የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስን ስንብት
ላለፉት 12 ዓመታት የሮማን ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የነበሩት አባ ፍራንሲስ በነገው ዕለት ሥርዓተ ቀብራቸው እንደሚፈጸም ይጠበቃል።
https://p.dw.com/p/4tbBr?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
ላለፉት 12 ዓመታት የሮማን ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የነበሩት አባ ፍራንሲስ በነገው ዕለት ሥርዓተ ቀብራቸው እንደሚፈጸም ይጠበቃል።
https://p.dw.com/p/4tbBr?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
DW
የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስን ስንብት
ላለፉት 12 ዓመታት የሮማን ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የነበሩት አባ ፍራንሲስ በነገው ዕለት ሥርዓተ ቀብራቸው እንደሚፈጸም ይጠበቃል።
የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ለወጣቶች የሚሰጡት ጥቅምና ጉዳት
በበርካታ የመገናኛ ዘዴ መተግበሪያዎች የሚሰራጩ ይዘቶች ጠቃሚ የመሆናቸውን ያህል ቀለል ያሉና እምብዛም ይዘቶቻቸው ጠንካራ መልእክት የማያስተላልፉ ይዘቶች በርካታ እይታን ስያገኙም መመልከት እንግዳ ነገር አይደለም፡፡
https://p.dw.com/p/4taFc?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
በበርካታ የመገናኛ ዘዴ መተግበሪያዎች የሚሰራጩ ይዘቶች ጠቃሚ የመሆናቸውን ያህል ቀለል ያሉና እምብዛም ይዘቶቻቸው ጠንካራ መልእክት የማያስተላልፉ ይዘቶች በርካታ እይታን ስያገኙም መመልከት እንግዳ ነገር አይደለም፡፡
https://p.dw.com/p/4taFc?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
DW
የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ለወጣቶች የሚሰጡት ጥቅምና ጉዳት
በበርካታ የመገናኛ ዘዴ መተግበሪያዎች የሚሰራጩ ይዘቶች ጠቃሚ የመሆናቸውን ያህል ቀለል ያሉና እምብዛም ይዘቶቻቸው ጠንካራ መልእክት የማያስተላልፉ ይዘቶች በርካታ እይታን ስያገኙም መመልከት እንግዳ ነገር አይደለም፡፡
የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕይወት እና የቤተክርስትያኒቱ መጻዒ ጊዜ
የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ባለፈው ሰኞ ነበር ነበር ከዚህ ዓለም ድካም የማረፋቸው ዜና የተሰማው ። የቫቲካኑን የቅዱስ ፔጥሮስ መንበር በመረከብ ከደቡባዊ የአሜሪካ ክፍለ ዓለም የመጡ የመጀመሪያው አቡንም ነበሩ ። ከረዥም የህመም ጊዜ በኋላ ያረፉት ፍራንሲስ 88 ዓመታቸው ነበር።
https://p.dw.com/p/4tbC0?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ባለፈው ሰኞ ነበር ነበር ከዚህ ዓለም ድካም የማረፋቸው ዜና የተሰማው ። የቫቲካኑን የቅዱስ ፔጥሮስ መንበር በመረከብ ከደቡባዊ የአሜሪካ ክፍለ ዓለም የመጡ የመጀመሪያው አቡንም ነበሩ ። ከረዥም የህመም ጊዜ በኋላ ያረፉት ፍራንሲስ 88 ዓመታቸው ነበር።
https://p.dw.com/p/4tbC0?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
DW
የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕይወት እና የቤተክርስትያኒቱ መጻዒ ጊዜ
የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ባለፈው ሰኞ ነበር ነበር ከዚህ ዓለም ድካም የማረፋቸው ዜና የተሰማው ። የቫቲካኑን የቅዱስ ፔጥሮስ መንበር በመረከብ ከደቡባዊ የአሜሪካ ክፍለ ዓለም የመጡ የመጀመሪያው አቡንም ነበሩ ። ከረዥም የህመም ጊዜ በኋላ ያረፉት ፍራንሲስ 88 ዓመታቸው ነበር።
የሚያዝያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
የቀድሞው የሰላም ሚኒስቴር ደ ኤታ ታዬ ደንደአ ጉዳይን ለማየት ዛሬ ያስቻለው ፍርድ ቤት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ከንቲባ አዳነች አቤቤበፌዴራል ፖሊስ በኩል መጥሪያ እንዲሰጥ በሚል አማራጭ ላይ ትዕዛዝ ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ያዘ።
በጋምቤላ ከተማ ለመታጠብ ወደ ባሮ ወንዝ በሚሄዱ ሰዎቸ ላይ አዞዎች ጉዳት እያደረሱ በመሆኑ ነዋሪው ጥንቃቄ እንዲደርግ የከተማዋ ፖሊሰ አስጠነቀቀ፡፡ የከተማዋ ፖሊስ አዛዥ ኡሞድ ኦኬሎ ለዶይቼ ቬሌ እንደገለጡት ባለፈው ሳምንት አንዲት የ17 ዓመት ልጃገረድና ሌላ የ16 ዓመት አዳጊ ልጅ በአዞ ጥቃት ሕይወታቸው አልፏል።
