Construction Proxy
19.2K subscribers
525 photos
17 videos
74 files
282 links
#1 construction portal to get:
construction news
construction market
construction materials price
engineering estimates
Sub contract
https://constructionproxy.com
Address any comment to admin👨‍💼 @ConproxyBot
Download Telegram
ማስታወቂያ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በ7ኛ ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ በ7 ክፍለ ከተሞች የሚገኙና ለተለያዩ አገልግሎቶች የተዘጋጁ የልማት ቦታዎችን በጨረታ አወዳድሮ በሊዝ ለማስተላለፍ ጥቅምት 01 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ልሳን ጋዜጣ በማውጣት ከህዳር 01 ቀን 2018ዓ.ም እስከ ህዳር 05 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ በይፋ ተከፍቶ አሸናፊዎች መለየታቸው ይታወሳል። ይህን ተከትሎ አሸናፊዎች በተቋማችን በመቅረብ የሊዝ ዉል እንድትፈጽሙ ህዳር 20 ቀን 2018ዓ.ም በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ጥሪ ባስተላለፍነው መሰረት በሊዝ ደንብ ቁጥር 162/2016 በተቀመጠው የአስር ቀን ገደብ ውስጥ በርካታ የሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ቢሮ ቀርበው የሊዝ ዉል ፈጽመዋል፡፡

ይሁን እንጂ ስማችሁ ከዚህ በታች የተገለጸ የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች በደንቡ መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ቀርባችሁ ውል አልፈፀማችሁም።

በመሆኑም የሊዝ ደንብ ቁጥር 162/2016 አንቀጽ 25 ንኡስ አንቀፅ 4 በግዜ ገደብ ዉል ያልፈፀሙ አንደኛ የወጡ አሸናፊ ተጫራቾች በሶስት ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ቀርበው ውል እንዲፈጽሙ የማስጠንቀቂያ ጊዜ እንዲሰጣቸው በሚደነግገው መሰረት ከ06/04/2018ዓ.ም እስከ 08/04/2018 ባሉት 3/ሶስት/ ተከታታይ የስራ ቀናት ቀርባችሁ የሊዝ ዉል እንድትፈጽሙ እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ቢቀር በሊዝ ደንብ ቁጥር 162/2016 አንቀጽ 25 ንኡስ አንቀፅ 5 መሰረት አሸናፊነታችሁ ተሰርዞ ያስያዛችሁት የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ለመንግስት ገቢ በማድረግ ሁለተኛ ለወጡ ተጫራቾች እድሉ የሚሰጥ መሆኑን እናሳዉቃለን፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ

ታህሳስ 04/2018ዓ.ም
31👍13🤔2
ማስታወቂያ

ለማህበር ቤት ተጠባባቂ ተመዝጋቢዎች
13👍13🥰2
7030(1).pdf
7.1 MB
List of applicants
👍219👏1
#ነዳጅ

በጥር ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር ከታሕሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በታሕሳስ ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን አሳውቋል።

አሁን ላይ ያለው የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ስንት ነው ?

- ቤንዚን 129.12 ብር በሊትር
- ነጭ ናፍጣ 129.12 ብር በሊትር
- ኬሮሲን 129.12 ብር በሊትር

የሌሎች ምርቶችም ዋጋ በታሕሳስ ወር በነበረበት ይቀጥላል።
👍16🙏4👏3👌3🔥2
648_የኮንስትራክሽን_ብቃት_ማረጋገጫና_ምዝገባ_መመሪያ.pdf
2.7 MB
የ ኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያ
- ኮንትራክተር ከ ደረጃ 1 እስከ 10
- የአማካሪ መሃንዲስ ፈቃድ
- ባለሙያ ሁሉም አይነት
👍4519
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ዛሬ ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ስራ አስጀመሩ።
👍3114
2018 2nd Q Construction Works (Only Direct Cost)(1).pdf
22.7 MB
የ2018 ዓ/ም 2ኛ ሩብ ዓመት የኮንስትራክሽን ስራዎች ቀጥተኛ ዋጋ ጥናት

2018E.C  2nd Quarter Construction Works (Only Direct Cost)t

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ
👍4124🔥3
1997 እና ለ2005 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች በሙሉ!
http://aahdab.et/saving
2👍2810🙏4
#ነዳጅ
#የካቲት

" ከአውሮፕላን ነዳጅ በቀር የሌሎች ነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል " - ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር

#ማስታወሻ ፦ አሁን ላይ ያለው የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ስንት ነው ?

