በቡና ጥራት ምርምር እና ቁሌት ዘዴዎች ላይ ለሴቶች ማህበር ስልጠና ተሰጠ
==========****=========
ዲላ፡ ታህሳስ 10/2018 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዳይሬክቶሬት በቡና ጥራት ግምገማ፣ በቡና ቁሌት እና በቡና ቅምሻ ርዕሶች ላይ ለ“ዉሊ አብንዶ” የሴቶች ማህበር ስልጠና ሰጥቷል። ስልጠናው 12 የማህበሩ ሴት አባላትን ያሳተፈ ነበር።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክተር አቶ ተካልኝ ታደሰ፣ ስልጠናው ቡናን በጥራት ቆልቶ በማሸግ፣ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ማቅረብ እንዲቻል የሚያግዝ መሆኑን ገልፀው፣ ሙያዊ እገዛና የዕውቀት ሽግግር ማድረግ በጥራት ምርት ለማቅረብና ደንበኛን ለማፍራት እንደሚያግዝ አመልክተዋል።
አቶ ተካልኝ በተጨማሪም፣ ማህበራቱ ይህን ቴክኒካል ዕውቀት ቀድሞ ማግኘታቸው ሌሎችንም ሴቶች በተጠቃሚነት ለማሳተፍ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዳይሬክተር አለሙ ደሳ (ዶ/ር) ስልጠናው ዩኒቨርሲቲው ለማህበረሰቡ ከሚያደርገው ድጋፍ አንዱ መሆኑን ገልጸው፣ ማህበሩ የቡናን ጥራት በጠበቀ መልኩ፣ ከዝግጅት ጀምሮ ለገበያ እስከማቅረብ ድረስ ያለውን ሂደት እንዲረዱ፣ በተግባር የተደገፈ የክህሎት ስልጠና መሆኑን እስረድተዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም፣ ስልጠናው ሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ እንዲሁም የአካባቢው ቡና ጥራቱን ጠብቆ እና በሳይንሳዊ መንገድ ተዘጋጅቶ ለገበያ እንዲቀርብ አስፈላጊ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
በተያያዘ ዜና፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም የሶስተኛ ዙር የቡና ሰልጣኞች በቡና ምርትና ልማት ዙሪያ የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል። የመስክ ጉብኝቱ በክፍል ውስጥ በንድፈ ሃሳብ የተማሩትን ትምህርቶች በተግባር ለማጠናከር የተዘጋጀ ሲሆን፣ ከዘር ጀምሮ እስከ ችግኝ ዝግጅት፣ የችግኝ እድገትና እንክብካቤ ድረስ በተግባር እንዲማሩ ለማስቻል ነው።
ጉብኝቱ በዱመርሶ ችግኝ ጣቢያና በወናጎ ወረዳ በካራ ሶዲቲ ቀበሌ ያሉ የአርሶ አደር እና ሞዴል አርሶ አደር ማሳዎች ላይ የተደረገ ሲሆን፣ የዚህ ዙር ሰልጣኞችም በዩኒቨርሲቲው የሚሰጠው ስልጠና ከተግባራዊ ምልከታ ጋር በማጣጣም ያገኙት ዕውቀት በዘርፉ ላይ ለሚሰሩት ስራ እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ!