ነገ በሚካሄደው የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ የቀብር ሥነሥርዓት ቢያንስ የ 130 ሐገራት መሪዎችና ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች እንደሚገኙ ቫቲካን አስታወቀች። በቀብሩ ሥነ ሥርዓት ይገኛሉ ተብለው ከሚጠበቁት የሐገራት መሪዎች የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የሚገኙበት ሲሆን ትራምፕ በዛሬው ዕለት ሮም ገብተዋል።
ዩክሬይን ከሩስያ ጋር የገጠመችውን ጦርነት ለማቆምና ጊዚያዊ ሰላም ለማምጣት ግዛቷን ለሩስያ አሳልፋ ልትሰጥ እንደምትችል አንድ የዩክሬይን ባለስልጣን ፍንጭ ሰጡ። ባለስልጣኑ ሐሳባቸው በዩክሬይን ፕሬዚዳንትና በሕዝቡ ተቀባይነት ባይኖረውም መራሩን ሃቅ ግን መቀበል አለብን ሲሉ ተደምጠዋል።
አንድ የሩስያ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ በመኪና ላይ በተጠመደ ቦምብ መገደላቸውን ተሰማ። የሩስያ ጦር የዘመቻ ዳይረክቶሬት ምክትል አዛዥ የተገደሉት በመኪናቸው ላይ በተጠመደና በርቀት መቆጣጠሪያ በሚፈነዳ ቦምብ ነው ተብሏል።
https://p.dw.com/p/4tbQH?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
የቀድሞው የሰላም ሚኒስቴር ደ ኤታ ታዬ ደንደአ ጉዳይን ለማየት ዛሬ ያስቻለው ፍርድ ቤት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ከንቲባ አዳነች አቤቤበፌዴራል ፖሊስ በኩል መጥሪያ እንዲሰጥ በሚል አማራጭ ላይ ትዕዛዝ ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ያዘ።
በጋምቤላ ከተማ ለመታጠብ ወደ ባሮ ወንዝ በሚሄዱ ሰዎቸ ላይ አዞዎች ጉዳት እያደረሱ በመሆኑ ነዋሪው ጥንቃቄ እንዲደርግ የከተማዋ ፖሊሰ አስጠነቀቀ፡፡ የከተማዋ ፖሊስ አዛዥ ኡሞድ ኦኬሎ ለዶይቼ ቬሌ እንደገለጡት ባለፈው ሳምንት አንዲት የ17 ዓመት ልጃገረድና ሌላ የ16 ዓመት አዳጊ ልጅ በአዞ ጥቃት ሕይወታቸው አልፏል።
ነገ በሚካሄደው የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ የቀብር ሥነሥርዓት ቢያንስ የ 130 ሐገራት መሪዎችና ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች እንደሚገኙ ቫቲካን አስታወቀች። በቀብሩ ሥነ ሥርዓት ይገኛሉ ተብለው ከሚጠበቁት የሐገራት መሪዎች የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የሚገኙበት ሲሆን ትራምፕ በዛሬው ዕለት ሮም ገብተዋል።
ዩክሬይን ከሩስያ ጋር የገጠመችውን ጦርነት ለማቆምና ጊዚያዊ ሰላም ለማምጣት ግዛቷን ለሩስያ አሳልፋ ልትሰጥ እንደምትችል አንድ የዩክሬይን ባለስልጣን ፍንጭ ሰጡ። ባለስልጣኑ ሐሳባቸው በዩክሬይን ፕሬዚዳንትና በሕዝቡ ተቀባይነት ባይኖረውም መራሩን ሃቅ ግን መቀበል አለብን ሲሉ ተደምጠዋል።
አንድ የሩስያ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ በመኪና ላይ በተጠመደ ቦምብ መገደላቸውን ተሰማ። የሩስያ ጦር የዘመቻ ዳይረክቶሬት ምክትል አዛዥ የተገደሉት በመኪናቸው ላይ በተጠመደና በርቀት መቆጣጠሪያ በሚፈነዳ ቦምብ ነው ተብሏል።
https://p.dw.com/p/4tbQH?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
DW
የሚያዝያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
በጋምቤላ በአዞ ጥቃት 2 ሰዎች ሞቱ
የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ-ጳጳስ ፍራንሲስ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ።
በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ የጀርመን ፕረዚደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር እና የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ ቢያንስ የ130 ሐገራት መሪዎችና ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች እንደተሳተፉ ታውቋል። በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ከሐገራት መሪዎች እና ባለሥልጣናት በተጨማሪ ከተለያዩ ሀገራት የተጓዙ ከ250,000 በላይ ሰዎች ተገኝተዋል።
በቀብራቸው ሥነ-ሥርዓት ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ በሃይማኖታዊ እና ሰብአዊ ጉዳዮች የፈጸሟቸውን ዋና ዋና ተግባራት ተወስቷል። በተለይም ስደተኞች እና ድሆችን በመርዳት ያበረከቱት አስተዋፅኦ «ቁጥር ስፍር የሌለው» መሆኑን ተገልጿል።
