በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የማዕከላዊ ክላስተር የ4ተኛው ዓመት የመጋቢነት አመራር ሥልጠና(4th Year Pastoral Leadership Training) በአዲስ አበባ ከተማ ማካሄድ መጀመሩ ተገለጸ።
የማዕከላዊ ክላስተር የ4ተኛው ዓመት የመጋቢነት አመራር ሥልጠና(4th Year Pastoral Leadership Training) በአዲስ አበባ ከተማ በመካነ ኢየሱስ ሴሚናሪዮም በዶ/ር አማኑኤል ገ/ሥላሴ የስብሰባ አዳራሽ መሰጠት ተጀምሯል።
የመጋቢያንን የአመራር ክህሎትን ለማሳደግ በአራት ዓመታት ተከፋፍሎ በተቀረፀ ልዩ ሥርዓተ ትምህርት በመሰጠት ላይ የሚገኘው ይህ ሥልጠና በዚህኛው ዙር ማጠቃለያውን የሚያደርግ መሆኑ ተገልጾዋል። የዘንድሮው ስልጠና "ደቀመዛሙርትን እና ደቀ መዝሙር አድራጊዎችን ማብዛት!" በሚል መሪ ሐሳብ እየተሰጠ ይገኛል።
በስልጠናው ከአዲስ አበባ ሲኖዶስና ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ የተወጣጡ የሲኖዶስና የሰበካ መሪዎች፤ የማኀበራነ ምዕመናን ቄሶች፣ ወንጌላውያን እና ሽማግሌዎች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በጋራ እየተካፈሉ እንደሚገኙ ተገልጿል ።
ባለፉት ወራት በቦረናና በዲላ ከተሞች በርካታ ሲኖዶሶችን ያሳተፈ ሥልጠና በተመሳሳይ ይዘት መሰጠታቸው የሚታወስ መሆኑ ተገልጾዋል ። የማዕከላዊ ክላስተርን ጨምሮ በቀጣይ በሌሎች ክላስተር የሚሰጠውን የ4ተኛ ዓመት የመጋቢነት አመራር ሥልጠና የቤተ ክርስቲያኒቱ የሚስዮንና ቲኦሎጂ መምሪያ ከፒ ኤል አይ ኢንተርናሽናል(PLI International) ጋር በትብብር ያዘጋጃቸው መሆኑን ከመምሪው ለመረዳት ተችሏል።
መረጃውን የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
የማዕከላዊ ክላስተር የ4ተኛው ዓመት የመጋቢነት አመራር ሥልጠና(4th Year Pastoral Leadership Training) በአዲስ አበባ ከተማ በመካነ ኢየሱስ ሴሚናሪዮም በዶ/ር አማኑኤል ገ/ሥላሴ የስብሰባ አዳራሽ መሰጠት ተጀምሯል።
የመጋቢያንን የአመራር ክህሎትን ለማሳደግ በአራት ዓመታት ተከፋፍሎ በተቀረፀ ልዩ ሥርዓተ ትምህርት በመሰጠት ላይ የሚገኘው ይህ ሥልጠና በዚህኛው ዙር ማጠቃለያውን የሚያደርግ መሆኑ ተገልጾዋል። የዘንድሮው ስልጠና "ደቀመዛሙርትን እና ደቀ መዝሙር አድራጊዎችን ማብዛት!" በሚል መሪ ሐሳብ እየተሰጠ ይገኛል።
በስልጠናው ከአዲስ አበባ ሲኖዶስና ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ የተወጣጡ የሲኖዶስና የሰበካ መሪዎች፤ የማኀበራነ ምዕመናን ቄሶች፣ ወንጌላውያን እና ሽማግሌዎች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በጋራ እየተካፈሉ እንደሚገኙ ተገልጿል ።