==========****=========
ዲላ፡ ታህሳስ 10/2018 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዳይሬክቶሬት በቡና ጥራት ግምገማ፣ በቡና ቁሌት እና በቡና ቅምሻ ርዕሶች ላይ ለ“ዉሊ አብንዶ” የሴቶች ማህበር ስልጠና ሰጥቷል። ስልጠናው 12 የማህበሩ ሴት አባላትን ያሳተፈ ነበር።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክተር አቶ ተካልኝ ታደሰ፣ ስልጠናው ቡናን በጥራት ቆልቶ በማሸግ፣ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ማቅረብ እንዲቻል የሚያግዝ መሆኑን ገልፀው፣ ሙያዊ እገዛና የዕውቀት ሽግግር ማድረግ በጥራት ምርት ለማቅረብና ደንበኛን ለማፍራት እንደሚያግዝ አመልክተዋል።
አቶ ተካልኝ በተጨማሪም፣ ማህበራቱ ይህን ቴክኒካል ዕውቀት ቀድሞ ማግኘታቸው ሌሎችንም ሴቶች በተጠቃሚነት ለማሳተፍ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዳይሬክተር አለሙ ደሳ (ዶ/ር) ስልጠናው ዩኒቨርሲቲው ለማህበረሰቡ ከሚያደርገው ድጋፍ አንዱ መሆኑን ገልጸው፣ ማህበሩ የቡናን ጥራት በጠበቀ መልኩ፣ ከዝግጅት ጀምሮ ለገበያ እስከማቅረብ ድረስ ያለውን ሂደት እንዲረዱ፣ በተግባር የተደገፈ የክህሎት ስልጠና መሆኑን እስረድተዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም፣ ስልጠናው ሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ እንዲሁም የአካባቢው ቡና ጥራቱን ጠብቆ እና በሳይንሳዊ መንገድ ተዘጋጅቶ ለገበያ እንዲቀርብ አስፈላጊ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
በተያያዘ ዜና፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም የሶስተኛ ዙር የቡና ሰልጣኞች በቡና ምርትና ልማት ዙሪያ የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል። የመስክ ጉብኝቱ በክፍል ውስጥ በንድፈ ሃሳብ የተማሩትን ትምህርቶች በተግባር ለማጠናከር የተዘጋጀ ሲሆን፣ ከዘር ጀምሮ እስከ ችግኝ ዝግጅት፣ የችግኝ እድገትና እንክብካቤ ድረስ በተግባር እንዲማሩ ለማስቻል ነው።
ጉብኝቱ በዱመርሶ ችግኝ ጣቢያና በወናጎ ወረዳ በካራ ሶዲቲ ቀበሌ ያሉ የአርሶ አደር እና ሞዴል አርሶ አደር ማሳዎች ላይ የተደረገ ሲሆን፣ የዚህ ዙር ሰልጣኞችም በዩኒቨርሲቲው የሚሰጠው ስልጠና ከተግባራዊ ምልከታ ጋር በማጣጣም ያገኙት ዕውቀት በዘርፉ ላይ ለሚሰሩት ስራ እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ!
❤12👎5👍3
CALL FOR INNOVATIVE PROJECT PROPOSALS
===========**==========
Dilla University, through the University–Industry Linkage and Technology Transfer (UIL-TT) Directorate, invites innovative and impactful project proposals for the 3rd Call for Innovative and Technology Projects – 2025.
We encourage faculty members, researchers, and innovators to submit proposals that address real-world challenges and promote technology transfer, innovation, and sustainable development.
📌 Deadline: 29 December 2025
Let’s transform ideas into solutions and strengthen innovation at Dilla University!
===###===
#University_of_the_Greenland!
===========**==========
Dilla University, through the University–Industry Linkage and Technology Transfer (UIL-TT) Directorate, invites innovative and impactful project proposals for the 3rd Call for Innovative and Technology Projects – 2025.
We encourage faculty members, researchers, and innovators to submit proposals that address real-world challenges and promote technology transfer, innovation, and sustainable development.
📌 Deadline: 29 December 2025
Let’s transform ideas into solutions and strengthen innovation at Dilla University!
===###===
#University_of_the_Greenland!
❤17👍10👎1
ዲላ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ገቢ ተማሪዎችን እየተቀበለ ነው
=========**==========
ዲላ ዩኒቨርሲቲ በ2018ዓ.ም በአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ወደ ዩኒቨርሲቲው የተመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎችን እየተቀበለ ነው።
በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ወደ ዩኒቨርሲቲው የተመደቡ የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ተማሪዎች ዛሬ እና ነገ ተጠቃለው የሚገቡ ይሆናል።
ዩኒቨርሲቲው እንኳን ወደ አረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ በሰላም መጣችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ!
=========**==========
ዲላ ዩኒቨርሲቲ በ2018ዓ.ም በአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ወደ ዩኒቨርሲቲው የተመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎችን እየተቀበለ ነው።
በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ወደ ዩኒቨርሲቲው የተመደቡ የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ተማሪዎች ዛሬ እና ነገ ተጠቃለው የሚገቡ ይሆናል።
ዩኒቨርሲቲው እንኳን ወደ አረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ በሰላም መጣችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ!
❤42👍4👎3
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ
==========*=========
ታህሳስ 22/04/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ጋር 'ሲቢኢ በእጄ' የተሰኘ የዲታል ቁጠባና ብድር አገልግሎት ለማስጀመር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሟል።
በዚህ 'ሲቢኢ በእጄ' በተሰኘው አገልግሎት የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች ያለ ምንም ዋስትና በሞባይል ስልካቸው አማካኝነት ከአምስት መቶ እስከ አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር በፈለጉት ሰዓት የብድር አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ አለሙ(ዶ/ር)፣ ስምምነቱ ዩኒቨርሲቲው የጀመረውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ከማጠናከር ባሻገር የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች ስራቸውን ተረጋግተው እንዲሰሩ ብሎም የብድር አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው የሰራተኞቹን ፍላጎት ያማከሉ በርካታ ፕሮጀክቶችን ወደ ተግባር ለማስገባት በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ በቀጣይ ለሚያከናውናቸው ስራዎች ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ ስለመሆኑ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ሙሴ ከበደ በበኩላቸው፣ ባንኩ እየተገበረ ያለው ሲቢኢ በእጄ፣ የብድርና ቁጠባ ባህልን በማሳደግ የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። አክለውም የባንኩን መስፈርት ለሚያሟሉ የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች ባንኩ ለቤት መስሪያ፣ ለተሽከርካሪ መግዣና ለሌሎችም ፍላጎቶች የብድር አገልግሎት እንደሚሰጥ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ዲጂታል ባንኪንግ ስራ አስኪያጅ አቶ የሱፍቃድ ይርጋ፣ ፍላጎት ያላቸውን መምህራን እና ሰራተኞች ሲቢኢ በእጄ አካውንት በመክፍት በፈለጉበት ሰዓት ወደ ባንኩ በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው ብድር መውሰድ እንደሚችሉ ጠቁመው በቀጣይም ለተቋሙ ሰራተኞች በብድር እና ቁጠባው አሰራር ስርዓት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እንደሚዘጋጁ ገልፀዋል።
ስምምነቱን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ አለሙ(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ሙሴ ከበደ የተፈራረሙ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማት በቀጣይም በሌሎች የልማትና የቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ በትብብር ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለባንኩ ላበረከተው የላቀ አስተዋፅኦ የምስጋና ምስክር ወረቀት አስረክቧል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
==========*=========
ታህሳስ 22/04/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ጋር 'ሲቢኢ በእጄ' የተሰኘ የዲታል ቁጠባና ብድር አገልግሎት ለማስጀመር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሟል።
በዚህ 'ሲቢኢ በእጄ' በተሰኘው አገልግሎት የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች ያለ ምንም ዋስትና በሞባይል ስልካቸው አማካኝነት ከአምስት መቶ እስከ አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር በፈለጉት ሰዓት የብድር አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ አለሙ(ዶ/ር)፣ ስምምነቱ ዩኒቨርሲቲው የጀመረውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ከማጠናከር ባሻገር የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች ስራቸውን ተረጋግተው እንዲሰሩ ብሎም የብድር አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው የሰራተኞቹን ፍላጎት ያማከሉ በርካታ ፕሮጀክቶችን ወደ ተግባር ለማስገባት በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ በቀጣይ ለሚያከናውናቸው ስራዎች ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ ስለመሆኑ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ሙሴ ከበደ በበኩላቸው፣ ባንኩ እየተገበረ ያለው ሲቢኢ በእጄ፣ የብድርና ቁጠባ ባህልን በማሳደግ የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። አክለውም የባንኩን መስፈርት ለሚያሟሉ የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች ባንኩ ለቤት መስሪያ፣ ለተሽከርካሪ መግዣና ለሌሎችም ፍላጎቶች የብድር አገልግሎት እንደሚሰጥ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ዲጂታል ባንኪንግ ስራ አስኪያጅ አቶ የሱፍቃድ ይርጋ፣ ፍላጎት ያላቸውን መምህራን እና ሰራተኞች ሲቢኢ በእጄ አካውንት በመክፍት በፈለጉበት ሰዓት ወደ ባንኩ በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው ብድር መውሰድ እንደሚችሉ ጠቁመው በቀጣይም ለተቋሙ ሰራተኞች በብድር እና ቁጠባው አሰራር ስርዓት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እንደሚዘጋጁ ገልፀዋል።
ስምምነቱን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ኤልያስ አለሙ(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ሙሴ ከበደ የተፈራረሙ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማት በቀጣይም በሌሎች የልማትና የቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ በትብብር ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለባንኩ ላበረከተው የላቀ አስተዋፅኦ የምስጋና ምስክር ወረቀት አስረክቧል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
👍24❤23🙏3👎1
አዲስ ለገቡ የአቅም ማሻሻያ ኘሮግራም ተማሪዎች ገለፃ ተደረገ።
=======*=========
ዲ.ዩ: ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በ2018 ዓ.ሞ በአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ወደ ዩኒቨርስቲው ለተመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ገለፃ ተሰጥቷል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ዋና ሬጂስትራር አስናቀ ይማም (ዶ/ር)፣ በ2018 የትምህርት ዘመን የሪሚዲያል መግቢያ መስፈርቶችን አሟልተው ወደ ዩኒቨርሲቲው ለተመደቡ ተማሪዎች እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዉ፣ በአቅም ማሻሻያ ኘሮግራም ወደ ዩኒቨርሲቲው የተመደቡ በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ 2ሺ 674 እና በማህበራዊ ሳይንስ 1ሺ 484፣ በአጠቃላይ 4ሺህ 158 ተማሪዎች የተመደቡ መሆናቸውን ገልፀዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፍሬሽ ማን ፕሮግራም ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ዋና አስተባባሪ መምህር መንግሥቱ ተሾመ እንደተናገሩት ተማሪዎች እያንዳንዱን ተግባር ተከታትለው ተምረው ዉጤታማ መሆን እንዳለባቸው ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ መሠራቱን ተናግረዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት ም/ዲን እና የተማሪዎች አገልግሎት ዲን ተወካይ አቶ መልካሙ አለሙ በበኩላቸው ተማሪዎች በዶርሚተሪ አካባቢ፣ በምግብ አገልግሎት፣ በክሊኒክ አገልግሎት ዙሪያ እንዲሁም የመዝናኛ አገልግሎትን በተመለከተ፣ በሌላ በኩል የተማሪ መብቶች እና ግዴታዎች እንዲሁም የዲስፕሊን ቅጣት ሊያስከትሉ የሚችሉ ጉዳዮችን በተመለከተ ግንዛቤ መሠጠቱን ተናግረዋል።
ገለፃዉን ሲከታተሉ ካገኘናቸው ተማሪዎች መካከል እንደገለፁት በተቋሙ የተደረገላቸው አቀባበል እንዳስደሰታቸው እና በዩኒቨርሲቲው ቆይታቸው ሊጠብቋቸው ስለሚገባ የስነ-ምግባር መርሆዎች በቂ እዉቀት እንዳገኙ ገልፀዉልናል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ!
