Construction Proxy
19.4K subscribers
527 photos
17 videos
75 files
282 links
#1 construction portal to get:
construction news
construction market
construction materials price
engineering estimates
Sub contract
https://constructionproxy.com
Address any comment to admin👨‍💼 @ConproxyBot
Download Telegram
#ነዳጅ

በጥር ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር ከታሕሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በታሕሳስ ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን አሳውቋል።

አሁን ላይ ያለው የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ስንት ነው ?

- ቤንዚን 129.12 ብር በሊትር
- ነጭ ናፍጣ 129.12 ብር በሊትር
- ኬሮሲን 129.12 ብር በሊትር

የሌሎች ምርቶችም ዋጋ በታሕሳስ ወር በነበረበት ይቀጥላል።
👍16🙏4👏3👌3🔥2
648_የኮንስትራክሽን_ብቃት_ማረጋገጫና_ምዝገባ_መመሪያ.pdf
2.7 MB
የ ኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያ
- ኮንትራክተር ከ ደረጃ 1 እስከ 10
- የአማካሪ መሃንዲስ ፈቃድ
- ባለሙያ ሁሉም አይነት
👍4519
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ዛሬ ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ስራ አስጀመሩ።
👍3114
2018 2nd Q Construction Works (Only Direct Cost)(1).pdf
22.7 MB
የ2018 ዓ/ም 2ኛ ሩብ ዓመት የኮንስትራክሽን ስራዎች ቀጥተኛ ዋጋ ጥናት

2018E.C  2nd Quarter Construction Works (Only Direct Cost)t

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ
👍4326🔥3
1997 እና ለ2005 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች በሙሉ!
http://aahdab.et/saving
2👍2911🙏4
#ነዳጅ
#የካቲት

" ከአውሮፕላን ነዳጅ በቀር የሌሎች ነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል " - ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር

#ማስታወሻ ፦ አሁን ላይ ያለው የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ስንት ነው ?

- ቤንዚን 129.12 ብር በሊትር
- ነጭ ናፍጣ 129.12 ብር በሊትር
- ኬሮሲን 129.12 ብር በሊትር
👍18🙏4👏2🤔2👌1
It would be better if the new road section were planned strictly as an NMT (Non-Motorized Transport) route, with no motorized traffic allowed, i am just saying .
አዲሱ የመንገድ ክፍል ለNMT (ለእግረኞችና ለብስክሌት) ብቻ እንዲዘጋጅ እና የሞተር ተሽከርካሪ እንዳይፈቀድ ቢሆን ይሻላል ነበር።
22👍22😁5🔥3🤔3
ዜና ሹመት
ዶ/ር ኢንጅነር መኮንን ጥበቡ ከየካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሸሙ፡፡

ዶ/ር ኢንጅነር መኮንን ጥበቡ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን በተለያዩ ኃላፊነቶች በመስራት ልምድ ያካበቱ ሲሆን በከተማው የመሠረተ ልማት ሥራዎች ላይ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።
👍3821
በ civil Engineering
በ COTM
- Site Engineer
- Office Engineering
-Project Manager
- inspector
- Forman
- driver (በሹፌር)
- የመሳሰሉት በ ቲክታክ tiktok የወጡ ስራዎችን ተመለክታችሁ አስተይዬት ስጡ ። እስኪ ቁም ነገር እንስራ።

https://www.tiktok.com/@conp251?_r=1&_t=ZS-94Xk8YfMZiq
👍188
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ደብዳቤ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሰረት በማድረግ ከመጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሬ መደረጉን ያስረዳል።

በደብዳቤው በተገለጸው መሰረት በሊትር፦
- ነጭ ናፍጣ 139.84 ብር
-​ ቤንዚን 132.18 ብር
-​ ኬሮሲን 146.14 ብር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ 137.03 ብር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 133.45 ብር
-​ የአውሮፕላን ነዳጅ 145.23 ብር ሆኗል።

በዚህም ነጭ ናፍጣ ላይ የ10 ብር፣ ኬሮሲን ላይ የ7 ብር፣ ቤንዚን ላይ የ3 ብር፣ በመጋቢት ወር በሊትር ጭማሪ የተደረገ ሲሆን፣ በየካቲት 2018 ዓ/ም ቤንዚን 129.12 ብር፣ ነጭ ናፍጣ 129.12 ብር፣ ኬሮሲን 129.12 ብር ይሸጡ ነበር።
#fuel
20👍13😁5
በአዲስ አበባ ሕንፃ አስገንቢዎች የሠራተኞችን ደኅንነት የሚቆጣጠር ባለሙያ እንዲመድቡ ሊደረግ ነው
- ሪፖርተር -

በአዲስ አበባ ከተማ ሕንፃ የሚያስገነቡ የሠራተኞችን ደኅንነትን የሚቆጣጠር ባለሙያ እንዲመድቡ እንደሚገደዱ፣ የከተማዋ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አበበ እሸቱ (ኢንጂነር) ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በሥራ ላይ የሚያጋጥም ሞትን ለመከላከልና የግንባታ ደኅንነት መሠረታዊ አስፈላጊነትን ለማረጋገጥ የሕንፃ አስገንቢዎች በዘርፉ የሠለጠነ የደኅንነት ባለሙያ እንዲቀጥሩ ይገደዳሉ፡፡ ይህን ለማድረግ የሚያስችል መመርያ እንደሚወጣ ገልጸው፣ እያንዳንዱ የግንባታ ቦታ በሕግ ተደግፎ የደኅንነት ባለሙያ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
31👍18👏7🤯1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የስሚንቶ ዋጋ : ምነው አለ ? 🤔🤔
The recent cement price surge is difficult to justify. While fuel prices have increased by only about 2.5%, a change that still caused noticeable supply challenges, the price of cement has risen dramatically by 90% to 110%. What makes this situation even more concerning is the absence of any significant demand pressure that would typically explain such a spike.

Now more than ever, government intervention is essential to stabilize the market and prevent this issue from escalating further, as it did two years ago.
#Cement
38👍9😁6🤔1🎉1
#fuel
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ደብዳቤ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሰረት በማድረግ ከመጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሬ መደረጉን ያስረዳል።
20👍7😱6🥰1
𝐀𝐟𝐫𝐢𝐜𝐚 𝐇𝐚𝐥𝐥 𝐖𝐢𝐧𝐬 𝐆𝐥𝐨𝐛𝐚𝐥 𝐀𝐜𝐜𝐥𝐚𝐢𝐦: 𝐅𝐫𝐨𝐦 𝐃𝐢𝐩𝐥𝐨𝐦𝐚𝐭𝐢𝐜 𝐋𝐚𝐧𝐝𝐦𝐚𝐫𝐤 𝐭𝐨 𝐌𝐨𝐝𝐞𝐫𝐧𝐢𝐬𝐭 𝐌𝐚𝐬𝐭𝐞𝐫𝐩𝐢𝐞𝐜𝐞

In the heart of #AddisAbaba stands a building that has witnessed some of the most consequential political moments in modern African history. More than six decades after its inauguration, #AfricaHall has received global recognition for both its architectural significance and the meticulous restoration that has brought it back to life.

The project was recently awarded the #WorldMonumentsFund / #Knoll Modernism Prize, a biennial award recognizing outstanding efforts to preserve modernist architecture around the world.

For 2026, the prize specifically honors projects that have restored or renovated modernist buildings within the past decade, especially those that overcame significant threats including deterioration, obsolescence, or inappropriate alterations while also improving the site’s environmental and sustainability and benefiting the local community.
Via Reporter
20👍8😁1😱1
የኢትዮጵያ የህንጻ አዋጅ 1356.pdf
1.4 MB
ክፍል አንድ፡ ስለ አዲሱ የሕንፃ አዋጅ ቁጥር 1356/2017 ማወቅ ያለብዎት ወሳኝ ነጥቦች!
*
ማንኛ
ውንም ግንባታ ከመጀመርዎ ወይም የጥገና ሥራ ከማከናወንዎ በፊት የአዋጁን ይዘት መረዳት ከሕግ ተጠያቂነት ከመታደጉም በላይ፣ ንብረትዎን ካልተገባ ብክነት ይጠብቃል። ለዛሬ የአዋጁን ተፈጻሚነት፣ የ"ህንፃ" ትርጉም እና የግንባታ ባለቤቶች ግዴታን እንደሚከተለው በዝርዝር አቅርበንላችኋል።