በሌላ ዜና በቀብሩ ሥነስርዓት የተገኙት የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እና የዩክሬይኑ ፕረዚደንት ቮሎደሚር ዘለንስኪ ተገናኝተው መነጋገራቸውን ታውቋል። የዋይት ሃውስ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ስቲቨን ቼንግ «ትራምፕ እና ዘለንስኪ ዛሬ ተገናኝተው ፍሬያማ ውይይት አካሂደዋል፤ ዝርዝር ጉዳዩ ወደ ፊትይገለጻል» ማለታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።
በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ የጀርመን ፕረዚደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር እና የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ ቢያንስ የ130 ሐገራት መሪዎችና ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች እንደተሳተፉ ታውቋል። በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ከሐገራት መሪዎች እና ባለሥልጣናት በተጨማሪ ከተለያዩ ሀገራት የተጓዙ ከ250,000 በላይ ሰዎች ተገኝተዋል።
በቀብራቸው ሥነ-ሥርዓት ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ በሃይማኖታዊ እና ሰብአዊ ጉዳዮች የፈጸሟቸውን ዋና ዋና ተግባራት ተወስቷል። በተለይም ስደተኞች እና ድሆችን በመርዳት ያበረከቱት አስተዋፅኦ «ቁጥር ስፍር የሌለው» መሆኑን ተገልጿል።
በሌላ ዜና በቀብሩ ሥነስርዓት የተገኙት የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እና የዩክሬይኑ ፕረዚደንት ቮሎደሚር ዘለንስኪ ተገናኝተው መነጋገራቸውን ታውቋል። የዋይት ሃውስ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ስቲቨን ቼንግ «ትራምፕ እና ዘለንስኪ ዛሬ ተገናኝተው ፍሬያማ ውይይት አካሂደዋል፤ ዝርዝር ጉዳዩ ወደ ፊትይገለጻል» ማለታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።
ሐማስ በእጁ ያሉ እስራኤላውያን ታጋቾች በሙሉ በአንዴ ለመልቀቅና ለ 5 ዓመታት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት ለመድረስ መስማማቱን አስታወቀ። ሐማስ ይህን ያስታወቀው ልኡካኑ ከግብጽ አደራዳሪዎች ጋር በተናጥል በካይሮ ያካሄዱትን ውይይት ተከትሎ ነው።
አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የሐማስ ከፍተኛ ባለስልጣን ዛሬ ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ፤ «ሐማስ በእጁ የሚገኙ እስራኤላውያን ታጋቾች በሙሉ በአንዴ ለመልቀቅና ለ 5 ዓመታት የሚዘልቅ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ ዝግጁ ነው» ብለዋል።
ሐማስ የሚካሄዱ የተኩስ አቁም ስምምነቶች ጦርነቱን እስከ ወድያኛው ሊያስቆሙ የሚችሉ መሆን አለባቸው፤ በተጨማሪም እስራኤል ከጋዛ ሙሉ በሙሉ እንድትወጣና የሰብአዊ ዕርዳታ ያለእንቅፋት ለተረጂዎች እንዲቀርብ በተደጋጋሚ መጠየቁንም ዜናው አክሏል።
አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የሐማስ ከፍተኛ ባለስልጣን ዛሬ ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ፤ «ሐማስ በእጁ የሚገኙ እስራኤላውያን ታጋቾች በሙሉ በአንዴ ለመልቀቅና ለ 5 ዓመታት የሚዘልቅ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ ዝግጁ ነው» ብለዋል።
ሐማስ የሚካሄዱ የተኩስ አቁም ስምምነቶች ጦርነቱን እስከ ወድያኛው ሊያስቆሙ የሚችሉ መሆን አለባቸው፤ በተጨማሪም እስራኤል ከጋዛ ሙሉ በሙሉ እንድትወጣና የሰብአዊ ዕርዳታ ያለእንቅፋት ለተረጂዎች እንዲቀርብ በተደጋጋሚ መጠየቁንም ዜናው አክሏል።
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቼስኮስ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ተዘከሩ
ሥዩም ጌቱ
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ለርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ያዘጋጀችው መሥዋዕተ-ቅዳሴ በልደታ ማርያም ካቴድራል ተካሒዷል። ከዓመታት በፊት ለኢትዮጵያ እና ኤርትራ ዕርቅ “የመጀመሪያውን ታላቅ የበረከት ድምጽ ያሰሙ” ፍራንሲስ እንደነበሩ ያስታወሱት ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዝግጅቱ ባደረጉት ንግግር “ዓለም ትልቅ ሰው አጥታለች” ብለዋል