=======*=========
ዲ.ዩ: ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በ2018 ዓ.ሞ በአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ወደ ዩኒቨርስቲው ለተመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ገለፃ ተሰጥቷል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ዋና ሬጂስትራር አስናቀ ይማም (ዶ/ር)፣ በ2018 የትምህርት ዘመን የሪሚዲያል መግቢያ መስፈርቶችን አሟልተው ወደ ዩኒቨርሲቲው ለተመደቡ ተማሪዎች እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዉ፣ በአቅም ማሻሻያ ኘሮግራም ወደ ዩኒቨርሲቲው የተመደቡ በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ 2ሺ 674 እና በማህበራዊ ሳይንስ 1ሺ 484፣ በአጠቃላይ 4ሺህ 158 ተማሪዎች የተመደቡ መሆናቸውን ገልፀዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፍሬሽ ማን ፕሮግራም ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ዋና አስተባባሪ መምህር መንግሥቱ ተሾመ እንደተናገሩት ተማሪዎች እያንዳንዱን ተግባር ተከታትለው ተምረው ዉጤታማ መሆን እንዳለባቸው ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ መሠራቱን ተናግረዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት ም/ዲን እና የተማሪዎች አገልግሎት ዲን ተወካይ አቶ መልካሙ አለሙ በበኩላቸው ተማሪዎች በዶርሚተሪ አካባቢ፣ በምግብ አገልግሎት፣ በክሊኒክ አገልግሎት ዙሪያ እንዲሁም የመዝናኛ አገልግሎትን በተመለከተ፣ በሌላ በኩል የተማሪ መብቶች እና ግዴታዎች እንዲሁም የዲስፕሊን ቅጣት ሊያስከትሉ የሚችሉ ጉዳዮችን በተመለከተ ግንዛቤ መሠጠቱን ተናግረዋል።
ገለፃዉን ሲከታተሉ ካገኘናቸው ተማሪዎች መካከል እንደገለፁት በተቋሙ የተደረገላቸው አቀባበል እንዳስደሰታቸው እና በዩኒቨርሲቲው ቆይታቸው ሊጠብቋቸው ስለሚገባ የስነ-ምግባር መርሆዎች በቂ እዉቀት እንዳገኙ ገልፀዉልናል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ!
❤45🙏3👎2👍1
የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት
=====***======
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኤልያስ አለሙ መላው የክርስትና እምነት ተከታዮችን እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው፣ መላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በዓሉን ሲያከብር፣ ያለው ለሌለው በማካፈል፣ በመረዳዳት ስሜት በፍፁም መተሳሰብ እና ወንድማዊ ፍቅር መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ከቤተሰብ ብዙ ሺህ ኪሎሜትሮችን ርቀው በዓሉን በዩኒቨርሲቲው እያሳለፉ የሚገኙ ተማሪዎችም፣ ያላንዳች ሀሳብ በተለመደው መንገድ፣ ቤተሰብ ጋር ያሉ እስኪመስላቸው ድረስ በዓሉን በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች እንዲያከብሩ ለማስቻል ዩኒቨርሲቲው የተለመደውን ሁሉ ነገር ለማድረግ ዝግጅቱን ማጠናቀቁንም ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል።
በዩኒቨርሲቲው ከኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ጎን ለጎን የሌሎች ጎረበት ሀገራት ተማሪዎችም ስለመኖራቸው የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ፣ በዓሉን የጋራ በማድረግ ኢትዮጵያዊ ባህላችንን እና መልካም እሴቶቻችንን ለሌሎች በማጋራት ልናሳልፍ ይገባል ብለዋል።
በመጨረሻም በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት እና የደስታ በዓል እንዲሆን ተመኝተዋል።
================================
President of Dilla University Elias Alemu (PhD), has conveyed his heartfelt Christmas wishes to the entire Christian community on the joyous occasion commemorating the birth of Jesus Christ.
In his festive address, the President urged all members of the university to celebrate with a spirit of generosity—sharing with the less fortunate, offering comfort, and embracing humility and fraternal affection.
He further shared that the university has taken deliberate steps to ensure students far from home—some separated by thousands of kilometers—can still partake in Christmas traditions and feel a sense of familial warmth through organized events and gatherings.
Dr. Elias pointed out that alongside Ethiopian nationals, learners from various nations also study at Dilla. He encouraged everyone to celebrate collectively as an opportunity to showcase Ethiopia's rich cultural heritage and virtuous traditions.
The President expressed his hope that this Christmas be filled with peace, love, unity, and happiness.
===###===
#University_of_the_Greenland!