🏢 "ህንፃ" የሚለው ቃል ሰፊ ትርጉም የተሰጠው ሲሆን የሚከተሉትን ግንባታዎች ያጠቃልላል፦
• ማንኛውም ለመኖሪያ፣ ለንግድ፣ ለኢንዱስትሪ ወይም ለሌላ አገልግሎት ታስቦ ከምድር በላይ ወይም በከርሰ-ምድር (Basement) የተገነባ ቋሚ ወይም ጊዜያዊ ግንባታ፤
• እንደ አጥር፣ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮች፣ የውሃና መብራት ዝርጋታዎች ያሉ ተያያዥ ሥራዎች፤
• በህንፃው ግቢ ውስጥ የሚሰሩ መንገዶች እና ለህንፃው አገልግሎት እንዲውሉ ተለይተው የተሰሩ ማናቸውም መሰረተ-ልማቶች።
📍 የአዋጁ ተፈጻሚነት ወሰን (አንቀጽ 3)
አዋጁ በማንና የት ላይ ተፈጻሚ እንደሚሆን በአንቀጽ 3 ላይ በዝርዝር ተደንግጓል፦
• በከተሞች ውስጥ፦ 10,000 (አሥር ሺህ) እና ከዚያ በላይ ነዋሪዎች ባሏቸው ከተሞች በሚከናወኑ ግንባታዎች ሁሉ።
• ከከተማ ወሰን ውጭ፦ ለሕዝብ አገልግሎት የሚውሉ ሕንፃዎች (ትምህርት ቤት፣ ሆስፒታል ወዘተ)፣ የኢንዱስትሪ ወይም የዘመናዊ እርሻ ተቋማት እና የሪል ስቴት ግንባታዎች።
• ለነባር ሕንፃዎች፦ አዋጁ ከመውጣቱ በፊት የተገነቡ ሕንፃዎች ቢሆኑም፤ ለአካል ጉዳተኞች ተደራሽ ለማድረግ በሚደረግ ማሻሻያ እንዲሁም ለሕዝብ ደህንነትና ጤንነት አስጊ የሆኑ ሕንፃዎችን ለማስተካከል ወይም ለማፍረስ አዋጁ ተፈጻሚ ይሆናል።
@ConstructionProxy
45😁1
አዲስ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ጭማሪ ተደረገ 🛢️📈

በነዳጅ ዋጋ ላይ የ25 ብር ጭማሪ ተደረገ።

አዲስ አበባ | ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዛሬ ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ስራ ላይ የሚውል አዲስ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ማስተካከያ ማድረጉን አስታውቋል 📢📅

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በወጣው ይፋዊ መግለጫ መሠረት፣ የዋጋ ማስተካከያው የተደረገው የዓለም የነዳጅ ዋጋ መነሻ በማድረግና በሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀደም ብሎ በተላለፈው የዋጋ ግንባታ ለፈጻሸም ውሳኔ መሠረት መሆኑ ተገልጿል 🌍📊

በአዲሱ የዋጋ ማስተካከያ መሠረት አዲስ አበባ ከተማ የሚሸጡ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በሊትር፦🛒💰
1. ቤንዚን፦ 167.50 ብር
2. ኬሮሲን፦ 320.66 ብር
3. ነጭ ናፍጣ ፦ 180.46 ብር
4. ቀለል ያለ ጥቁር ናፍጣ ፦ 170.62 ብር
5. ከባድ ጥቁር ናፍጣ ፦ 167.37 ብር
6. የአውሮፕላን ነዳጅ፦ 319.76 ብር

መንግስት ይህ የዋጋ ማስተካከያ ከዛሬ ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሱቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን የወሰነ ሲሆን፣ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላትም መላክዋል 🚗

©️የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር

#fuel
20😭10😁2