DW Amharic
56.8K subscribers
3.95K photos
940 videos
69 files
15.1K links
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
Download Telegram
የጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜና

ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የውጭ እርዳታን ማቆማቸው አፍሪቃ ውስጥ ድንጋጤ አስከትሏል። የአሜሪካው ግዙፍ የእርዳታ ድርጅት USAID በአሜሪካም ሆነ በውጪው ዓለም ለሚገኙ ሠራተኞቹ ከፊታችን ዓርብ ጀምሮ አስተዳደራዊ እረፍት መስጠቱን ይፋ አድርጓል።

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ክልሉን ከትግራይ ክልል የሚያገናኘው የብረት ድልድይ ትናንት በደረሰበት ጉዳት አገልግሎት መስጠት ማቋረጡ ተገለጸ።

ፍልስጤማውያን ከአካባቢው ሳይለቁ ባስቸኳይ ጋዛ መልሶ እንዲገነባ ግብፅ ጥሪ አቀረበች። የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ጋዛን የማስተዳደር ዕቅድ ከወዲሁ ጠንካራ ትችት ገጥሞታል።

የዩጋንዳ ፖሊስ የሀገሪቱ ማዕከላዊ ባንክ መረጃ መጠለፉን ተከትሎ ዘጠኝ የፋይናንስ ሚኒስቴር ባለሥልጣናት አሠረ። https://p.dw.com/p/4q500?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
👉🏾 @dwamharicbot
አሜሪካ ለወባ በሽታ መከላከያ ፕሮጀክቶች የምታደርገው ድጋፍ በድንገት መቋረጡ ለገዳዩ በሽታ መስፋፋት አይነተኛ አስተዋጽዖ ሊኖረው እንደሚችል ተነገረ። አንድ ግዙፍ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት እንዳለው የርዳታው መቋረጥ በተለይ በአፍሪቃ ብዙ ሰዎችን የሚገድለዉ የወባ በሽታ አዲስ ዝርያ እንዲፈጠር ብሎም የከፋ የጤና ጥፋት እንዳያስከትል ያሰጋኛል ብሏል።
መቀመጫውን ለንደን ብሪታንያ ያደረገውና በመላው ዓለም የወባ በሽታን ለመከላከል የሚጥረዉ ግብረ ሰናይ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ ጀምስ ቲቤንደርና «በሽታው የሚያሳከትለውን ጥፋት አስቀድመን ለመገመት ብንሞክርም ሁኔታው ከተጠበቀው በላይ ማለፉን » ተመልክተናል ብለዋል።
አሜሪካ ለወባ በሽታ መከላከያ ፕሮጀክቶች የምታደርገውን ድጋፍ ማቋረጧን ተከትሎ ሞዛምቢክ ውስጥ በወባ መከላከያ ላይ የሚሰራ አንድ መርኃ ግብር እንዲዘጋ እና ሰራተኞች እንዲባረሩ ማድረጉን ኃላፊው ጠቁመዋል። በተጨማሪም እስያ ውስጥ የወባ ተሐዋሲን ለመቆጣጠር ለሰዎች ይሰጥ የነበረ ስልጠና መቋረጡም ተመልክቷል።
ከኢትዮጵያን፣ ከኤርትራ ፣ ከሱዳን ፣ ከደቡብ ሱዳን እና ከዩጋንዳ የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት የወባ ህክምና ዋነኛ መሰረት በሆነው በአርቴሚሲን ላይ ተመሰረቶ በተቀናጀ መልኩ የሚሰጥ ህክምና መድሃኒትን የሚቋቋም ተዋሐሲ የመጀመሪያ ምልክቶች እየታዩ መሆናቸውም ተሰምቷል።
የአሜሪካ መንግሥት በአብዛኛው በአፍሪካ በየዓመቱ ከ250 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ ሕሙማን መካከል ከ600,000 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆነውን በሽታ ለመቆጣጠር እና ለመመርመር 40 በመቶ የሚሆነውን ዓመታዊ የገንዘብ ድጋፍ ያደርግ ነበር።...
...በዓመት እስከ 1 ቢሊየን ዶላር ይደርስ የነበረውን የገንዘብ ድጋፍ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የውጭ ዕርዳታን ለማቆም መወሰናቸውን ተከትሎ ዕገዳ ተጥሎበታል። ይህም በሽታውን ለመከላከል የሚደረገውን የተቀናጀ ርብርብ ለአደጋ እንደሚያጋልጥ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘገባ አመልክቷል።
የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ ጦራቸዉ ጋዛ የሚኖሩ ፍልስጥኤማዉያን ግዛቲቱን «በፈቃደኝነት»እንዲለቁ የሚያችል» ዕቅድ እንዲነድፍ አዘዘ። የሚንስትሩ ትዕዛዝ የተሰማው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የጋዛ ሰርጥን ለመቆጣጠር እንደሚፈልጉ ካስታወቁ በኋላ ዓለማቀፍ ተቃዉሞ እየተሰማ ባለበት ወቅት ነው።
