Construction Proxy
19.5K subscribers
530 photos
18 videos
77 files
284 links
#1 construction portal to get:
construction news
construction market
construction materials price
engineering estimates
Sub contract
https://constructionproxy.com
Address any comment to admin👨‍💼 @ConproxyBot
Download Telegram
Eid Mubarak
PROJECT MANAGER
WALIIF CONSTRUCTION SHARE COMPANY CIVIL ENGINEERING CONTRACT May 16, 2021 - May 21, 2021
Description
Job Requirement
Education: BSc in Civil Engineering or Construction Technology & Management
Related Experience: 10 years and above
Place of Work: Project Sites (out of Addis Ababa)

How to Apply
Closing Date:5 (five) consecutive days from the first date of announcement
Interested applicants who fulfill the above requirements can submit their application with non- returnable copies of the CV’s.
Address: Arat Kilo, Infront of Berhanena Selam Printing Press at Dink Sira Building 8th Floor Tel. 0118124767 Email: wcsc1002@gmail.com
1
% of urban households in Africa who can afford the cheapest newly built house in 2020

According to the research based on income data, 3.52% Ethiopians can afford US $17, 226 for houses.

@Businessinfoeth
የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫ እና ምዝገባ አዲስ መመሪያ ወጣ
*************
የኮስተባ ሕዝብ ግንኑነትና ኮሙኒኬሽን
ሰኔ 7 ቀን 2013 ዓ.ም
*************
የኮንስትራክሽን ባለሙያ፣ አማካሪ፣ የስራ ተቋራጭ ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ እንዲሁም የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ምዝገባ መመሪያ 648/2013 በአዲስ መልክ ፀድቆ መውጣቱ ተመለከተ፡፡

በዚሁ መሰረትም የቀድሞው የኮንስትራክሽን ባለሙያዎችና ስራ ተቋራጮች የምዝገባ መመሪያ ቁጥር 19/2005፤የኮንስትራክሽን ዲዛይን ባለሙያዎችና አማካሪዎች ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 22/2005 ፣ እንዲሁም የቀድሞውን መመሪያ ተከትሎ ወጥተው የነበሩ መስፈርቶችም አዲስ በፀደቀው የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 648/2013መሰረት የተሻሩ መሆናቸው ተመልክቷል::

ይህ የተመለከተው የኮንስትራክሽን ስራዎች ተቆጣጣሪ ባለስልጣን የህግ ዝግጅት ኮድና ስታንዳርድ ዳይሬክቶሬት ለተቋሙ የምዝገባና ሰርተፊኬሽን ስራ ክፍል ሀላፊዎችና ሰራተኞች እንዲሁም በዘርፉ የሚመለከታቸውን የተጠሪ ተቋማት ሃላፊዎችና ባለሙያዎችን አዲስ በፀደቀው የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 648/2013 ላይ በቢሾፍቱ ከተማ ሰሞኑን ባተዘጋጀ የስልጠና መርሃግብር ነው፡፡
በስልጠናው ላይ እንደተመለከተው አዲሱ የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 648/2013 ከረቂቅ ዝግጅቱ አንስቶ አስከ ፀደቀበት ድረስ የተከናወኑ ተግባራት፣ መነሻ መርሆዎቹና አስፈላጊነቱ ተብራርቷል፡፡

በዋናነትም ሀገራዊ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ተሳታፊዎችን በጥራት እና በብዛት ለማሳደግ ብሎም ውድድሩን ለማስፋት ዕድል የሚፈጥር መመሪያ ሆኖ መዘጋጀቱ ነው የተመለከተው፡፡

በተያያዘም የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ሀገርንና ህዝብን ወደ ብልፅግና የሚያሸጋግር መደላድል እንዲሆን የሚስችለውን የአፈፃፀም ሚና ማሳደግ ፣ የምዝገባ አገልግሎት አሰጣጥንና የመረጃ አያያዝን ምቹና ዘመናዊ ማድረግ፣ በኢንዱስትሪው ውስጥ የተንሰራፋውን ብልሹ አሰራር ማስወገድ፣ ዘርፉ ዕውቀት መር እንዲሆን ማስቻል የመመሪያው አበይት መርሆዎች እንደሆኑም ተገብራርቷል፡፡

ኢንዱስትሪው በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ማለትም በጊዜ፣ በዋጋ፣ በጥራት እና በደህንነት ረገድ ያሉበትን አሉታዊ ገፅታው እንዲለወጥ የሚያስችል ምቹ የአሰራር ስርዓትን መዘርጋትም ሌላው መርህ ነው፡፡
እንዲሁም ኢትዮጵያን በቀጣይ አስር ዓመታት ውስጥ አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተያዘውን ራዕይ ለማሳካት በሚደረገው ርብርብ ውስጥ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የላቀ ሚና እንዲጫወት ማስቻልም ትኩረቱ ነው፡፡

አዲሱ የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያው ከረቂቅ ጀምሮ እስከ ፀደቀበት ድረስ በተለያዩ ባለድርሻ አካላት እየታየ ያለፈባቸውን ሂደቶች፤ በዝግጅት ሂደቱ ውስጥም የተገኙ ግብዓቶች ተካትተው በጠቅላይ አቃቤ ሕግ አማካኝነት ግብዓት ተሰጥቶ የጸደቀ መሆኑም ተብራርቷል፡፡

በመመሪው የሚካተቱ የግንባታ ተዋናዮችና ዘርፎች፣ የመመሪያው ይዘቶች፣ የሚጠበቁ መስፈርቶች፣ የብቃት አረጋጋጭ እና መዝጋቢዎች ኃላፊነቶች የሚሉና ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮች ላይ ያጠነጠኑ ሰነዶች ለሰልጣኞች ቀርበዋል፡፡

ተሳታፊዎች በበኩላቸው ለስራ አፈፃፀም ተግዳሮት ናቸው እንዲሁም መሻሻል ይገባቸዋል ያሏቸውን አስተያየቶች ሰጥተዋል፤፡ በዋናነትም ከፍትሃዊ አሰራር፣ ሚዛናዊነት ከመጠበቅ፣ ከመረጃ ነፃነት፣ ከመመሪው አስገዳጅነት እና ከአሻሚነት አንፃር ይሻሻሉ ሏቸውን ሃሳቦች አካፍለዋል፡፡
በአጠቃላም ሀገራዊ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ከፍ ከማድረግ አኳያ በመመሪው ውስጥ መካተት ያሉባቸው እንዲሁም እርምት ያስፈልጓቸዋል ያሏቸውን አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡

በቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ የተለያዩ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ግብረመልስ ሰጥተዋል፡፡ መሰረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይም መመሪያው እንደገና እርማት የሚወሰድበት አግባብ በቀጣይ የሚታይ መሆኑም ተመልክቷል፡፡

በዋናነት ግን መመሪው በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ላይ መሰረታዊ ለውጥ እንዲመጣ፣ ተወዳዳሪነቱ እንዲያድግ፣ ሙያ እና ዕውቀት ተኮር እንዲሆን፣ የተሳለጠና አስተማማኝ መረጃ እንዲፈጠር፣ የአሰራር ስርዓቱ እንዲዘምን፣ ከፍተኛ የሆነ የስራ ዕድልን እንዲፈጥር፣ ሙዊ ስነምግባር እና ሕጋዊነት እንዲሰፍን፣ ጥራትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የግንባታ ስርኣት እውን እንዲሆን ለማስቻል ወሳኝነቱ ተሰምሮበታል፡፡
ገምሹ በየነ ኮንስትራክሽን በ4.2 ቢሊዮን ብር መንገድ ሊገነባ ነው

ከ4.2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ኦሮሚያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልልን የሚያስተሳስረው 160 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጀመረ፡፡

የግንባታ ስራውን የሚያካሂደው ገምሹ በየነ ኮንስትራክሽን ኋ/የተ/የግ/ማ የተባለ አገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡

የመንገዱን ጥራት ቁጥጥር እና የማማከር ሥራዎችን የሚያከናውነው ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን እና ቁጥጥር ስራዎች ድርጅት ነው።

የግንባታዉ ወጪው የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በሶስት አመታት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል።
መንገዱ በገጠር ከ8-10 ሜትር ߹ በቀበሌ 12 ሜትር፣ በወረዳ የእግረኛ መንገድን አካቶ ከ19-24 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ይገነባል።
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
የታጣቂዎች ጥቃት የሁለት ወጣት ኢንጂነሮችን ነፍስ ነጠቀ።

በኮንስትራክሽን የስራ ላይ ተሰማርተው በሙያቸው ሀገራቸውን እና ህዝባቸውን እያገለገሉ የነበሩ ሁለት ወጣት ኢንጂነሮች በታጣቂዎች ተገደሉ።

#አሥራት_ሺካ እና #ሮቤል_ልደቱ የተባሉት ወጣት ኢንጂነሮች ትላንት ሰኔ 8/2013 ለሥራ ጉዳይ "አማሮ ልዩ ወረዳ" ሲጓዙ "ጀሎ" በምትባል ቀበሌ በታጣቂዎች በተከፈተባቸው ተኩስ ህይወታቸው አልፏል።

ሁለቱም ወጣት ኢንጂነሮች ባላቸው እውቀት ህዝባቸውን እና ሀገራቸውን በማገልገል ላይ እያሉ ነው በታጣቂዎች በግፍ የተገደሉት።

የወጣቶቹን ግድያ የአማሮ ልዩ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያረጋገጠ ሲሆን ጉዳዩን ለደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አሳውቀናል ብሏል።