- ቤንዚን 129.12 ብር በሊትር
- ነጭ ናፍጣ 129.12 ብር በሊትር
- ኬሮሲን 129.12 ብር በሊትር
👍18🙏4👏2🤔2👌1
It would be better if the new road section were planned strictly as an NMT (Non-Motorized Transport) route, with no motorized traffic allowed, i am just saying .
አዲሱ የመንገድ ክፍል ለNMT (ለእግረኞችና ለብስክሌት) ብቻ እንዲዘጋጅ እና የሞተር ተሽከርካሪ እንዳይፈቀድ ቢሆን ይሻላል ነበር።
21👍21😁5🔥3🤔3
ዜና ሹመት
ዶ/ር ኢንጅነር መኮንን ጥበቡ ከየካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሸሙ፡፡

ዶ/ር ኢንጅነር መኮንን ጥበቡ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን በተለያዩ ኃላፊነቶች በመስራት ልምድ ያካበቱ ሲሆን በከተማው የመሠረተ ልማት ሥራዎች ላይ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።
👍3820
በ civil Engineering
በ COTM
- Site Engineer
- Office Engineering
-Project Manager
- inspector
- Forman
- driver (በሹፌር)
- የመሳሰሉት በ ቲክታክ tiktok የወጡ ስራዎችን ተመለክታችሁ አስተይዬት ስጡ ። እስኪ ቁም ነገር እንስራ።

https://www.tiktok.com/@conp251?_r=1&_t=ZS-94Xk8YfMZiq
👍168
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ደብዳቤ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሰረት በማድረግ ከመጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሬ መደረጉን ያስረዳል።

በደብዳቤው በተገለጸው መሰረት በሊትር፦
- ነጭ ናፍጣ 139.84 ብር
-​ ቤንዚን 132.18 ብር
-​ ኬሮሲን 146.14 ብር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ 137.03 ብር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 133.45 ብር
-​ የአውሮፕላን ነዳጅ 145.23 ብር ሆኗል።

በዚህም ነጭ ናፍጣ ላይ የ10 ብር፣ ኬሮሲን ላይ የ7 ብር፣ ቤንዚን ላይ የ3 ብር፣ በመጋቢት ወር በሊትር ጭማሪ የተደረገ ሲሆን፣ በየካቲት 2018 ዓ/ም ቤንዚን 129.12 ብር፣ ነጭ ናፍጣ 129.12 ብር፣ ኬሮሲን 129.12 ብር ይሸጡ ነበር።
#fuel
15👍12😁5
በአዲስ አበባ ሕንፃ አስገንቢዎች የሠራተኞችን ደኅንነት የሚቆጣጠር ባለሙያ እንዲመድቡ ሊደረግ ነው
- ሪፖርተር -

በአዲስ አበባ ከተማ ሕንፃ የሚያስገነቡ የሠራተኞችን ደኅንነትን የሚቆጣጠር ባለሙያ እንዲመድቡ እንደሚገደዱ፣ የከተማዋ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አበበ እሸቱ (ኢንጂነር) ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በሥራ ላይ የሚያጋጥም ሞትን ለመከላከልና የግንባታ ደኅንነት መሠረታዊ አስፈላጊነትን ለማረጋገጥ የሕንፃ አስገንቢዎች በዘርፉ የሠለጠነ የደኅንነት ባለሙያ እንዲቀጥሩ ይገደዳሉ፡፡ ይህን ለማድረግ የሚያስችል መመርያ እንደሚወጣ ገልጸው፣ እያንዳንዱ የግንባታ ቦታ በሕግ ተደግፎ የደኅንነት ባለሙያ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
26👍18👏7🤯1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የስሚንቶ ዋጋ : ምነው አለ ? 🤔🤔
The recent cement price surge is difficult to justify. While fuel prices have increased by only about 2.5%, a change that still caused noticeable supply challenges, the price of cement has risen dramatically by 90% to 110%. What makes this situation even more concerning is the absence of any significant demand pressure that would typically explain such a spike.

Now more than ever, government intervention is essential to stabilize the market and prevent this issue from escalating further, as it did two years ago.
#Cement
33👍8😁6
#fuel
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ደብዳቤ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሰረት በማድረግ ከመጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሬ መደረጉን ያስረዳል።
13👍5😱5