https://p.dw.com/p/4td7n?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
ሥዩም ጌቱ
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ለርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ያዘጋጀችው መሥዋዕተ-ቅዳሴ በልደታ ማርያም ካቴድራል ተካሒዷል። ከዓመታት በፊት ለኢትዮጵያ እና ኤርትራ ዕርቅ “የመጀመሪያውን ታላቅ የበረከት ድምጽ ያሰሙ” ፍራንሲስ እንደነበሩ ያስታወሱት ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዝግጅቱ ባደረጉት ንግግር “ዓለም ትልቅ ሰው አጥታለች” ብለዋል
https://p.dw.com/p/4td7n?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
DW
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቼስኮስ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ተዘከሩ
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ለርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ያዘጋጀችው መሥዋዕተ-ቅዳሴ በልደታ ማርያም ካቴድራል ተካሒዷል። ከዓመታት በፊት ለኢትዮጵያ እና ኤርትራ ዕርቅ “የመጀመሪያውን ታላቅ የበረከት ድምጽ ያሰሙ” ፍራንሲስ እንደነበሩ ያስታወሱት ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዝግጅቱ ባደረጉት ንግግር “ዓለም ትልቅ ሰው አጥታለች” ብለዋል
የርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ግብዓተ-መሬት በሮማ ከተማ በቅድስት ማርያም ካቴድራል ተፈጸመ
የርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ግብዓተ-መሬት በጣልያን ሮማ ከተማ በምትገኘው ቅድስት ማርያም ካቴድራል ተፈጽሟል። ፍራንሲስ ከጎርጎሮሳዊው 1903 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከቫቲካን ውጪ የተቀበሩ የቤተ-ክርስቲያኒቱ ርዕሰ-ሊቃነ ጳጳስ ሆነዋል። የርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ግብዓተ-መሬት የሚቀርቧቸው ብቻ በተገኙበት መፈጸሙን ቫቲካን አስታውቃለች።
https://p.dw.com/p/4tdAY?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
የርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ግብዓተ-መሬት በጣልያን ሮማ ከተማ በምትገኘው ቅድስት ማርያም ካቴድራል ተፈጽሟል። ፍራንሲስ ከጎርጎሮሳዊው 1903 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከቫቲካን ውጪ የተቀበሩ የቤተ-ክርስቲያኒቱ ርዕሰ-ሊቃነ ጳጳስ ሆነዋል። የርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ግብዓተ-መሬት የሚቀርቧቸው ብቻ በተገኙበት መፈጸሙን ቫቲካን አስታውቃለች።
https://p.dw.com/p/4tdAY?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
DW
የርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ግብዓተ-መሬት በሮማ ከተማ በቅድስት ማርያም ካቴድራል ተፈጸመ
የርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ግብዓተ-መሬት በጣልያን ሮማ ከተማ በምትገኘው ቅድስት ማርያም ካቴድራል ተፈጽሟል። ፍራንሲስ ከጎርጎሮሳዊው 1903 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከቫቲካን ውጪ የተቀበሩ የቤተ-ክርስቲያኒቱ ርዕሰ-ሊቃነ ጳጳስ ሆነዋል። የርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ግብዓተ-መሬት የሚቀርቧቸው ብቻ በተገኙበት መፈጸሙን ቫቲካን አስታውቃለች።
የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ አስፈትቶ ወደ መደበኛ ኑሮ መመለስ መጀመሩ
በትግራይ ክልል 17 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት እና ወደ ሰላማዊ ሕይወት የመመለስ ሥራ በእንግሊዝኛ ምህጻሩ DDR መከወኑን ብሔራዊ ተሃድሶ ኮምሽን አስታወቀ።
https://p.dw.com/p/4tb8z?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
በትግራይ ክልል 17 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት እና ወደ ሰላማዊ ሕይወት የመመለስ ሥራ በእንግሊዝኛ ምህጻሩ DDR መከወኑን ብሔራዊ ተሃድሶ ኮምሽን አስታወቀ።
https://p.dw.com/p/4tb8z?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
DW
የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ አስፈትቶ ወደ መደበኛ ኑሮ መመለስ መጀመሩ
በትግራይ ክልል 17 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት እና ወደ ሰላማዊ ሕይወት የመመለስ ሥራ በእንግሊዝኛ ምህጻሩ DDR መከወኑን ብሔራዊ ተሃድሶ ኮምሽን አስታወቀ።
አፍሪቃውያን ካርዲናሎች በመጭው የጳጳስ ምርጫ እና በኮንጎ የካቪላ መመለስ የፈጠረው ውጥረት
የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ከሌላው ዓለም ይልቅ የአማኞቿ ቁጥር በአፍሪካ እያደገ ነው። በዓለም ዙሪያ ከሚገኙ ካቶሊኮች ውስጥ የአፍሪካውያን 20 በመቶውን ይይዛሉ።ከዚህ አንፃር ቤተክርስቲያኗ በሟቹ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ምትክ አፍሪቃዊ ጳጳስ ትምርጥ ይሆን?በሌላ በኩል የኮንጎ የቀድሞው መሪ ጆሴፍ ካቢላ አማፂያንን ተቀላቅለዋል መባሉ ውጥረት ፈጥሯል።
https://p.dw.com/p/4td2h?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ከሌላው ዓለም ይልቅ የአማኞቿ ቁጥር በአፍሪካ እያደገ ነው። በዓለም ዙሪያ ከሚገኙ ካቶሊኮች ውስጥ የአፍሪካውያን 20 በመቶውን ይይዛሉ።ከዚህ አንፃር ቤተክርስቲያኗ በሟቹ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ምትክ አፍሪቃዊ ጳጳስ ትምርጥ ይሆን?በሌላ በኩል የኮንጎ የቀድሞው መሪ ጆሴፍ ካቢላ አማፂያንን ተቀላቅለዋል መባሉ ውጥረት ፈጥሯል።
https://p.dw.com/p/4td2h?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
DW
አፍሪቃውያን ካርዲናሎች በመጭው የጳጳስ ምርጫ እና በኮንጎ የካቪላ መመለስ የፈጠረው ውጥረት
የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ከሌላው ዓለም ይልቅ የአማኞቿ ቁጥር በአፍሪካ እያደገ ነው። በዓለም ዙሪያ ከሚገኙ ካቶሊኮች ውስጥ የአፍሪካውያን 20 በመቶውን ይይዛሉ።ከዚህ አንፃር ቤተክርስቲያኗ በሟቹ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ምትክ አፍሪቃዊ ጳጳስ ትምርጥ ይሆን?በሌላ በኩል የኮንጎ የቀድሞው መሪ ጆሴፍ ካቢላ አማፂያንን ተቀላቅለዋል መባሉ ውጥረት ፈጥሯል።
የዲጂታል መፍትሔዎች የራዲዮ ድራማ ክፍል 9 “የተስፋ ብርሀን
ባለፈው ክፍል እምነት የትምህርት ቤቷን የመወዳደሪያ ሃሳብ አሾልካ ሰጥታለች የሚል ክስ ቀርቦባት ነበር። ለማ ከተባለ አንድ የፍሎራ ትምህርት ቤት መምህር ጋር መታየቷ ለዚህ ምክንያት ተደርጎ ተወስዷል። ትምህርት ቤቱ እያበለጸገ የሚገኘው የመወዳደሪያ ድረ-ገጽ ከፍሎራ ትምህርት ቤት ጋር ፍጹም አንድ ሆኖ ተገኝቷል። ወላጅ አባቷን እየፈለገች የምትገኘው ጀምበሬ ከሆነ ሰው የቅርብ ጊዜ ፎቶ እና የስልክ ቁጥር ተልኮላታል። ይህ ሰው የሚታመን ይሆን? “የተስፋ ብርሃን” የተሰኘው 9ኛ ክፍል ምን ይነግረን ይሆን?
https://p.dw.com/p/4nvkj?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
ባለፈው ክፍል እምነት የትምህርት ቤቷን የመወዳደሪያ ሃሳብ አሾልካ ሰጥታለች የሚል ክስ ቀርቦባት ነበር። ለማ ከተባለ አንድ የፍሎራ ትምህርት ቤት መምህር ጋር መታየቷ ለዚህ ምክንያት ተደርጎ ተወስዷል። ትምህርት ቤቱ እያበለጸገ የሚገኘው የመወዳደሪያ ድረ-ገጽ ከፍሎራ ትምህርት ቤት ጋር ፍጹም አንድ ሆኖ ተገኝቷል። ወላጅ አባቷን እየፈለገች የምትገኘው ጀምበሬ ከሆነ ሰው የቅርብ ጊዜ ፎቶ እና የስልክ ቁጥር ተልኮላታል። ይህ ሰው የሚታመን ይሆን? “የተስፋ ብርሃን” የተሰኘው 9ኛ ክፍል ምን ይነግረን ይሆን?
https://p.dw.com/p/4nvkj?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
dw.com
የዲጂታል መፍትሔዎች የራዲዮ ድራማ ክፍል 9 “የተስፋ ብርሀን”
ባለፈው ክፍል እምነት የትምህርት ቤቷን የመወዳደሪያ ሃሳብ አሾልካ ሰጥታለች የሚል ክስ ቀርቦባት ነበር። ለማ ከተባለ አንድ የፍሎራ ትምህርት ቤት መምህር ጋር መታየቷ ለዚህ ምክንያት ተደርጎ ተወስዷል። ትምህርት ቤቱ እያበለጸገ የሚገኘው የመወዳደሪያ ድረ-ገጽ ከፍሎራ ትምህርት ቤት ጋር ፍጹም አንድ ሆኖ ተገኝቷል። ወላጅ አባቷን እየፈለገች የምትገኘው ጀምበሬ ከሆነ ሰው የቅርብ ጊዜ ፎቶ እና የስልክ ቁጥር…
የሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ-ጳጳስ ፍራንሲስ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ።
በኢራን የራጃኢ
ወደብ ባጋጠመ ፍንዳታና ከባድ ቃጠሎ 4 ሰዎች ሲሞቱ ከ500 በላይ ሰዎች መቁሰላቸው ተሰማ።
ከየመን ሁቲ አማጽያን የተቃጣ የሚሳይልና የሰው አልባ የጦር አውሮፕላን ጥቃት ማክሸፉን የእስራኤል ሰራዊት አስታወቀ።
የሩስያ ጦር በዩክሬይን
ተይዞ የነበረውን የኩርሱክ ግዛት በዛሬው ዕለት ሙሉ በሙሉ መልሶ መቆጣጠሩን አስታወቀ።
https://p.dw.com/p/4tdNj?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ-ጳጳስ ፍራንሲስ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ።
በኢራን የራጃኢ
ወደብ ባጋጠመ ፍንዳታና ከባድ ቃጠሎ 4 ሰዎች ሲሞቱ ከ500 በላይ ሰዎች መቁሰላቸው ተሰማ።
ከየመን ሁቲ አማጽያን የተቃጣ የሚሳይልና የሰው አልባ የጦር አውሮፕላን ጥቃት ማክሸፉን የእስራኤል ሰራዊት አስታወቀ።
የሩስያ ጦር በዩክሬይን
ተይዞ የነበረውን የኩርሱክ ግዛት በዛሬው ዕለት ሙሉ በሙሉ መልሶ መቆጣጠሩን አስታወቀ።
https://p.dw.com/p/4tdNj?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
dw.com
የሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
የሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ/ም የአድማጮች ማህደር ዝግጅት
ስንት ጋዜጠኞች ናቸው በገለልተኛነት ሙያዊ ስነምግባራቸውን እየተወጡ ያሉት? ብዙዎቹ ወደቀኝ ካለዚያም ወደግራ ያዘመሙ ሙያቸውን ለሚያራምዱት ዓላማ ማስፈፀሚያ የሚጠቀሙ ናቸው። በመንግስት እና በተቃዋሚ ሀይሎች ጫማ ውስጥ እራሳቸውን አስገብተው ከህሌናቸው ይልቅ ለሆዳቸው ተገዝተው የሚኖሩ
https://p.dw.com/p/4tbVS?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
ስንት ጋዜጠኞች ናቸው በገለልተኛነት ሙያዊ ስነምግባራቸውን እየተወጡ ያሉት? ብዙዎቹ ወደቀኝ ካለዚያም ወደግራ ያዘመሙ ሙያቸውን ለሚያራምዱት ዓላማ ማስፈፀሚያ የሚጠቀሙ ናቸው። በመንግስት እና በተቃዋሚ ሀይሎች ጫማ ውስጥ እራሳቸውን አስገብተው ከህሌናቸው ይልቅ ለሆዳቸው ተገዝተው የሚኖሩ
https://p.dw.com/p/4tbVS?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
dw.com
የሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ/ም የአድማጮች ማህደር ዝግጅት
ስንት ጋዜጠኞች ናቸው በገለልተኛነት ሙያዊ ስነምግባራቸውን እየተወጡ ያሉት? ብዙዎቹ ወደቀኝ ካለዚያም ወደግራ ያዘመሙ ሙያቸውን ለሚያራምዱት ዓላማ ማስፈፀሚያ የሚጠቀሙ ናቸው። በመንግስት እና በተቃዋሚ ሀይሎች ጫማ ውስጥ እራሳቸውን አስገብተው ከህሌናቸው ይልቅ ለሆዳቸው ተገዝተው የሚኖሩ ናቸው።
የአርቲስትና አክቲቪስት ሰሎሞን ተካልኝ የቀብር ሥነ ሥርዓት ትናንት አትላንታ ጆርጂያ ውስጥ ተፈጸመ።
ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በድንገተኛ ህመም በ57ኛ ዓመቱ ህይወቱ ያለፈው፣አርቲስትና አክቲቪስት ሰሎሞን ትናንት አትላንታ ውስጥ፣ "ኢተርናል ሒልስ ሜሞሪያል ጋርደን፣በተባለ የመቃብር ሥፍራ ላይ የቀብር ሥነ-ስርዓቱ ተፈጽሟል።
ከቀብር ሥነ ሥርዓቱ ቀደም ብሎ፣በአትላንታ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣የጸሎተ ፍትሓት መርሐ ግብር መካሄዱንም፣ባልደረባችን ታሪኩ ኃይሉ ዘግቧል።
ሰሎሞን ተካልኝ፣ በአዲስ አበባ ዙሪያ ካለው ኮረብታማ ሰፈር ከወላጆቹ ከአቶ ተካልኝ መሃሪና ከእናቱ ከወይዘሮ ታዱሽ ተሰማ አብራክ እንደ ጎርጎሮሳዊው ጊዜ አቆጣጠር ጥቅምት ሰባት ቀን 1968 መወለዱን በሕይወት ታሪክ ማኀደሩ ላይ ተመልክቷል።
ሰሎሞን የሙዚቃ መሳሪያዎች ቅንብርና ውህደት የሚወድ የነበረ ቢሆንም፣የእርሱ ታላቁ መሳሪያ የነበረው ግን፣የራሱ የታደለው የፈጥሮው ድምጽ እንደነበረ ተወስቷል።
በየጎዳናው በከበሮ ታጅቦ ከመዝፈን ጀምሮ፣በደተሟላ የምሽት ክለብ እስካደገበት ድረስ ለታዳሚዎቹ ደስታና ስሜት ሲያጋራ መቆየቱም ተገልጿል።
በኋላም በአክቲቪስትነት፣ በሬዲዮና በሌሎች የተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያ አውታሮች፣የፖለቲካ አቋሞቹን ሲያራምድ ቆይቷል።
ሰለሞን በሚያስተላልፋቸው ፖለቲካዊ ሃሳቦቹ ከአንድ ወገን ብርቱ ነቀፋ እና ትችት ሲያስተናግድ ከሌላ ወገን ደግሞ ድጋፍ ሲቸረው ቆይቷል።
ቤተሰቦቹ፣ጓደኞቹና ወዳጆቹ በተገኙበት ግብዓተ መሬቱ የተፈጸመው ሰሎሞን ተካልኝ፣የአራት ልጆች አባት ነበር።
ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በድንገተኛ ህመም በ57ኛ ዓመቱ ህይወቱ ያለፈው፣አርቲስትና አክቲቪስት ሰሎሞን ትናንት አትላንታ ውስጥ፣ "ኢተርናል ሒልስ ሜሞሪያል ጋርደን፣በተባለ የመቃብር ሥፍራ ላይ የቀብር ሥነ-ስርዓቱ ተፈጽሟል።
ከቀብር ሥነ ሥርዓቱ ቀደም ብሎ፣በአትላንታ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣የጸሎተ ፍትሓት መርሐ ግብር መካሄዱንም፣ባልደረባችን ታሪኩ ኃይሉ ዘግቧል።
ሰሎሞን ተካልኝ፣ በአዲስ አበባ ዙሪያ ካለው ኮረብታማ ሰፈር ከወላጆቹ ከአቶ ተካልኝ መሃሪና ከእናቱ ከወይዘሮ ታዱሽ ተሰማ አብራክ እንደ ጎርጎሮሳዊው ጊዜ አቆጣጠር ጥቅምት ሰባት ቀን 1968 መወለዱን በሕይወት ታሪክ ማኀደሩ ላይ ተመልክቷል።
ሰሎሞን የሙዚቃ መሳሪያዎች ቅንብርና ውህደት የሚወድ የነበረ ቢሆንም፣የእርሱ ታላቁ መሳሪያ የነበረው ግን፣የራሱ የታደለው የፈጥሮው ድምጽ እንደነበረ ተወስቷል።
በየጎዳናው በከበሮ ታጅቦ ከመዝፈን ጀምሮ፣በደተሟላ የምሽት ክለብ እስካደገበት ድረስ ለታዳሚዎቹ ደስታና ስሜት ሲያጋራ መቆየቱም ተገልጿል።
በኋላም በአክቲቪስትነት፣ በሬዲዮና በሌሎች የተለያዩ የማኀበራዊ ሚዲያ አውታሮች፣የፖለቲካ አቋሞቹን ሲያራምድ ቆይቷል።
ሰለሞን በሚያስተላልፋቸው ፖለቲካዊ ሃሳቦቹ ከአንድ ወገን ብርቱ ነቀፋ እና ትችት ሲያስተናግድ ከሌላ ወገን ደግሞ ድጋፍ ሲቸረው ቆይቷል።
ቤተሰቦቹ፣ጓደኞቹና ወዳጆቹ በተገኙበት ግብዓተ መሬቱ የተፈጸመው ሰሎሞን ተካልኝ፣የአራት ልጆች አባት ነበር።
በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ትዕግሥት አሰፋ የዓለም የሴቶች ክብረ-ወሰን በማሻሻል አሸነፈች
በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ትዕግሥት አሰፋ በርቀቱ የዓለም የሴቶች ክብረ-ወሰን በማሻሻል አሸነፈች። ባለፈው ዓመት በቀዝቃዛ የአየር ጠባይ እና በቋንጃዋ ላይ በተሰማት ሕመም ተቸግራ እንደነበር ያስታወሰችው ትዕግሥት ዘንድሮ "የለጠ ተስማሚ" ሆኖ እንደቀለላት ተናግራለች።
https://p.dw.com/p/4teK9 ?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ትዕግሥት አሰፋ በርቀቱ የዓለም የሴቶች ክብረ-ወሰን በማሻሻል አሸነፈች። ባለፈው ዓመት በቀዝቃዛ የአየር ጠባይ እና በቋንጃዋ ላይ በተሰማት ሕመም ተቸግራ እንደነበር ያስታወሰችው ትዕግሥት ዘንድሮ "የለጠ ተስማሚ" ሆኖ እንደቀለላት ተናግራለች።
https://p.dw.com/p/4teK9 ?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾
@dwamharicbot
DW
በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ትዕግሥት አሰፋ የዓለም የሴቶች ክብረ-ወሰን በማሻሻል አሸነፈች
በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ትዕግሥት አሰፋ በርቀቱ የዓለም የሴቶች ክብረ-ወሰን በማሻሻል አሸነፈች። ባለፈው ዓመት በቀዝቃዛ የአየር ጠባይ እና በቋንጃዋ ላይ በተሰማት ሕመም ተቸግራ እንደነበር ያስታወሰችው ትዕግሥት ዘንድሮ "የለጠ ተስማሚ" ሆኖ እንደቀለላት ተናግራለች።
የሚያዝያ 19 ቀን2017 የዓለም ዜና
· ርዋንዳ በሙስና እና ሥልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም የጠረጠረቻቸውን ሦስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት አሰረች። በቁጥጥር ሥር የዋሉት የርዋንዳ ማዕድን፣ ፔትሮሊየም እና ጋዝ ቦርድ ሹማምንት ናቸው።
· በኢራን ሻሒድ ራጃኢ የተባለ ወደብ ላይ በተከሰተ ፍንዳታ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 40 አሻቀበ። ትላንት ቅዳሜ ከሖርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ በሚገኝ የኢራን ትልቁ ወደብ ላይ በደረሰው ፍንዳታ ከ1,000 በላይ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል።
· በካናዳ ቫንኮቨር ከተማ በሚኖሩ የፊሊፒንስ ዜጎች ባሕላዊ መርሐ-ግብር ላይ አንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ ነድቶ ዘጠኝ ሰዎች ገደለ። ትላንት ቅዳሜ ምሽት ጥቃቱ የተፈጸመው የፊሊፒንስ ሰዎች በሀገሪቱ ነጻነት ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው ብሔራዊ ጀግና የሚታሰቡበትን በዓል ለመታደም በተሰበሰቡበት ነው።
· የእስራኤል ጦር በሊባኖስ ዋና ከተማ ደቡባዊ ክፍል የሚኖሩ ሰዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ አስጠነቀቀ። ጦሩ ማስጠንቀቂያውን ከሰጠ ከአንድ ሰዓት በኋላ እስራኤል በተዋጊ ጀቶች በደቡባዊ ቤይሩት ጥቃት መፈጸሟን ሬውተርስ ዘግቧል።
