DW Amharic
56.4K subscribers
4.14K photos
984 videos
69 files
15.7K links
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
Download Telegram
ኤርትራ መንግሥት ተቃዋሚዎች አዲስ አበባ ውስጥ መወያየታቸው ተገለፀ

የኤርትራ መንግሥትን ለመለወጥ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ያዘጋጁት የተባለ ውይይት ትናንት ሰኞ ጥር 19 ቀን፣ 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ መደረጉን ከተሳታፊ ድርጅቶች አንዱ ለዶቼ ቬለ ዐሳወቀ ። «የኢትዮጵያ መንግሥት ዕውቅና ሳይኖረው አልሆነም»፦ የኤርትራ አፋር ብሔራዊ ኮንግረስ
https://p.dw.com/p/4pkCa?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
የኢትዮጵያ መንግስት በሲቪል ማኅበራት ላይ የሚወስደው እርምጃ «እየተባባሰ መሄዱን » ዓለማቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ሂዉማን ራይትስ ዎች አስታወቀ። ዓለማቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ባለፈው ሳምንት በሁለት የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ላይ የወሰደውን የዕገዳ እርምጃ አውግዟል።
የሲቪክ ማህበራትን የሚቆጣጠረው የመንግስት አካል ባለፈው ታህሳስ ወር በሀገሪቱ አንጋፋ የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆነውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) እና የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል ከስራ ማገዱ ይታወሳል።
ተቆጣጣሪው የመንግስት አካል ለእገዳው "ማህበራቱ ናጻነት የጎደላቸው እና ከተፈቀደላቸው ስልጣን ተላልፈው እየሰሩ ነው" የሚል ክስ ማቅረቡን ሂዉማን ራይትስ ዎች በመግለጫው አመልክቷል።
በሂዉማን ራይትስ ዎች የአፍሪቃ ዳሬክተር ማዉሲ ሴጉን «የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ላይ ጥቃት ፈጽመዋል።» ማለታቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
ዳሬክተሯ አክለው መንግስት «ወሳኝ የሰብአዊ መብት ጉዳዮችን በመቀስቀስ እና በመሰነድ ላይ የተሰማሩ ቡድኖችን በማገድ እንዲሁም በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ ምርመራ የማድረግ ፍላጎት አላሳየም » ብለዋል።
መንግስት በዝነዚሁ ማህበራት ላይ ከወሰደው እርምጃ አስቀድሞ የመብቶች እና የዲሞክራሲ እድገት ማዕከል ፣በሰብአዊ መብቶች ጠበቆች ማህበር እና የሰብአዊ መብቶች ማህበር ላይ ተመሳሳይ ዕገዳ መጣሉን ዘገባው አስታውሷል። በኋላ ላይ ግን በሰብአዊ መብቶች ማህበር ላይ የተጣለው ዕገዳ ተነስቷል።
የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ቃል አቀባይ ቢሌነ ስዩም ከጎርጎርሳዊው 2018 ጀምሮ ጠቅላይ ሚንስትር አቢይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ "ሁሉም ተዋናዮች በኢትዮጵያ ውስጥ ትርጉም ባለው መልኩ እንዲሰማሩ የበለጠ አሳታፊ እና ህጋዊ መሰረት ያለው ሁኔታ ለመፍጠር "ጉልህ እርምጃዎች" እንደተወሰዱ መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል።
ቢለኔ እንዳሉት እርምጃው "በአንድ ወቅት የተከለከለ እና ጥብቅ ቁጥጥር የነበረበት የሲቪል ማህበረሰብ ምህዳር ፤ ድርጅቶች የሀገሪቱን ህጎች በማክበር በነፃነት እና ከፓርቲያዊነት በፀዳ መልኩ እንዲሰሩ ያስችላል። "
በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች በመንግስት እና በታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ባለው ውጊያ መንግስት እና ታጣቂዎች የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈጽመዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።
ትክክለኛውን የዶይቸ ቬለ ቲክቶክ ገጻችን ይከተሉ!
ውድ አድማጮች ፦ዶቼ ቬለ የተለያዩ መገናኛ አውታሮችን በመጠቀም አድማሱን በማስፋት ዝግጅቶቹን በቲክቶክም በማቅረብ ላይ ይገኛል። ስለሆነም የትክክለኛው የዶይቸ ቬለ ቲክቶክ ገጽ አባል በመሆን ዝግጅቶቹን እንዲከታተሉ እንጋብዛለን። ትክክለኛው የቲክቶክ አድራሻ ይህ ነው፤ https://www.tiktok.com/@dw_amharic አባል ይሁኑ ። ለወዳጆቻችሁም ያጋሩ ።
በቅርቡ ዶቼ ቬለ በቲክቶክ ገጹ ካጋራቸው አጫጭር መረጃዎች ስለየሐሰት መረጃ የሚያስረዳውን በዚህ ማገናኛ ተጠቅመው ይመልከቱ። ሌሎችንም ያገኛሉ።
https://www.tiktok.com/@dw.../video/7461907922088398085...
የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በራዲዮ እና በኢትዮሳት ሳተላይትም በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል።
ዶይቸ ቬለን በቲክቶክም ይከተሉ!
ዶቼ ቬለ በኢትዮሳት ያድምጡ!
ውድ አድማጮቻችን ዶቼ ቬለ የቀጥታ ሥርጭቱን በኢትዮ-ሳት ማስተላለፍ መጀመሩን ልብ ብለዋል?
የዶቼ ቬለን የቀጥታ ሥርጭች በኢትዮ-ሳት ወይንም (NSS-12) በ10985,0 ሜጋ ኸርዝ፣ ሆሪዞንታል፣ DW-08 ላይም ማድመጥ ይቻላል። ትራንስፖንደሩ፦ MEH01 ወይንም EAH01 ነው።
ከዚህ ቀደም ዶቼ ቬለ ከሚገኝባቸው አማራጭ የማድመጫ መስመሮች በተጨማሪ በጎርጎሪዮሳዊው አዲስ ዓመት 2025 ሥርጭቱንን በኢትዮሳት ላይም ማቅረብ መጀመሩን ሲገልጽ በደስታ ነው!
ፖለቲካዊ ፣ ማኅበራዊ እና ኤኮኖሚያዊ ይዘት ያላቸውን ዝግጅቶች እና ዓለም አቀፍ ወቅታዊ የዜና ትንታኔዎች የሚያሰራጨው ዶቼ ቬለ አሁን አዲስ በጀመረው የኢትዮሳት የሳተላይት ማሠራጫ ከሰኞ እስከ እሑድ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር እንደተለመደው ከምሽት አንድ ሰዓት ጀምሮ ይደመጣል።
ሥርጭታችን በኢትዮሳት ላይ በጥራት ይደመጣል? አስተያየታችሁን ጻፉልን።
ለገለልተኛና ወቅታዊ መረጃ ምርጫዎ ዶቼ ቬለ ይሁን!
ዶቼ ቬለን በኢትዮሳት ያድምጡ።
የጥር 21 ቀን 2017 ዓ/ም የስርጭት ማስታወቂያ
የዜና መጽሄታችን በዛሬው ዝግጅቱ
ከአቶ እስክንድር ነጋ ፣የአማራ ህዝባዊ ግንባር መሪ ጋር የየተደረገውን ቃለ መጠይቅ
በኦሮምያ ክልል በምእራብ ወለጋ ዞን አራት ሰላማዊ ሰዎች በፀጥታ ኅይሎች ተግደለዋል ሲሉ ነዋሪዎች መናገራቸው፤
አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በአማራ ክልል ስለሚፈጸሙ የጅምላ እሥሮች እና ሌሎች የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ዝምታን መምረጡን መውቀሱ
እንዲሁም ዳግም መፈናቀል ያሰጋቸው የአዋሽ ፈንታሌ እና ዱለቻ ወረዳዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ተፈናቃዮች አቤቱታን ያስተነትናል።
ውድ አድማጮቻችን ዶቼ ቬለ የቀጥታ ሥርጭቱን በኢትዮ-ሳት ማስተላለፍ መጀመሩን ልብ ብለዋል?
የዶቼ ቬለን የቀጥታ ሥርጭች በኢትዮ-ሳት ወይንም (NSS-12) በ10985,0 ሜጋ ኸርዝ፣ ሆሪዞንታል፣ DW-08 ላይም ማድመጥ ይቻላል። ትራንስፖንደሩ፦ MEH01 ወይንም EAH01 ነው።
ከስርጭታችን ጋር መልካም ቆይታ !
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጥላቻ እና ፍርሃትን መፍጠር እንዲህ ቀላል ሆኖ አያውቅም!
አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ለቀኝ አክራሪ አንቂዎች ፍፁም መሳሪያ ሆኖላቸዋል። ሰው ሰራሽ አስተውሎቱ ዘረኛ እና ፀረ-ስደተኛ ዘመቻዎችን እንዲፈጥሩ እና እንዲያራምዱ ብሎም በብዙ እንዲታይላቸው ያስችላቸዋል።
በአንድ ወቅት ከጀርመን ፋሽስታዊ መንግስት መሰል ፕሮፖጋንዳ ይስተጋባ እንደነበር ነው። ተቺዎችም ይህንኑ ነው የሚያረጋግጡት።
ነጭነት የበላይ እና ገዢ እንደሆነ ተደርጎ የመታየቱን ያህል የዕልቂት ማስከተሉ ትምህርት ትቶ አልፏል።
በተንቀሳቃሽ ምስሎች የጀመረው የዘረኝነት ፕሮፖጋንዳው ፍጻሜው ተመሳሳይ ላይሆን የሚችልበት ዕድልም የለም ።
የረቡዕ ጥር 21 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
አርዕስተ ዜና
*ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል የኢትዮጵያ መንግሥት ያደርሰዋል ያለዉን የመብት ጥሰትና የሲቪክ ማኅበራት ማገዱን እንዲያቆም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ግፊት እንዲያደርግ ጠየቀ ።

*ዓለማቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ሒውማን ራይትስ ዎች በበኩሉ፦ የኢትዮጵያ መንግስት በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ተጨማሪ የሲቪል ማኅበራት እንቅስቃሴን ማገዱ የሲቪል ማኅበረሱ ድፍለቃ ለመጠናከሩ አመላካች ነው ሲል ዛሬ ገልጧል ።  

*አቶ እስክንድር ነጋ ይመሩታል የሚባለው የአማራ ኃይል ሰሞኑን ከዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር አድርጎታል የተባለውን የ«ውይይት» ሂደት እንደሚያውቀው የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል ዐሳወቀ ።

ዜናው በዝርዝር በድምጽ እና በጽሑፍ ከታች ከማገናኛው መከታተል ይቻላል ።https://p.dw.com/p/4pnOz?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በሚያካሂደው 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 17 መደበኛ ስብሰባ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሞሽን ዋና ዳይሬክተር ሹመትን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። የኮሞሽኑ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ዶክተር ዳንኤል በቀለ የስራ ጊዚያቸውን ካጠናቀቁ እስከአሁን ኮሚሽኑ በተጠባባቂ ኮሚሽነር ሲ,መራ የቆየ ሲሆን ኮሞሽኑን ሊመሩ ይችላሉ ተብለው ከተመለመሉ እጮዎች መካከል የቀድሞው የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ዛሬ ይሾማሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የኮሚሽኑ ገለልተኝነት በተመለከተ ያላችሁን ምልከታ፤ ከአዲሱ ኮሚሽነርስ ምን ትጠብቃላች? ተወያዩበት።
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
በአፍሪካ ተጽዕኖ ለማሳደር የሚደረጉ ዘመቻዎች በተለይም በሩሲያ በከፍተኛ መጠን ጨምረዋል። ዶይቼ ቬለ የዘመቻዎቹን ዘዴዎች፣ ዓላማዎች እና በቀጠናዎች መካከል ያላቸውን ልዩነት ሰንዷል። https://p.dw.com/p/4poN5?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሠራተኞች ጊዜውን ያመዛዘነ የደመወዝ ጭማሪ አልተደረገልንም፣ ኑሮንም ለመምራት ተቸግረናል አሉ። ሰራተኞቹ የደመወዝ ጭማሪ ቢጠይቁም አጥጋቢ ምላሽ እንዳላገኙ ነው ያመለከቱት። ቢሮው በበኩሉ “የደመወዝ ማስተካከያ ተደርጎ ክፍያው በቅርቡ ይፈፀማል” ብሏል።
ከጎጃም፣ ከጎንደር፣ ከወሎና ከሌሎች የተለያዩ የአማራ ክልል ገቢዎች ጽ/ቤቶች አስተያየታቸውን የሰጡን ሠራተኞች እንደሚሉት በአገር አቀፍ ደረጃ የመንግሥት ሠራተኛው የደመወዝ ጭማሪ ቢደረግለትም በአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ግን ምንም ዓይነት የደመወዝ ጭማሪም ሆነ ማስተካከያ ባለመደረጉ ለከፍተኛ የኑሮ ችግር ተዳርገናል ብለዋል።
የአማራ ክልል ግቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ክብረት መሐመድ በጉዳዩ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ “ የሠራተኛውን የደመወዝ ይሻሻልልን ጥያቄ ለመመለስ ሥራዎች እየተሰሩ ነው፣ ክፍያም በቅርቡ ይፈፀማል” ብለዋል ሲል አለምነው መኮንን ዘግቧል።
እስራኤልና ሐማስ በደረሱት ስምምነት መሰረት ዛሬም የታገቱ እስራኤላውያን የመመለስ ስነስርአት ተካሂዷል። ሐማስ በጣሬው ዕለት አንዲት እስራኤላዊት ወታደር የምትገኝባቸው 8 ታጋጆች ለቀይ መስቀል አስረክቧል።
ሐማስ በተለይ በቁጥጥሩ ሥር የነበረችውን እስራኤላዊት ወታደር ለቀይ መስቀል ያስረከበው በሰሜን ጋዛ በጃባሊያ አካባቢ እንደሆነ የዘገበው አዣንስ ፍራንስ ፕረስ ነው።
የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ ተከሳሾች ላይ በዛሬው እለት በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወሰነ።
ፍርድ ቤቱ ዛሬ ውሳኔውን የሰጠው ተከሳሾቹ ከ10 ወር ግድም በፊት ሚያዚያ 07 ቀን 2016 ዓ.ም. ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ሳይሰጥ በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ (ቀሲስ በላይ መኮንን) አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በተከፈተባቸው ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ላይ ነው።
ችሎቱ 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በአምስት ዓመት ጽኑ እስራት እና በ10 ሺህ ብር መቀጮ፤ እንዲሁም 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው ሶስት ዓመት ከሶስት ወር ጽኑ እስራት እና የሶስት ሺህ ብር መቆጮ ተወስኖባቸዋል ሲል ስዮም ጌቱ ከአዲስ አበባ ዘግቧል።