የመከላከያ ሚንስትሩ እስራኤል ካትዝ፣ ትራምፕ ከ2 ሚሊዮን በላይ ፍልስጥኤማዉያን የሚኖሩባትን ጋዛን ለመቆጣጠር ማቀዳቸውን አድንቀው «የፕሬዚደንቱን በድፍረት የተሞላ ዕቅድ በደስታ እንቀበላለን ፤ በየትኛውም ዓለም እንደሚሆነው የጋዛ ነዋሪዎች ከመኖሪያቸዉ በነጻነት መውጣት እና መሰደድ ሊፈቀድላቸው ይገባል » ብለዋል።
ሚንስትሩ ፍልስጥኤማዉያኑ በየብስ ፣ በባህር አለያም በአየር እንደምርጫቸው ከጋዛ መውጣት እንዲችሉ አማራጮች ማዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
የአረብ እና የአውሮጳ ህብረት አባል ሃገራትን ጨምሮ በርካታ ሃገራት የፍልስጥኤማዉያኑን ከሃገራቸው እንዲሰደዱ በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቀረበውን ሃሳብ ተቃዉመዋል።
የፍልስጥኤም አስተዳደር ፕሬዚዳንት መሐሙድ አባስ በበኩላቸው የአሜሪካውን ፕሬዚዳንት ዕቅድ በይፋ ውድቅ ባደረጉበት መግለጫቸው ። «ህጋዊ የፍልስጥኤማዉያን መብቶች ለድርድር አይቀርቡም»… ሃሳቡም «ከባድ የመብት ጥሰት ነው » ብለውታል።
የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬሽ በበኩላቸው“የፍልስጤም ሕዝብ በገዛ ምድራቸው እንደሰው የመኖር የማይገሰስ መብቶች» እንዳላቸው አጽንዖት ሰጥተዋል።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሰው ሰራሽ አስተዉሎት ስራዬን ይነጥቀኝ ይሆን ብለው ይሰጋሉ? #ቴክኖሎጂንበቀላሉ #በማድመጥመማር #AI #DW_Amharic #ClickITEasy
ዶቼቬለን በቲክቶክም ይከተሉ
ትክክለኛውን የዶይቸ ቬለ ቲክቶክ ገጻችን ይከተሉ!
ውድ አድማጮቻችን ፦የተለያዩ መገናኛ አውታሮችን በመጠቀም አድማሳችንን በማስፋት ዝግጅቶቻችንን በቲክቶክም ማቅረብ ጀምረናል ። የትክክለኛው የዶይቸ ቬለ ቲክቶክ ገጽ አባል በመሆን ዝግጅታችንን ተከታተሉ። በትክክለኛው በዚህ የቲክቶክ አድራሻችን፦ https://www.tiktok.com/@dw_amharic አባል ይሁኑ ። ለወዳጆቻችሁም ያጋሩ ።
ሥርጭታችን በኢትዮሳት ሳተላይት ማቅረብ መጀመራችንና በቲክቶክ አድራሻችንም ዝግጅቶችን ዝግጅቶቻችን እየቀረቡ ስለሆነ መከታተል ትችላላችሁ።
የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በራዲዮ እና በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል።
አሁኑኑ የዶይቸ ቬለ ቲክቶክ ገፅ ደምበኛ ይሁኑ!
የጥር 29 ቀን 2017 ዓ/ም ስርጭታችን አራት ርዕሰ ጉዳዮች በትንታኔ ይቀርባሉ
የአሜሪካ የተራድኦ ድርጅት እርዳታ መቋረጥ በአማራ ክልል የሚፈጥረው ጫና
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የትግራይ ክልል ፖለቲከኞች ለጻፉት መልእክት የህወሃት መሪዎች ምላሽ
በእሥር ላይ የሚገኙት የምክር ቤት አባላት የፍርድ ቤት ውሎ
እንዲሁም የጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ ያጋጠመው ችግርን የሚመለከቱ ዘገባዎች ተሰናድተዋል።
የዕለቱን የዓለም ዜናዎች አዜብ ታደሰ ታስደምጠናለች፤ ሸዋዬ ለገሰ ለአንድ ሰዓት አብሯችሁ በመቆየት ስርጭቱን ትመራለች።
እናንተም በያላችሁበት አብራችሁን እስከፍጻሜው እንድትሆኑ በአክብሮት እንጋብዛለን!
በቴሌግራም እና በዩቲዩብ በኩልም የዶቼ ቬለን ዜናዎች ማግኘት ትችላላችሁ።
ትክክለኛውን የዶይቼ ቬለ የዩቲዩብ ቻናል በሚከተለው መስፈንጠሪያ ታገኙታላችሁ።
https://www.youtube.com/@dwamharic/videos
መልካም ቆይታ። dwamharic_newshour
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በጋዛ ሰርጥ የተፈጠረው የኃይል ቀውስ ነዋሪዎች የሃይል ምንች አማራጮች እንዲፈልጉ አድርጓቸዋል
አላ አቡ ሲታ፣ አማራጭ የኃይል ባትሪዎችን ይጠግናል።
«በእነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ ድንኳን ያለውና መብራት የሌለው ማንኛውም ሰው የመጨረሻ አማራጩ ያለውን ባትሪ ለመጠገን ይገደዳል። እኛም በጥገና እናግዛቸዋለን። ምክንያቱም አዲሶች በገበያ ላይ አይገኙምና። አዳዲስ ባትሪዎች እንዲገቡ ስለማይፈቀድ አሮጌዎቹን ለመጠገን እንገደዳለን።» ሲል ተናግሯል።
የጋዛ የኤሌክትሪክ ኩባንያ እንዳለው ጋዛ ውስጥ አብዛኛው የመንገድ ላይ የመብራት ቋሚዎች ወድመዋል ፤ አልያም ብርቱ ጉዳት ሳይደርስባቸው አይቀርም።