በሌላ በኩል የደቡብ ክልል ኮንስትራክሽን ባለልስጣን ባወጣው የሀዘን መግለጫ ወጣት ሮቤል ልደቱ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የመንግስት ፕሮጀክቶች ግንባታ ጥራት ክትትል እና ቁጥጥር ስራ ሂደት ባለሞያ እንደነበር ገልጾ በህልፈቱ የተሰማውን ሀዘን ገልጿል።

ባልስልጣኑ 'ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት' ብሎ ከመግለፅ በዘለለ ዝርዝር መረጃ አልሰጠም።

የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ስለግድያው ፣ ጥቃት ፈፃሚዎቹ ስለመያዛቸው እና ሌሎች ተያያዥ መረጃ እንዲሰጠን ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

@tikvahethiopia
Several cement plants in #Ethiopia will undergo maintenance beginning next month, aggravating fears that shortages in supply will send retail prices through the roof.

Via - AddisFortune
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
የታጣቂዎች ጥቃት የ10 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ።

• 10 ሰዎች ተገድለዋል።
• የሟቾች አስክሬን ዛሬ አርብ ለቤተሰቦቻቸው ይሰጣል።

ከቀናት በፊት በደቡብ 'አማሮ ልዩ ወረዳ' አካባቢ ታጣቂዎች የሁለት ወጣት ኢንጂነሮችን ህይወት በግፍ ማጥፋታቸውን ከሰማን በኃላ ዛሬ ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት በመንገድ ግንባታ ሥራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ 10 ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መግደላቸውን ሰምተናል።

ይህን መረጃ ይፋ ያደረገው ቢቢሲ የአማርኛው ክፍል ነው።

ጥቃት ተፈፅም የሰዎች ህይወት መጥፋቱን የምዕራብ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዲሪርሳ ዋቁማ ያረጋገጡ ሲሆን ጥቃቱ በዞኑ ሜታ ወልቂጤ ወረዳ "ሎያ ጎዳኔ" ቀበሌ ውስጥ ረቡዕ ሰኔ 09/2013 ዓ.ም አመሻሽ 12 ሰዓት አካባቢ መፈፁም ገልፀዋል።

በታጣቂዎች የተገደሉት የፌደራል እና የኦሮሚያ መንገዶች ባለስልጣን ባለሙያ የሆኑ 9 ሰዎች እና የቀበሌው ነዋሪ የሆነች አንዲት ሴት ናቸው ብለዋል።

ጥቃቱ በተፈጸመበት መኪና ውስጥ ከነበሩ 11 የመንገድ ሥራ ባለሙያዎች በሕይወት የተረፉ መኖራቸውንም አክለዋል።

በጥቃቱ የተገደሉት ሰዎች አስከሬን አዲስ አበባ ወደሚገኘው ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል መላኩን እና ለቤተሰቦቻቸው መርዶ መነገሩን ጠቅሰው አስከሬናቸው ዛሬ አርብ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።

አቶ ዲሪርሳ ፥ ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው አስራ አንድ የመንገድ ግንባታ ባለሙያዎች መካከል ከግድያው ያመለጡት ሁለቱ "በአካላቸው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም፤ ደህና ናቸው" ብለዋል።

በምዕራብ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ ጥቃቱን የፈጸመው "ኦነግ-ሸኔ" የተባለው ቡድን እንደሆነ ገልፀዋል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-06-18

@tikvahethiopia
#EthiopiaCheck Scam Alert

አሁንም ራሳችንን ከአታላዮች እንጠብቅ--- ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን

ኮርፖሬሽኑ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ፋኩልቲ እና የንግድ ሥራ ት/ቤት በታህሳስ ወር 2013 ዓ.ም በየሙያ መስኩ እና በየደረጃው ተመዝግበው መስፈርቱን ላሟሉ አመልካቾች ሰጥቶት በነበረው ፈተና ከማለፊያ ውጤት በታች ያገኙ ማለትም ከ 60% በታች ውጤት ያላቸውን ተወዳዳሪዎችን ስልክ እየደወሉ ገንዘብ ክፈሉና እናስቀጥራችኋለን በማለት የሚያታልሉ እና የኮርፖሬሽኑን መልካም ስም የሚያጎድፉ አጭበርባሪዎች እንዳሉ ወደ መ/ቤታችን በመምጣት ካመለከቱ ተወዳዳሪዎች መረዳት መቻሉን በመግለፅ የሚመለከታቸው አካላት ከመሰል አታላዮች እራሳቸውን እንዲጠብቁ ኮርፖሬሽናችን ቀደም ሲል ማሳሰቢያ መስጠቱ ይታወሳል፡፡

ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅትም ይህ የማታለል ድርጊት በሌለ መልኩ ቀጥሎ ስልክ እየደወለ ገንዘብ ከከፈላችሁኝ ከኮርፖሬሽኑ አንዱ ፕሮጀክት ወደ ሌላው እንድትዛወሩ አደርጋለሁ የሚል ግለሰብ ስለመኖሩ ይኸው የማታለል ሙከራ ደረሰብን ካሉ ግለሰቦች መረጃ ደርሶናል፡፡

በመረጃው መሠረት ይህን የማታለል ሙከራ እያደረገ ያለው ከዚህ ቀደም ኮርፖሬሽኑ በሰጠው ማሳሰቢያ ላይ ረቡኒ ኢሳያስ በሚል ስምና የስልክ ቁጥር 0966459226 በባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000338403422 ገንዘብ አስገቡ እና ሥራ አስቀጥራችኋለው እያለ የማታለል ሙከራውን የቀጠለው ይኸው ግለሰብ ገንዘብ ክፈሉና ትዛወሩበታላችሁ በሚል የሚጠቅሰው ፕሮጀክት በአሁኑ ጊዜ ሥራ ላይ የሌለ እና ቀደም ብሎ የተዘጋ ነው፡፡

በመሆኑም የሚመለከታችሁ አካላት ይህንኑ በመገንዘብ ከመሰል የመጭበርበር ጥቃት ራሳችሁን እንድትጠብቁ ኮርፖሬሽኑ በጥብቅ እያሳሰበ ጉዳዩን በሕግ አግባብ እየተከታተለው መሆኑን በድጋሚ ለማስታወስ ይወዳል፡፡
Reporter, Seni 13, 2013 EC
The_Addis_Ababa_City_Government_Construction_Professionals_Ethics.pdf
14.3 MB
The-Addis-Ababa-City-Government-Construction-Professionals-Ethics-Regulation-No-1022018.pdf
የአመልካቾች ዝርዝር.pdf
2.4 MB
All applicant for Addis Ababa city Roads Authorities
AACRA:
በጁኒየር ሲቪል መሀንዲስ ክፍት የስራ መደብ ላይ መስፈርቱን ያሟሉ ተወዳዳሪዎች በዕጣ ለመለየት በስማቸው የመጀመሪያ ፊደል የተለዩበት ዝርዝር

1 የስማቸው የመጀመሪያ ፊደል ሀ ፊደል እና ለ ፊደል ቤቶች የሆነ 6/11/13 - ጠዋት
2 የስማቸው የመጀመሪያ ፊደል መ ፊደል ቤቶች የሆነ 6/11/13 - ከሰዓት
3 የስማቸው የመጀመሪያ ፊደል ሰ/ሠ ፊደል እና ረ ፊደል ቤቶች የሆነ 7/11/13 - ጠዋት
4 የስማቸው የመጀመሪያ ፊደል ሸ፣ቀ እና በ ፊደል ቤቶች የሆነ 7/11/13 - ከሰዓት
5 የስማቸው የመጀመሪያ ፊደል ተ፣ ቸ እና ነ ፊደል ቤቶች የሆነ 8/11/13 - ጠዋት
6 የስማቸው የመጀመሪያ ፊደል አ ፊደል ቤቶች የሆነ 8/11/13 - ከሰዓት
7 የስማቸው የመጀመሪያ ፊደል ከ፣ ወ፣ ዘ እና የ ፊደል ቤቶች የሆነ 9/11/13 - ጠዋት
8 የስማቸው የመጀመሪያ ፊደል ደ፣ ጀ እና ገ ፊደል ቤቶች የሆነ 9/11/13 - ከሰዓት
9 የስማቸው የመጀመሪያ ፊደል ጠ፣ ጨ፣ ፀ፣ ፈ እና ፐ ፊደል ቤቶች የሆነ 13/11/13 - ጠዋት

ማሳሰቢያ

1. አመልካቾች እጣ ለማውጣት በሚመጡበት ቀን ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ ይዘው መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡
2. ዕጣ በምታወጡበት ቀን የስም ዝርራችሁ ያለበትን ተራ ቁጥር አይታችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን፡፡
3. ዕጣማውጣት የምትችሉት በወጣው ፕሮግራም ብቻ መሆኑን እያሳሰብን ከዛ ውጪ የሚመጣ አመልካች የማናስተናግድ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
#የአባይ_በረሃ መንገድ የመንሸራተት አደጋ አጋጥሞታል።

ከአዲስ አበባ ወደ ባህር ዳር የሚወስደው ዋናው መንገድ በአባይ በረሀ ውስጥ የመሸራተት አደጋ ስለደረሰበት ለተሽከርካሪዎች ዝግ ሆኗል።