https://p.dw.com/p/4iAQ6?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
የአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ
በዚህ ሳምንት ሞቅዲሾ ከአስመራ፣አዲስ አበባ ከካርቱም መክረዋል።የሶማልያና ኢትዮጵያ ውዝግብ በቀጠለበት በዚህ ወቅት ፕሬዝዳንቷ ወደ ኤርትራ ተጉዘዋል። የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትርም ደግሞ ወደ ሱዳን ተጉዘው ከሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ጋር ተወያይተዋል፣ ፖርት ሱዳንንም ጎብኝተዋል።ዢ,ሰሞኑ የአካባቢው ሀገራት መሪዎች ይፋዊ ጉብኝት ምን እንደምታ አለው?
https://p.dw.com/p/4iBwF?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሱዳን ጉብኝት
የዐቢይን ጥረት በተለይ ተቃዋሚዎቻቸው በራሳቸው አገር ያለውን የሰላም ችግር እያነሱ የራሷ አሮባት አይነት ትችት ሲያቀርቡባቸው ተስምቷል።። በሌላ በኩል ደግሞ የሱዳን ቀውስ በኢትዮጵያም ሊያስክትል ከሚችለው ችግርና ኢትዮጵያም በአካባቢው ካላት ተስሚነትና ጥቅም አንጻር ጉብኝቱና ተንሳሺነቱ ተገቢና አስፈላጊም እንደሆነ በመግለጽ የሜክራከሩ አሉ ።
https://p.dw.com/p/4iBZW?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
የታገቱት የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ቤተሰቦች ተማሪዎቹ አልተለቀቁም ይላሉ
“ልጆቹ እስካሁን አልተለቀቁም በዚያው በአጋቾች እጅ ናቸው” ያሉት የታጋች ቤተሰብ ትናንት በመገናኛ ብዙሃን የተሰራጨው መረጃ ተጨባጭነት እውነታውን ማረጋገጥ አልተቻላቸውም፡፡ ከታጋች ተማሪዎች አንዷን በአጋቾች በኩል አግኝተው ማነጋገራቸውን የሚገልጹት የቤተሰብ አባል ከመቶ በላይ ተማሪዎች እስካሁንም ድረስ በዚያው እንደሚገኙ መረዳታቸውን ገልጸዋል፡፡
«የተማሪዎቹ እገታ በብልጽግና የተቀነባበረ ነው»ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የሚለው ቡድን
ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ፣መንግሥት ሸኔ የሚለው ቡድን በቅርቡ ከኦሮምያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን እግቷል መባሉን አስተባበለ። የኦሮምያ መንግሥት ኮምኒኬሽን ቢሮ በዚህ ሳምንት አጋማሽ ባወጣው መግለጫ አሸባሪ ያለውን ቡድኑን በአጋችነት ከሷል። እገታውን በገዥው የብልጽግና ፓርቲ አባላት የተቀነባበረ ያለው ቡድኑ ግን ለእገታው «የብልጽግና ካድሬዎች ፣ሰላዮች እና የፀጥታ ኅይሎች»ያላቸውን ተጠያቂ ማድረጉን አዲስ ስታንዳርድ የተባለው የሀገር ውስጥ የህትመት መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል።
ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም. ከአማራ ክልል ተነስተው ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበሩት ከ160 በላይ ተማሪዎች የታገቱት ገርባ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ነበር። የኦሮምያ መንግሥት ከ167ቱ ታጋቾች መካከል 160ውን ማስለቀቅ መቻሉን እና ቀሪዎቹንም ለማስለቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ባለፈው ረቡዕ ነበር ያስታወቀው ።ይሁንና ዶቼቬለ ያነጋገራቸው የተማሪዎቹ ጓደኞችና ቤተሰቦች ግን እስከ ትናንት ድረስ ተማሪዎቹ አልተለቀቁም ብለዋል። ከእገታ ያመለጠ አንድ ተማሪም ትናንት እንደተናገረው ተማሪዎቹ አሁንም በአጋቾች እጅ ናቸው። ቤተሰቦች እንደሚሉት የሚገኙበት ሁኔታም አሰቃቂ ነው። አንድ የታጋች ተማሪ እህት ለዶቼቬለ እንደተናገሩት አጋቾቹ ደውለውላቸው ብዙ ገንዘብ እንዲያመጡ ጠይቀዋቸዋል።
ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ፣መንግሥት ሸኔ የሚለው ቡድን በቅርቡ ከኦሮምያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን እግቷል መባሉን አስተባበለ። የኦሮምያ መንግሥት ኮምኒኬሽን ቢሮ በዚህ ሳምንት አጋማሽ ባወጣው መግለጫ አሸባሪ ያለውን ቡድኑን በአጋችነት ከሷል። እገታውን በገዥው የብልጽግና ፓርቲ አባላት የተቀነባበረ ያለው ቡድኑ ግን ለእገታው «የብልጽግና ካድሬዎች ፣ሰላዮች እና የፀጥታ ኅይሎች»ያላቸውን ተጠያቂ ማድረጉን አዲስ ስታንዳርድ የተባለው የሀገር ውስጥ የህትመት መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል።
ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም. ከአማራ ክልል ተነስተው ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበሩት ከ160 በላይ ተማሪዎች የታገቱት ገርባ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ነበር። የኦሮምያ መንግሥት ከ167ቱ ታጋቾች መካከል 160ውን ማስለቀቅ መቻሉን እና ቀሪዎቹንም ለማስለቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ባለፈው ረቡዕ ነበር ያስታወቀው ።ይሁንና ዶቼቬለ ያነጋገራቸው የተማሪዎቹ ጓደኞችና ቤተሰቦች ግን እስከ ትናንት ድረስ ተማሪዎቹ አልተለቀቁም ብለዋል። ከእገታ ያመለጠ አንድ ተማሪም ትናንት እንደተናገረው ተማሪዎቹ አሁንም በአጋቾች እጅ ናቸው። ቤተሰቦች እንደሚሉት የሚገኙበት ሁኔታም አሰቃቂ ነው። አንድ የታጋች ተማሪ እህት ለዶቼቬለ እንደተናገሩት አጋቾቹ ደውለውላቸው ብዙ ገንዘብ እንዲያመጡ ጠይቀዋቸዋል።
ኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን በመከላከል ተሸለመች
ኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለመከላከል በሰራችው ውጤታማ በተባለ ሥራ በተባበሩት መንግስታት ሥነ ሕዝብ ድርጅት እውቅና ማግኘቷን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሀን ዘገቡ ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በትናንትናው እለት በኒውዮርክ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና መስሪያ ቤት ተገኝተው ሽልማቱን መቀበላቸውን መገናኛ ብዙሀኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃን ጠቅሰው ዘግበዋል። ሚኒስትሯ እውቅናና ሽልማቱ መንግስት ለሥርዓተ-ፆታ እኩልነትና ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት የበለጠ የሚያጠናክር ነው ማለታቸውም ተገልጿል።
የተባበሩት መንግስታት ሥነ ህዝብ ድርጅት (UNFPA) የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ በኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስወገድ የተቋቋመውን ጥምረት እንኳን ደስ አላችሁ ብሏል ። ይሁንና ግጭት ባለበት የአማራ ክልል አካባቢዎች ያለ እድሜ ጋብቻ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ዶቼቬለ ከዚህ ቀደም ዘግቧል።
ለመሆኑ በየአካባቢያችሁ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛት በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? እስቲ የምታውቁትን አካፍሉን፦
ኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለመከላከል በሰራችው ውጤታማ በተባለ ሥራ በተባበሩት መንግስታት ሥነ ሕዝብ ድርጅት እውቅና ማግኘቷን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሀን ዘገቡ ። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በትናንትናው እለት በኒውዮርክ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና መስሪያ ቤት ተገኝተው ሽልማቱን መቀበላቸውን መገናኛ ብዙሀኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃን ጠቅሰው ዘግበዋል። ሚኒስትሯ እውቅናና ሽልማቱ መንግስት ለሥርዓተ-ፆታ እኩልነትና ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት የበለጠ የሚያጠናክር ነው ማለታቸውም ተገልጿል።
የተባበሩት መንግስታት ሥነ ህዝብ ድርጅት (UNFPA) የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ በኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስወገድ የተቋቋመውን ጥምረት እንኳን ደስ አላችሁ ብሏል ። ይሁንና ግጭት ባለበት የአማራ ክልል አካባቢዎች ያለ እድሜ ጋብቻ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ዶቼቬለ ከዚህ ቀደም ዘግቧል።
ለመሆኑ በየአካባቢያችሁ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛት በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? እስቲ የምታውቁትን አካፍሉን፦
«አዲስ ፓስፖርት በሁለት ወራት እድሳት ደግሞ በአንድ ወር መስጠት ተችሏል።»የኢትዮጵያ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት
የኢትዮጵያ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት በአሁኑ ጊዜ ፓስፖርት ማግኘት ችግር አይደለም ሲል አስታወቀ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የአገልግሎቱ ባለሥልጣናት እንዳሉት ግን ችግሩ ሰንድ አሟልቶ አለመቅረብ ነው። ይህም ለአገልግሎት መጓተትና ለብልሹ አሰራር በር መክፈቱን ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ ለአገልግሎቱ ጠያቂዎች ቀጠሮ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ አዲስ ፓስፖርት በሁለት ወራት፣ እድሳት ደግሞ ከቀጠሮ ጀምሮ በአንድ ወር ውስጥ መስጠት ተችሏል ብለዋል። በ2016 ዓመተ ምህረት 1.1 ሚሊዮን ፓስፖርት መታተሙን የተናገረው አገልግሎቱ አሁንም ቢሆን ችግሩ ሙሉ በሙሉ አለመቃለሉን ጋዜጣዊ መግለጫውን የተከታተለው ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዘግቧል። ከአዲስ ፓስፖርት አሰጣጥና ከፓስፖርት እድሳት ጋር በተያያዘ እናንተስ ምን ልምድ አላችሁ? አጋሩን
የኢትዮጵያ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት በአሁኑ ጊዜ ፓስፖርት ማግኘት ችግር አይደለም ሲል አስታወቀ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የአገልግሎቱ ባለሥልጣናት እንዳሉት ግን ችግሩ ሰንድ አሟልቶ አለመቅረብ ነው። ይህም ለአገልግሎት መጓተትና ለብልሹ አሰራር በር መክፈቱን ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ ለአገልግሎቱ ጠያቂዎች ቀጠሮ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ አዲስ ፓስፖርት በሁለት ወራት፣ እድሳት ደግሞ ከቀጠሮ ጀምሮ በአንድ ወር ውስጥ መስጠት ተችሏል ብለዋል። በ2016 ዓመተ ምህረት 1.1 ሚሊዮን ፓስፖርት መታተሙን የተናገረው አገልግሎቱ አሁንም ቢሆን ችግሩ ሙሉ በሙሉ አለመቃለሉን ጋዜጣዊ መግለጫውን የተከታተለው ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዘግቧል። ከአዲስ ፓስፖርት አሰጣጥና ከፓስፖርት እድሳት ጋር በተያያዘ እናንተስ ምን ልምድ አላችሁ? አጋሩን
የኬንያ ፖሊስ አዛዥ ሥራቸውን ለቀቁ።