ባለፉት ወራት በቦረናና በዲላ ከተሞች በርካታ ሲኖዶሶችን ያሳተፈ ሥልጠና በተመሳሳይ ይዘት መሰጠታቸው የሚታወስ መሆኑ ተገልጾዋል ። የማዕከላዊ ክላስተርን ጨምሮ በቀጣይ በሌሎች ክላስተር የሚሰጠውን የ4ተኛ ዓመት የመጋቢነት አመራር ሥልጠና የቤተ ክርስቲያኒቱ የሚስዮንና ቲኦሎጂ መምሪያ ከፒ ኤል አይ ኢንተርናሽናል(PLI International) ጋር በትብብር ያዘጋጃቸው መሆኑን ከመምሪው ለመረዳት ተችሏል።
መረጃውን የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
የኢትዮጵያ አማኑኤል ብርሃንና ህይወት ቤ/ክ ከተለያዩ አጥቢያዎች ለተወጣጡ አገልጋዮች ስልጠና ሰጠች።
ከተመሰረተች 26 ዓመታትን ያስቆጠረችው ቤተክርስቲያንኗ ባለፉት 10 ቀናትም በአራቱ ቀጠናዎቿ ማለትም በዶኒ ፣በአለምጤና ፣ በአርቤጎና እና በሻሸመኔ ቀጠና ዙሪያ ላሉ የአጥቢያ አገልጋዮች ስልጠናውን ስትሰጥ ቆይታለች።
በአሁኑ ሰዓትም የኢትዮጵያ አማኑኤል ብርሃንና ህይወት ቤ/ክ በአራቱም አቅጣጫ ሰባት ቀጠናዎችና 48 አጥቢያዎች እንዳሉዋት ተገልጿል።
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይም ሐምሌ 25 እና 26 በሻሸመኔ አጥቢያ የወንጌል ስርጭት ጊዜ የተደረገ ሲሆን በተናጠል በተደረገ የወንጌል ስርጭትም 408 ሰዎች ወንጌልን የሰሙ ሲሆን ከነዚህም መካከል 12ቱ ጌታን ሲቀበሉ 14ቱ ደግሞ በንሰሀ መመለሳቸው ተነግሯል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም በጀማ ስብከት 2500 የሚጠጉ የከተማው ነዋሪዎች ወንጌልን ሲሰሙ 17 አዳዲስ ሰዎች ደግሞ የውሀ ጥምቀት መውሰዳቸውንም ከቤተክርስቲያኗ የደረሰን መረጃ ያሳያል ።
መረጃውን ከማህበራዊ ትስስር አገኘነው
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
ከተመሰረተች 26 ዓመታትን ያስቆጠረችው ቤተክርስቲያንኗ ባለፉት 10 ቀናትም በአራቱ ቀጠናዎቿ ማለትም በዶኒ ፣በአለምጤና ፣ በአርቤጎና እና በሻሸመኔ ቀጠና ዙሪያ ላሉ የአጥቢያ አገልጋዮች ስልጠናውን ስትሰጥ ቆይታለች።
በአሁኑ ሰዓትም የኢትዮጵያ አማኑኤል ብርሃንና ህይወት ቤ/ክ በአራቱም አቅጣጫ ሰባት ቀጠናዎችና 48 አጥቢያዎች እንዳሉዋት ተገልጿል።
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይም ሐምሌ 25 እና 26 በሻሸመኔ አጥቢያ የወንጌል ስርጭት ጊዜ የተደረገ ሲሆን በተናጠል በተደረገ የወንጌል ስርጭትም 408 ሰዎች ወንጌልን የሰሙ ሲሆን ከነዚህም መካከል 12ቱ ጌታን ሲቀበሉ 14ቱ ደግሞ በንሰሀ መመለሳቸው ተነግሯል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም በጀማ ስብከት 2500 የሚጠጉ የከተማው ነዋሪዎች ወንጌልን ሲሰሙ 17 አዳዲስ ሰዎች ደግሞ የውሀ ጥምቀት መውሰዳቸውንም ከቤተክርስቲያኗ የደረሰን መረጃ ያሳያል ።
መረጃውን ከማህበራዊ ትስስር አገኘነው
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