· ሩሲያ የዩክሬን ጦር ሠራዊት፣ የውጪ ተዋጊዎች እና በአውሮፓ የተላኩ ወታደራዊ አሰልጣኞች የሚጠቀሙባቸው ዒላማዎች ላይ ጥቃት መፈጸሟን እንደምትቀጥል የሀገሪቱ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ተናገሩ። ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ የዩክሬን ወታደሮች አሁንም በሩሲያ በሚገኘው የኩርስክ ግዛት እየተዋጉ መሆኑን ገልጸዋል።
·
በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ትዕግሥት አሰፋ በርቀቱ የዓለም የሴቶች ክብረ-ወሰን በማሻሻል አሸነፈች። ትዕግሥት ዛሬ እሁድየተካሔደውን ውድድር 2 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ከ50 ሰከንዶች በመሮጥ አጠናቃለች። ሰዓቱ በማራቶን በሴቶች ብቻ በተደረገ ውድድር አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቦላታል።
ዜናውን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ፦ https://p.dw.com/p/4teZu?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
· ርዋንዳ በሙስና እና ሥልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም የጠረጠረቻቸውን ሦስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት አሰረች። በቁጥጥር ሥር የዋሉት የርዋንዳ ማዕድን፣ ፔትሮሊየም እና ጋዝ ቦርድ ሹማምንት ናቸው።
· በኢራን ሻሒድ ራጃኢ የተባለ ወደብ ላይ በተከሰተ ፍንዳታ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 40 አሻቀበ። ትላንት ቅዳሜ ከሖርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ በሚገኝ የኢራን ትልቁ ወደብ ላይ በደረሰው ፍንዳታ ከ1,000 በላይ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል።
· በካናዳ ቫንኮቨር ከተማ በሚኖሩ የፊሊፒንስ ዜጎች ባሕላዊ መርሐ-ግብር ላይ አንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ ነድቶ ዘጠኝ ሰዎች ገደለ። ትላንት ቅዳሜ ምሽት ጥቃቱ የተፈጸመው የፊሊፒንስ ሰዎች በሀገሪቱ ነጻነት ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው ብሔራዊ ጀግና የሚታሰቡበትን በዓል ለመታደም በተሰበሰቡበት ነው።
· የእስራኤል ጦር በሊባኖስ ዋና ከተማ ደቡባዊ ክፍል የሚኖሩ ሰዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ አስጠነቀቀ። ጦሩ ማስጠንቀቂያውን ከሰጠ ከአንድ ሰዓት በኋላ እስራኤል በተዋጊ ጀቶች በደቡባዊ ቤይሩት ጥቃት መፈጸሟን ሬውተርስ ዘግቧል።
· ሩሲያ የዩክሬን ጦር ሠራዊት፣ የውጪ ተዋጊዎች እና በአውሮፓ የተላኩ ወታደራዊ አሰልጣኞች የሚጠቀሙባቸው ዒላማዎች ላይ ጥቃት መፈጸሟን እንደምትቀጥል የሀገሪቱ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ተናገሩ። ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ የዩክሬን ወታደሮች አሁንም በሩሲያ በሚገኘው የኩርስክ ግዛት እየተዋጉ መሆኑን ገልጸዋል።
·
በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ትዕግሥት አሰፋ በርቀቱ የዓለም የሴቶች ክብረ-ወሰን በማሻሻል አሸነፈች። ትዕግሥት ዛሬ እሁድየተካሔደውን ውድድር 2 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ከ50 ሰከንዶች በመሮጥ አጠናቃለች። ሰዓቱ በማራቶን በሴቶች ብቻ በተደረገ ውድድር አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቦላታል።
ዜናውን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ፦ https://p.dw.com/p/4teZu?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
dw.com
DW Amharic የሚያዝያ 19 ቀን 2017 የዓለም ዜና
ርዋንዳ በሙስና እና ሥልጣን ያለአግባብ በመጠቀም የጠረጠረቻቸውን ሦስት ባለሥልጣናት አሰረች። በኢራን ሻሒድ ራጃኢ ወደብ ላይ በተከሰተ ፍንዳታ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 40 አሻቀበ። በካናዳ ቫንኮቨር ከተማ በሚኖሩ የፊሊፒንስ ዜጎች መርሐ-ግብር ላይ አንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ ነድቶ ዘጠኝ ሰዎች ገደለ። የእስራኤል ጦር በቤይሩት ደቡባዊ ክፍል የሚኖሩ ሰዎች ለቀው እንዲወጡ አስጠነቀቀ። ሩሲያ የዩክሬን ጦር ሠራዊት፣…