በሀገሪቱ በተቀጣጠለው ፀረ መንግሥት ተቃውሞ በርካቶች መሞታቸውን ተከትሎ ጠንካራ ትችት የተሰነዘረባቸው የፖሊስ አዛዥ ጃፌት ኮሜ በዛሬው ዕለት የስንብት ደብዳቤ አስገብተዋል። የኬንያ ፕሬዝደንት ጽሕፈት ቤት የኮሜን የስንብት ደብዳቤ ፕሬዝደንት ዊልያል ሩቶ መቀበላቸውን አረጋግጧል። ጽሕፈት ቤቱ አክሎም በቦታቸው ምክትል የኬንያ ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ዳግላስ ካንጃ መተካታቸውን አስታውቋል። በሀገሪቱ የተካሄደውን ፀረ መንግሥት ተቃውሞ ያደራጀው ጀነሬሽን Z በአጭሩ ጄን Z የተሰኘው የኬንያ ወጣቶች ስብስብ በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የኃይል እርምጃ ወስዷል ያሉት የኬንያ ፖሊስ አዛዥ ሥልጣናቸውን እንዲቀቁ ግፊት ሲያደርግ ነበር።
በሀገሪቱ በተቀጣጠለው ፀረ መንግሥት ተቃውሞ በርካቶች መሞታቸውን ተከትሎ ጠንካራ ትችት የተሰነዘረባቸው የፖሊስ አዛዥ ጃፌት ኮሜ በዛሬው ዕለት የስንብት ደብዳቤ አስገብተዋል። የኬንያ ፕሬዝደንት ጽሕፈት ቤት የኮሜን የስንብት ደብዳቤ ፕሬዝደንት ዊልያል ሩቶ መቀበላቸውን አረጋግጧል። ጽሕፈት ቤቱ አክሎም በቦታቸው ምክትል የኬንያ ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ዳግላስ ካንጃ መተካታቸውን አስታውቋል። በሀገሪቱ የተካሄደውን ፀረ መንግሥት ተቃውሞ ያደራጀው ጀነሬሽን Z በአጭሩ ጄን Z የተሰኘው የኬንያ ወጣቶች ስብስብ በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የኃይል እርምጃ ወስዷል ያሉት የኬንያ ፖሊስ አዛዥ ሥልጣናቸውን እንዲቀቁ ግፊት ሲያደርግ ነበር።
ኻርቱም፤ የሱዳን ፖሊስ የውጪ ዜጎች ከኻርቱም እንዲወጡ ማዘዙ
የሱዳን የጸጥታ ኃይሎች የውጪ ዜጎች ከዋና ከተማዋ ኻርቱም እና በዙሪያ ካሉ አካባቢዎች እንዲወጡ ትዕዛዝ ሰጡ። ፖሊስ ባወጣው ማሳሰቢያ መሠረት የውጪ ዜጎች ከተባለው የሱዳን አካባቢ ለመውጣት የሁለት ሳምንት ጊዜ ብቻ ነው የተሰጣቸው። በመንግሥት ወታደሮችና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች መካከል የሚካሄደው ውጊያ ተጠናክሮ በመቀጠሉ የውጪ ዜጎች ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ አካባቢውን ለቀው መውጣት እንዳለባቸው ፖሊስ አሳስቧል። ሮይተር መገናኛ ብዙሃንን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ በፈጥኖ ደራሹ ኃይል ውስጥ የሌላ ሀገር ቅጥር ነፍሰገዳዮች የመኖራቸው ዘገባ ይፋ ከሆነ በኋላ፤ በተለይ ከሌሎች የአፍሪቃ ሃገራት በመጡ የውጪ ዜጎች ላይ ጥላቻ ይስተዋላል። ከቀናት በፊት ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ከ150 በላይ የውጪ ዜጎች መታሰራቸውንም አመልክቷል።
የሱዳን የጸጥታ ኃይሎች የውጪ ዜጎች ከዋና ከተማዋ ኻርቱም እና በዙሪያ ካሉ አካባቢዎች እንዲወጡ ትዕዛዝ ሰጡ። ፖሊስ ባወጣው ማሳሰቢያ መሠረት የውጪ ዜጎች ከተባለው የሱዳን አካባቢ ለመውጣት የሁለት ሳምንት ጊዜ ብቻ ነው የተሰጣቸው። በመንግሥት ወታደሮችና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች መካከል የሚካሄደው ውጊያ ተጠናክሮ በመቀጠሉ የውጪ ዜጎች ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ አካባቢውን ለቀው መውጣት እንዳለባቸው ፖሊስ አሳስቧል። ሮይተር መገናኛ ብዙሃንን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ በፈጥኖ ደራሹ ኃይል ውስጥ የሌላ ሀገር ቅጥር ነፍሰገዳዮች የመኖራቸው ዘገባ ይፋ ከሆነ በኋላ፤ በተለይ ከሌሎች የአፍሪቃ ሃገራት በመጡ የውጪ ዜጎች ላይ ጥላቻ ይስተዋላል። ከቀናት በፊት ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ከ150 በላይ የውጪ ዜጎች መታሰራቸውንም አመልክቷል።
