ድምፀ ተዋሕዶ
11.4K subscribers
3.42K photos
85 videos
189 links
ይህ መንፈሳዊ ቻናል መቀመጫውን እንግሊዝ ለንደን ያደረገ ማንኛውንም ታማኝ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የቤተ ክርስቲያን መረጃዎችን እና መንፈሳዊ ክንውኖችን ለምእመኑ በፍጥነት፤ በጥራት ያቀብላል።

የእግዚአብሔር ጸጋ እና በረከት በሁላችን ላይ ይደር።

ድምፀ ተዋሕዶ ለንደን
ለታማኝ መረጃዎ
Download Telegram
ከጳውሎስ ቤት ዴማስ ይሸፍት ዘንድ ግድ ነው።

ይህኝ ሁሉ ነፍሳት መጀመርያ የደነደነውን የጥላቻ ልባቸውን ሸፍነው ለኦርቶዶክስ የሳሱ ፣ርህራሄ ያሳዩ መስለው ለመግለጥ ሞከሩ።

በምንfiqina መኪና "ኦርቶዶክስ ነን" የሚል ታርጋ ከፊት አስለጥፈው ሮጡ።ከኦርቶዶክስ ቤት የሚያወጣን ማንም የለም ሲሉሳይጠየቁ ፎከሩ። ክርስቶስን ለመውደዳቸው ማስረጃ ይሆን ዘንድ እናቱን ሰደቡ።ቅዱሳንን አንጓጠው ቅዱሳን መላእክት ላይ ተሳለቁ።

መጽሐፍ ቅዱስን ስለመውደዳቸው መገለጫ ይሆን ዘንድ ሌሎች መጻህፍት ላይ የጥላቻ ዕጣ ተጣጣሉ።በሰፊው የቅድስና ውሃ ውስጥ ትንሽዬ መርዝ ሆነው ለመፍሰስ ሞከሩ።በተኩላነታቸው ላይ የበግ ቆዳ ለብሰው ተዟዟሩ።የትሩፋት ሥራ ሲያነዝራቸው፣የራሳቸውን መዳን መፈጸም ሲታክታቸው የእዛ ቤትን ጥቅስ ይዘው ለስንፍናቸው ምክንያት ፈለጉ።

ፈራጁን ክርስቶስ ከዙፋኑ ላይ አንስተው ለእራሳቸው ፈረዱ። እንደ ገላትያን ክርስቲያኖች ለኃጢያታቸው ክርስቶስን መገልገያ አደረጉ። እንግዲህ በአንድ ቤት ውስጥ ዴማስ ወይም ጳውሎስ ይኖር ዘንድ ግድ ነው። በጳውሎስ ቤት ዴማስ ምንም አይሰራም። በክርስቲያኖች እልፍኝ ኒቆላዊነት አይጸናም።

ለምዳችሁ መገፈፉ መልካም ቢሆንም በመጥፋታችሁ እናዝናለን!!!

መጨረሻችሁ ያምር ዘንድ ምኞቴ ነው !!!

Kune Demelash kassaye -Arba Minch
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
አሁን ያለውን ስናየው ግን ለማሰብ የሚከብድበት ደረጃም የደረሰ ይመስለኛል። ዛሬ አድማሱ ጀንበሬ የተቀበሉትን ስም ምን ዓይነት ሰዎች እንደሚጠሩበት ለመረዳት ፌስቡክን ማየት ብቻ ሊበቃ ይችላል። ስብከት የጀመረው ሁሉ የሚጠራበት ስም ነው። አሁንማ የስም እደላው ወደ ምእመናን ሁሉ ተሸጋግሮ፣ በኩረ ምእመናን፣ መጋቤ... የሚባለው ቁጥሩ በርካታ ሆኗል። ይህም አልበቃ ብሎ አንዳንድ ሰዎች የተጠና እና ማንም ያልተጠራበት አስፈጥረው እስከመቀበል ደርሰዋል። አንዳንዶች ደግሞ በሁለት ስም ሁሉ ይጠራሉ። ቢያንስ በንጉሡ ዘመን የሚቀበሉት ሰዎች የተመረጡ አይገባቸውም የማይባሉ፣ በብዙ ነገር የተመሰከረላቸው ነበሩ። ከሆነም እንኳ ያን መንገድ ባይለቅ አንድ ነገር ነበር። አሁን ግን ስም ማደሉ አስገራሚ ደረጃ ላይ ከመድረሱ የተነሣ ከበሽታነት ወደማይድን በሽታነት የተሸጋገረ ይመስለኛል። ኦ አኃውዬ ኢታፍቅርዎ ለዓለም ፣ ዓለሙኒ ሐላፊ፣ ንብረቱኒ ሐላፊ፣ እስመ ኩሉ ሓላፊ ውእቱ እያለች በቅዱስ ጳውሎስ ቃል ምእመናን ላይ በየቅዳሴው የምታውጅ ቤተ ክርስቲያን በዓለም እንኳ በሌለ በሽታ አገልጋዮቿን አስነድፋ መቀጠሏ የሚያስገርም ነው። ምንም እንኳ ጥናት የሚጠይቅ ቢሆንም ከላይ እንዳልኩት ይህ የመዓርግ ጣጣ ነገሥታትን ጥላ አድርጎ ከቤተ መንግሥት የገባ እንጂ ከቤተ ክርስቲያን አስተምህሮም ሆነ ትውፊት ምንም መነሻ የለውም። እንሰጠውም ከተባለ ከእናንተ ማንም መምህር ሊቅ ተብሎ አይጠራ የሚለው የጌታ ትምህርት ነው የሚመለከተው። እርሱም የሚቃወመው እንጂ የሚያጸድቀው እንዳልሆነ እናውቃለን። ታዲያ ጨርሶ አይጥፋ እንኳ ከተባለ ሁሉ በአግባብ እና በሥርዓት ይሁን በሚለው ቃለ ሐዋርያ መመራት ሲገባው እዚህ ደረጃ መድረሱ አሳዛኝ ነው። ምንአልባት አንዳንድ ሰዎች እንደሚሉት እንደ መጠሪያ ስም ወይም እንደ ክርስትና ስም ለሁሉም ከተዳረሰ በኋላ በዚያ በኩል ይጥፋ ተብሎ ካልሆነ በቀር አሁን ያለበት ደረጃ አሳፋሪነትን ያለፈ በእጅጉ አስቀያሚ የሆነ ይመስለኛል።

እንደ እኔ እንደ እኔ ቤታችን ቢያንስ በጉዳዩ ላይ ውይይት አድርጎ ቢያንስ በመመሪያ እና በሕግ መገደብ እና ትንሽ እንኳ ድንበር ያለው ነገር እንዲሆን ሊታሰብበት አይገባም ትላላችሁ? ቤተ ክርስቲያኒቱ ንጽሕት ክብርት የመሆኗን ያህል በዚህ ዘመን ያለን ልጆቿ ደግሞ ያላራከስነው ነገር ያለ አይመስልም። ለሁሉም መዳኛውን ይስጠን።

መምህር ብርሃኑ አድማስ
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM