ አሸብር ከተማ የሚዘጋጀው መጽሐፍ ለምርምር፣ ለ ዩኒቨርስቲዎች ፣ ለኮሎጆች፣ ለሥነ መለኮት ተቋማት የሚያግዝና የሚጠቅም መሆኑን አንስተው መጽሐፉ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋ እንደሚጻፍ ገልጻዋል።
ዳይሬክተር ተፈራ እንዳለ የኢትዮጵያ አብያተክርስቲያናትን ከአንድ መቶ አመት ያለፈ ታሪክ በተቀናጀ መልኩ ለትውልድ ፣ ለሀገር ፣ ለቤተክርስቲያን በሚመጥን መልኩ ለመዘጋጀት በዚህ ስራ ላይ ለመሳተፍ እድል በማግኘታቸው የተሠማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
ነሐሴ 7/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናትን ታሪክ በመጽሐፍ ሰንዶ ከማስቀመጥ አንጻር የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል እና ዊክሊፍ ኢትዮጵያ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ማህበር በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳይ ላይ ስምምነት አድርገዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ታሪክን መጻፍ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እንደሆነ በማንሳት ታሪክን ጠብቆ በታማኝነትና በጥራት መጻፍ አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ደረጄ ጀምበሩም የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት በሀገራችን ኢትዮጵያ ከአንድ መቶ አመታት በላይ እድሜ እንዳላቸው እና በወንጌልና በማህበራዊ አገልግሎት ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንዳበረከቱ በመገለጽ "የሚጻፈው ታሪክ እግዚአብሔር በቤተክርስቲያኑ በኩል የሰራው ስራ ስለሆነ ታሪኩ የእርሱ ነው።” በማለት ተናግረዋል።
የዊክሊፍ የቦርድ ስብሳቢ ፓስተር ግሩም ሞላም “ የታሪክ ጀማሪ እግዚአብሔር ነው። ታሪክንም የሚሰጠው እግዚአብሔር ነው። ስለተሰጠን ታሪክ አግዚአብሔር ይመስገን። ከ30 ሚሊዮን በላይ የሆነው የወንጌል አማኞችን ታሪክ ጽሕፎና ሰንዶ ለማስቀመጥ ካውንስሉ ከእኛ ጋር ለመስራት በማቀዱ ደስ ብሎናል።” ብለዋል።
የካውንስሉ የውጪ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ መጋቢ አሸብር ከተማ የሚዘጋጀው መጽሐፍ ለምርምር፣ ለ ዩኒቨርስቲዎች ፣ ለኮሎጆች፣ ለሥነ መለኮት ተቋማት የሚያግዝና የሚጠቅም መሆኑን አንስተው መጽሐፉ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋ እንደሚጻፍ ገልጻዋል።
ዳይሬክተር ተፈራ እንዳለ የኢትዮጵያ አብያተክርስቲያናትን ከአንድ መቶ አመት ያለፈ ታሪክ በተቀናጀ መልኩ ለትውልድ ፣ ለሀገር ፣ ለቤተክርስቲያን በሚመጥን መልኩ ለመዘጋጀት በዚህ ስራ ላይ ለመሳተፍ እድል በማግኘታቸው የተሠማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
❤5👍2
በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ አዲስ አበባ እና አካባቢው ክልል የወንጌል መስካሪዎች የአንድነት ፕሮግራም ተካሄደ።
ነሐሴ 6/2017 ዓ.ም በሴሚሲ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ በተካሄደው የወንጌላውያን እና የወንጌል መስካሪ አገልጋዮች የአንድነት ፕሮግራም ላይ 118 አገልጋዮች ተገኝተዋል። በዘማሪ አላምረው ኢያሱ ዝማሬ ቀርቦ ጉባኤው እግዚአብሔርን አምልኳል።
በመቀጠል በክልሉ የወጣቶች ቤተሰብ አገልግሎት ፣ የወንጌል ስርጭት አገልግሎት ሃላፊ በሆኑት በመጋቢ ኤልያስ አየለ "መቼ እንደ ሐዋርያቶችሁ" በሚል ርዕስ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት አቅርበዋል።
የፕሮግራሙ አላማ አመቱን ሙሉ ወንጌልን ሲሰብኩ የቆዩትን አገልጋዮች ጌታ ስለረዳቸው ለማመስገን እና ለማበረታታት መሆኑን ታውቋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
ነሐሴ 6/2017 ዓ.ም በሴሚሲ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ በተካሄደው የወንጌላውያን እና የወንጌል መስካሪ አገልጋዮች የአንድነት ፕሮግራም ላይ 118 አገልጋዮች ተገኝተዋል። በዘማሪ አላምረው ኢያሱ ዝማሬ ቀርቦ ጉባኤው እግዚአብሔርን አምልኳል።
በመቀጠል በክልሉ የወጣቶች ቤተሰብ አገልግሎት ፣ የወንጌል ስርጭት አገልግሎት ሃላፊ በሆኑት በመጋቢ ኤልያስ አየለ "መቼ እንደ ሐዋርያቶችሁ" በሚል ርዕስ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት አቅርበዋል።
የፕሮግራሙ አላማ አመቱን ሙሉ ወንጌልን ሲሰብኩ የቆዩትን አገልጋዮች ጌታ ስለረዳቸው ለማመስገን እና ለማበረታታት መሆኑን ታውቋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
❤3