የዶቼቬለ ስርጭት ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት በአሁኑ ጊዜ ፓስፖርት ማግኘት ችግር አይደለም ሲል ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
በሺህዎች የሚቆጠሩ የሶማሌላንድ ወታደሮች ለስልጠና ኢትዮጵያ ገብተዋል፤ የሶማሊያ ወታደሮች ደግሞ ኤርትራ ውስጥ እየሰለጠኑ ነው። እነዚህና ሌሎች ዘገባዎች በዜና መጽሔት ዝግጅታችን ይቀርባሉ።
ሳምንታዊው የወጣቶች መድረክ ተደራራቢ የአካል ጉዳት ሳይበግራት ሰሞኑን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተመረቀች አንዲት ታታሪ ወጣትን ያስተዋውቀናል። የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ቅኝት ደግሞ ሰሞኑን በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች አነጋጋሪ በነበሩ ጉዳዮች ላይ የተሰጡ አስተያየቶችን ጨምቆ ያቀርብልናል። ለሁሉም ቀጠሮአችሁ ከምሽቱ አende ሰዓት ላይ ከሚጀምረው የዶቼቬለ የአማርኛው ስርጭት ጋር ይሁን
የኢትዮጵያ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት በአሁኑ ጊዜ ፓስፖርት ማግኘት ችግር አይደለም ሲል ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
በሺህዎች የሚቆጠሩ የሶማሌላንድ ወታደሮች ለስልጠና ኢትዮጵያ ገብተዋል፤ የሶማሊያ ወታደሮች ደግሞ ኤርትራ ውስጥ እየሰለጠኑ ነው። እነዚህና ሌሎች ዘገባዎች በዜና መጽሔት ዝግጅታችን ይቀርባሉ።
ሳምንታዊው የወጣቶች መድረክ ተደራራቢ የአካል ጉዳት ሳይበግራት ሰሞኑን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተመረቀች አንዲት ታታሪ ወጣትን ያስተዋውቀናል። የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ቅኝት ደግሞ ሰሞኑን በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች አነጋጋሪ በነበሩ ጉዳዮች ላይ የተሰጡ አስተያየቶችን ጨምቆ ያቀርብልናል። ለሁሉም ቀጠሮአችሁ ከምሽቱ አende ሰዓት ላይ ከሚጀምረው የዶቼቬለ የአማርኛው ስርጭት ጋር ይሁን
https://p.dw.com/p/4iDsJ?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
ተደራራቢ የአካል ጉዳተኝነት ከመድረሻዋ ያላቆማት ወጣት
አካል ጉዳተኞች እንደ አካል ጉዳታቸው ክብደት እና ተፈጥሮ የተለያዩ ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ፈተናዎች ሊያጋጥሟቸው ይችላሉ። እንደዚያም ሆኖ ግን በገጠማቸው የአካል ጉዳት ማህበረሰቡም ሆነ ከተፈጥሯዊ ሁኔታዎች ታግለው አሸንፈው ለአካል ጉዳተኞች ብቻም ሳይሆን ለሌሎቹም ጭምር አርአያ የሆኑ ተጠቃሽ ሰዎች ጥቂት አይደሉም ።
https://p.dw.com/p/4iEKK?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
በአማራ ክልል የኢንተርኔት መቋረጥ ያስከተለዉ መጠነሰፊ ችግር
በአማራ ክልል የፀጥታ ሁኔታን ተከትሎ በአብዛኛ አካባቢዎች የኢንተርኔት አገልግሎት እንደተቋረጠ ነዉ። የስራ ባህሪያቸው ከኢንተርኔት ጋር ግንኙነት ያላቸው ተቋማትና ግለሰቦች በዚህ ምክንያት ለበርካታ ችግሮች መዳረጋቸውን እያማረሩ ነዉ፡ በክልሉ የተደነገገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መጠናቀቅን ተከትሎ የኢንተርኔት አገልግሎት ይጀምራል ተብሎ ነበር።
https://p.dw.com/p/4iDlw?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
የታገቱት ተማሪዎች ጉዳይ፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሱዳን ጉብኝት፤ የአዉሮጳ እግርኳስ ግጥምያ
ኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በታጣቂዎች ከታገቱት 167 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች 160ዎቹ መለቀቃቸውን የመንግሥት ባለሥልጣናት ቢናገሩም ቤተሰቦች ግን እስካሁን ልጆቹ እንዳልተለቀቁ አስታዉቀዋል። ኧረ እንደታገቱ ነው። ከታገቱት ተማሪዎች ውስጥ የኔ ባች የሆኑ በርካታ ጓደኞቼ አሁንም በአፋኞች እጅ ዉስጥ ናቸዉ ሲሉ ተማሪዎችተናግረዋል።
https://p.dw.com/p/4iEgG?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
በአፍሪቃዉ ቀንድ አዲስ የፖለቲካ አሰላለፍ እና የተንታኝ አስተያየት
በሺዎች የሚቆጠሩ የሶማሊላንድ ወታደሮች ወታደራዊ ሥልጠና ለመውሰድ ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸው የራስ ገዝ የሶማሊላንድ ምንግስታዊ ሚዲያ ዘገበ፡፡ በበርካታ አውቶብሶችና የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ ያሳየው መንግስታዊ ሚዲያው፤ ለወታደራዊ ሥልጠና ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ ናቸው ሲል አስታዉቋል።
https://p.dw.com/p/4iE9m?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
ብሪታንያ፤ ህገወጥ የተባሉትን ስደተኞችን ወደ ርዋንዳ የመመለስ እቅድ ተሰርዟል መባሉ
የሐምሌ አምስቱን የብሪታንያ ምርጫና የሠራተኛው ፓርቲ ጠቅላላ ድልን ተከትሎ አዲሱ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ኪየር ስታርመር የመጀመርያ የቢሮ ስራቸው ባለፈው በወግ አጥባቂው ፓርቲ ተደንግጎ የነበረውን ህገወጥ የተባሉትን ስደተኞችን ወደ ርዋንዳ የመመለስ ስራ ከመሰረቱ መሰረዝ መሆኑን አስታውቀዋል። “ዋናው መርሀችን ህዝብን ማገልገል ነው”
https://p.dw.com/p/4iDxY?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ውሎ
የሲዳማ ክልል 3ኛ ዓመት 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ እያካሄደ ይገኛል ፡፡ ም/ቤቱ የክልሉን ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አዳምጧል፡፡ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በአቶ ደስታ ሌዳሞ የቀረበው የ2016 ዓ.ም የሥራ ሪፖርት በማህበራዊ ፣ በምጣኔ ሀብታዊና በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራትን የዳሰሰ ነው ፡፡
https://p.dw.com/p/4iEqZ?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
የሐምሌ 5 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም ዜና
ኻርቱም፤ የሱዳን ፖሊስ የውጪ ዜጎች ከኻርቱም እንዲወጡ ማዘዙ ናይሮቢ፤ የኬንያ ፖሊስ አዛዥ ሥራቸውን ለቀቁ ናይሮቢ፤ የኬንያ ወጣቶች ተቃውሟቸውን ሊቀጥሉ እንደሚችሉ ማስጠንቀቃቸው ጄኔቫ፤ የሱዳን ተቀናቃኝ ኃይላት ለውይይት ጄኔቫ ሞስኮ፤ ሩሲያ በኔቶ ጉባኤ የባይደንን ስህተት ዓለም ልብ ይበልልኝ ማለቷ ካታማንዱ፤ ኔፓል ውስጥ የደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ
https://p.dw.com/p/4iDtG?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
DW
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የሥራ እንቅስቃሴ
ላለፉት 30 ዓመታት ከሀገር ለመውጣትም ይሁን ከውጭ ወደ ውስጥ ለመግባት "እግድ" ተጥሎባቸው የነበሩ የተባሉ 10 ሺህ ሰዎች ከእግድ ነፃ መደረጋቸውን የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስታወቀ። ሦስት የተቋሙ የበላይ ኃላፊዎች በሰጡት መግለጫ እነዚህ ከእግድ ነፃ የሆኑ ሰዎች ጉዳያቸው "በተረሳ ሁኔታ" ውስጥ የነበሩ ናቸው።
የሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ/ም የዓለም ዋና ዋና ዜና • ሞቃዲሾ ውስጥ እስር ቤት ሰብረው ለማምለጥ የሞከሩ አምስት የአልሸባብ አባላት መገደላቸውን የማረሚያ ቤቱ ባለስልጣናት አስታወቁ ። በሙከራው በነበረው የተኩስ ልውውጥ ሶስት የጥበቃ አባላትም ተገድለዋል።
• በናይሮቢ በቆሻሻ መጣያ ውስጥ ተቆራርጦ የተጣሉ የሰዎች አስክሬኖች ከተገኑ በኋላ የፖሊስ እጅ ይኖርበት እንደሁ እያመረመረ መሆኑን የኬንያ ፖሊስ ተከታታይ ቡድን አስታወቀ።
• በሳህል ሃገራት ከአልቃኢዳ እና ከአይ ኤስ ጋር ግንኙነት ባላቸው አክራሪ ኃይላት የተስፋፋው ሽብርተኝነት እና የተደራጁ ወንጀሎች በቀጣናው ብርቱ ስጋት መደቀናቸው የተመድ አስታወቀ።
• እስራኤል የሃማስ ወታደራዊ ክንፍ አዛዥን ዒላማ ያደረገ የአየር ጥቃት መፈጸሟን ካስታወቀች በኋላ ሐማስ ጥቃቱን ሐሰት ነው በማለት አስተባብሏል። ሐማስ ማስተባበያውን ያወጣው የእስራኤል ባለስልጣናት የሃማስ ወታደራዊ ክንፍ አዛዥ መሐመድ ደኢፍ የአየር ጥቃት ዒላማ መደረጉን ዛሬ ካስታወቁ በኋላ ነው ።
• አሜሪካ የረዥም ርቀት ተምዘግዛጊ ሚሳኤሎቿን ጀርመን የምትተክል ከሆነ በአጸፋው የአውሮጳ ዋና ዋና ከተሞችን ዒላማ ለማድረግ እገደዳለሁ ስትል ሩስያ አስጠነቀቀች።
https://p.dw.com/p/4iFvh?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
👉🏾 @dwamharicbot
• በናይሮቢ በቆሻሻ መጣያ ውስጥ ተቆራርጦ የተጣሉ የሰዎች አስክሬኖች ከተገኑ በኋላ የፖሊስ እጅ ይኖርበት እንደሁ እያመረመረ መሆኑን የኬንያ ፖሊስ ተከታታይ ቡድን አስታወቀ።
• በሳህል ሃገራት ከአልቃኢዳ እና ከአይ ኤስ ጋር ግንኙነት ባላቸው አክራሪ ኃይላት የተስፋፋው ሽብርተኝነት እና የተደራጁ ወንጀሎች በቀጣናው ብርቱ ስጋት መደቀናቸው የተመድ አስታወቀ።
• እስራኤል የሃማስ ወታደራዊ ክንፍ አዛዥን ዒላማ ያደረገ የአየር ጥቃት መፈጸሟን ካስታወቀች በኋላ ሐማስ ጥቃቱን ሐሰት ነው በማለት አስተባብሏል። ሐማስ ማስተባበያውን ያወጣው የእስራኤል ባለስልጣናት የሃማስ ወታደራዊ ክንፍ አዛዥ መሐመድ ደኢፍ የአየር ጥቃት ዒላማ መደረጉን ዛሬ ካስታወቁ በኋላ ነው ።
• አሜሪካ የረዥም ርቀት ተምዘግዛጊ ሚሳኤሎቿን ጀርመን የምትተክል ከሆነ በአጸፋው የአውሮጳ ዋና ዋና ከተሞችን ዒላማ ለማድረግ እገደዳለሁ ስትል ሩስያ አስጠነቀቀች።
https://p.dw.com/p/4iFvh?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
👉🏾 @dwamharicbot
DW
የሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ/ም የዓለም ዋና ዋና ዜና
የፕሪቶሪያው ግጭት የማቆም ስምምነት የአፈጻጸም ግምገማ
በአመዛኙ በጎ ነበር በተባለው የዚህ የስትራቴጂካዊ ግምገማ ውይይት፣ በሰሜን ኢትዮጵያ ሰላም ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ዘላቂ ድጋፍ እንደሚያደርግ የአፍሪካ ሕብረት አቋሙን ያሳየበት እንደነበርም ተገልጿል። https://p.dw.com/p/4iFb3?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
👉🏾 @dwamharicbot
በአመዛኙ በጎ ነበር በተባለው የዚህ የስትራቴጂካዊ ግምገማ ውይይት፣ በሰሜን ኢትዮጵያ ሰላም ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ዘላቂ ድጋፍ እንደሚያደርግ የአፍሪካ ሕብረት አቋሙን ያሳየበት እንደነበርም ተገልጿል። https://p.dw.com/p/4iFb3?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
👉🏾 @dwamharicbot
DW
የፕሪቶሪያው ግጭት የማቆም ስምምነት የአፈጻጸም ግምገማ
በአመዛኙ በጎ ነበር በተባለው የዚህ የስትራቴጂካዊ ግምገማ ውይይት፣ በሰሜን ኢትዮጵያ ሰላም ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ዘላቂ ድጋፍ እንደሚያደርግ የአፍሪካ ሕብረት አቋሙን ያሳየበት እንደነበርም ተገልጿል።