=====***======
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኤልያስ አለሙ መላው የክርስትና እምነት ተከታዮችን እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው፣ መላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በዓሉን ሲያከብር፣ ያለው ለሌለው በማካፈል፣ በመረዳዳት ስሜት በፍፁም መተሳሰብ እና ወንድማዊ ፍቅር መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ከቤተሰብ ብዙ ሺህ ኪሎሜትሮችን ርቀው በዓሉን በዩኒቨርሲቲው እያሳለፉ የሚገኙ ተማሪዎችም፣ ያላንዳች ሀሳብ በተለመደው መንገድ፣ ቤተሰብ ጋር ያሉ እስኪመስላቸው ድረስ በዓሉን በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች እንዲያከብሩ ለማስቻል ዩኒቨርሲቲው የተለመደውን ሁሉ ነገር ለማድረግ ዝግጅቱን ማጠናቀቁንም ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል።
በዩኒቨርሲቲው ከኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ጎን ለጎን የሌሎች ጎረበት ሀገራት ተማሪዎችም ስለመኖራቸው የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ፣ በዓሉን የጋራ በማድረግ ኢትዮጵያዊ ባህላችንን እና መልካም እሴቶቻችንን ለሌሎች በማጋራት ልናሳልፍ ይገባል ብለዋል።
በመጨረሻም በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት እና የደስታ በዓል እንዲሆን ተመኝተዋል።
================================
President of Dilla University Elias Alemu (PhD), has conveyed his heartfelt Christmas wishes to the entire Christian community on the joyous occasion commemorating the birth of Jesus Christ.
In his festive address, the President urged all members of the university to celebrate with a spirit of generosity—sharing with the less fortunate, offering comfort, and embracing humility and fraternal affection.
He further shared that the university has taken deliberate steps to ensure students far from home—some separated by thousands of kilometers—can still partake in Christmas traditions and feel a sense of familial warmth through organized events and gatherings.
Dr. Elias pointed out that alongside Ethiopian nationals, learners from various nations also study at Dilla. He encouraged everyone to celebrate collectively as an opportunity to showcase Ethiopia's rich cultural heritage and virtuous traditions.
The President expressed his hope that this Christmas be filled with peace, love, unity, and happiness.
===###===
#University_of_the_Greenland!
🙏36❤25👍8👎3
የስብሰባ ጥሪ
==****==
ለዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና አስተዳደር ሠራተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር አባላት በሙሉ
የዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና አስተዳደር ሠራተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር ጥር 02 ቀን 2018 ዓ.ም የማህበሩን 20ኛ አመት ምሥረታ በዓልን አስመልክቶ ጠቅላላ ጉባኤ ያካሄዳል፡፡
በዕለቱ ከጧቱ 2:30 ላይ በነባሩ ግቢ ሁለገብ አዳራሽ እንድትገኙ ማህበሩ ጥሪውን ያስተላልፋል።
#ማሳሰቢያ፡
1.ከአቅም በላይ ካልሆነ በስተቀር ማንኛውም የማህበሩ አባል በስብሰባው ላይ የመገኘት ግዴታ አለበት፡፡
2.በስብሰባው ላይ በተገኙ አባላት የሚወሰን ማንኛውም አይነት ውሳኔ ባልተገኙት አባላት ላይም ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
3.የሰርቪስ አገልግሎት በየፈርማታው ስለሚዘጋጅ 2፡00 ሰዓት ቀደም ብላችሁ በየፈርማታው እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
ከተባበርን እንችላለን!
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
==****==
ለዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና አስተዳደር ሠራተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር አባላት በሙሉ
የዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና አስተዳደር ሠራተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር ጥር 02 ቀን 2018 ዓ.ም የማህበሩን 20ኛ አመት ምሥረታ በዓልን አስመልክቶ ጠቅላላ ጉባኤ ያካሄዳል፡፡
በዕለቱ ከጧቱ 2:30 ላይ በነባሩ ግቢ ሁለገብ አዳራሽ እንድትገኙ ማህበሩ ጥሪውን ያስተላልፋል።
#ማሳሰቢያ፡
1.ከአቅም በላይ ካልሆነ በስተቀር ማንኛውም የማህበሩ አባል በስብሰባው ላይ የመገኘት ግዴታ አለበት፡፡
2.በስብሰባው ላይ በተገኙ አባላት የሚወሰን ማንኛውም አይነት ውሳኔ ባልተገኙት አባላት ላይም ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
3.የሰርቪስ አገልግሎት በየፈርማታው ስለሚዘጋጅ 2፡00 ሰዓት ቀደም ብላችሁ በየፈርማታው እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
ከተባበርን እንችላለን!
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
❤27👎6👍2