ለ ነባርና አዲስ የኮንስትራክሽን (BC/GC) ፍቃድ ተመዝጋቢዎች
ከዚህ በላይ በሰፈረው አዲስ የተርን ኦቨር ባለሙያና የኮንስትራክሽን መሳርያዎች መስፈርት መሰረት በማሟላት ፈቃድ ማግኘት ይችላሉ::
ለእድሳትም ሆነ አዲስ ብቃት ማረጋገጫ ለማውጣት ሲመጡ ለሚፈልጉት ደረጃ ማንኛውም ማስረጃዎች ኦሪጅናላቸውን ከ2 ኮፒ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባችሁ
የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ የፕራክቲሲንግ ፕሮፌሽናል የምስክር ወረቀት/ላይሰንስ ሊኖረው ይገባል ካልሆነ ከተቆጣጣሪ ማሃንዲሱ ጋር በድርጅቱ ስራ አስኪያጅነት የተዋዋለበትን ማስረጃ ማቅረብ አለበት
ለስራ ዘመኑ ዓመታዊ ተርን ኦቨር የሚያሳይ ማስረጃ፤ የተሸከርካሪ ምርመራ (ዕድሳት)የተደረገለት መኪና ሊብሬ፤ ለስራ ዘመኑ የሚያገለግል (የታደሰ) የባለሙያ ፕሮፌሽናል ላይሰንስ፤ ህጋዊ የስራ ዉል፤ ቲን ነምበር(የግብር ከፋይ ምዝገባ ምስክር ወረቀት)፤ የባለሙያው የትምህርት ዶክመንት፤ ባለሙያው ቀድሞ ሲሰራበት ከነበረው ድርጅት ስድስት ወር ያላለፈው የስራ መልቀቂያ፤ የቀበሌ መታወቂያ…) እና ሌሎችም ሊኖሩ ይችላሉ
Via ሱራፌል አሸናፊ 👈👈
❤12
🤚ሰላም ቤተስቦች እንዴት ናቹ ተጨማሪ ሃሳቦች ለአማካሪዎች እና ለተቋራጮች ምዝገባ:-
በኮንስትራክሽን ቢሮ የምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት ለማግኘት ከሚመጡ ተገልጋዮች የሚጠበቁ ቅድመ ሁኔታዎች ከዚህ ፅሁፍ ብ ፎቶ አያይዘንላቹዋል::
በኮንስትራክሽን ቢሮ የምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት ለማግኘት ከሚመጡ ተገልጋዮች የሚጠበቁ ቅድመ ሁኔታዎች ከዚህ ፅሁፍ ብ ፎቶ አያይዘንላቹዋል::
1❤27👏4😁2👍1
Forwarded from Construction Resources
2017 1st QUARTER CONSTRUCTION WORKS ONLY DIRECT COST.pdf
22.3 MB
❇️ የ2017 የአንደኛ ሩብ ዓመት የኮንስትራክሽን ስራዎች ቀጥተኛ ዋጋ ጥናት ይህን ይመስላል።
👏20👎2❤1👍1
ማህበራት መረጃ 2017 Latest.pdf
234.5 KB
**ማስታወቂያ ለማሕበራት*
❇️ ከ 2013 ዓ.ም ጀምሮ በማህበር የተደራጅታችሁና በዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ ውስጥ በተለያየ የልማት ሥራዎች ላይ ስትሳተፉ የነበራችሁ ማህበራት ስማችሁ በቢሮው ይፋዊ የማሕበራዊ ሚዲያ ገፆች የተለቀቀ ሲሆን በዝርዝር ውስጥ የሌላችሁ ማህበራት 8 ኛ ፎቅ ምህንድስና ግዥ ዳይርክቶሬት ተገኝታችሁ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 2 ቀናት ውስጥ ሪፖርት እንዲታደርጉ ያሳስባል ፡፡
የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ
ጥቅምት 12/1017
❇️ ከ 2013 ዓ.ም ጀምሮ በማህበር የተደራጅታችሁና በዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ ውስጥ በተለያየ የልማት ሥራዎች ላይ ስትሳተፉ የነበራችሁ ማህበራት ስማችሁ በቢሮው ይፋዊ የማሕበራዊ ሚዲያ ገፆች የተለቀቀ ሲሆን በዝርዝር ውስጥ የሌላችሁ ማህበራት 8 ኛ ፎቅ ምህንድስና ግዥ ዳይርክቶሬት ተገኝታችሁ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 2 ቀናት ውስጥ ሪፖርት እንዲታደርጉ ያሳስባል ፡፡
የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ
ጥቅምት 12/1017
👏12❤1
አዲሱ_የቤት_ሽያጭ_ዋጋ_ተመን_አሰራር_እና_ታክስ_አገልግሎት_ክፍያ_ማንዋል_ቁጥር_01_2016_watermark.pdf
1017.2 KB
በአዲስ አበባ ከተማ #ለአፓርትመንት_ቤቶች እና #ለጋራ_መኖሪያ_ቤቶች ወይም ኮንዶሚኒየም ቤቶች አማካኝ የሽያጭ ዋጋ ተመን በ34 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል።
በተሻሻለው የቤት ሽያጭ ዋጋ ተመን መሰረት ከኮንደሚንየም እና አፓርትመንት ውጪ ለሆኑ ግንባታዎች፦
➡️ የግንባታ ነጠላ ዋጋ በጭቃ የተሰራ ቪላ ቤት (G+0) ነጠላ ዋጋ በካሬ 15,000 ብር፣
➡️ በብሎኬት የተሰራ የቪላ ቤት (G+0) ነጠላ ዋጋ በካሬ 20,000 ብር፣
➡️ የህንጻ ወለላቸው ከG+1 እስከ G+5 25,000 ብር እና፣
➡️ G+6 እና በላይ የሆኑ ቤት ወይም ህንጻ ነጠላ ዋጋ በካሬ 30,000 ተደርጓል፡፡
የቦታው መገኛ ዋጋ ('location value') ለከተማው የቦታ ደረጃ የጸደቀው ወቅታዊ አማካይ የሊዝ ጨረታ ዋጋ እንዲሆን መደረጉም ተገልጿል።
የቤት ስም ንብረት ዝውውር ክፍያ ማለትም አሹራ 4 በመቶ እና የቴምብር ቀረጥ 2 በመቶ ከጠቅላላ የቤቱ ሽያጭ ዋጋ ተሰልቶ ከመጋቢት17 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እንዲከፈልም ቢሮ አዟል።
ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገው የቤት ሽያጭ ዋጋ ተመን መሻሩንም ቢሮ ጠቅሷል።
በፍርድ ቤት እና በባንክ ሃራጅ ሽያጭ የስም ንብረት ዝውውር የሚጠየቅባቸው ይዞታዎችን በተመለከተ ይዞታ አገልግሎትና መብት ፈጠራ ደንብ ላይ በተቀመጠው አግባብ ተፈጻሚ ይሆናል ተብሏል።
ይህ ማሻሻያ መምሪያ ከመውጣቱ በፊት የስም ንብረት ዝውውር አገልግሎት ጠይቀው በሂደት ላይ ሆኖ ክፍያ የፈጸሙ ተጋልጋዮች በቀድሞ አሰራር በከፈሉት ክፍያ መሰረት ይስተናገዳሉ ተብሏል።
ግንባታቸው ያልተጠናቀቁ ህንፃዎች የትመና ስራ የሚሰራላቸው ግንባታው በደረሰበት ወይም አሁን ላይ ባለበት ግንባታ ደረጃ እንደሚሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ያሳወቃል።
በተሻሻለው የቤት ሽያጭ ዋጋ ተመን መሰረት ከኮንደሚንየም እና አፓርትመንት ውጪ ለሆኑ ግንባታዎች፦
➡️ የግንባታ ነጠላ ዋጋ በጭቃ የተሰራ ቪላ ቤት (G+0) ነጠላ ዋጋ በካሬ 15,000 ብር፣
➡️ በብሎኬት የተሰራ የቪላ ቤት (G+0) ነጠላ ዋጋ በካሬ 20,000 ብር፣
➡️ የህንጻ ወለላቸው ከG+1 እስከ G+5 25,000 ብር እና፣
➡️ G+6 እና በላይ የሆኑ ቤት ወይም ህንጻ ነጠላ ዋጋ በካሬ 30,000 ተደርጓል፡፡
የቦታው መገኛ ዋጋ ('location value') ለከተማው የቦታ ደረጃ የጸደቀው ወቅታዊ አማካይ የሊዝ ጨረታ ዋጋ እንዲሆን መደረጉም ተገልጿል።
የቤት ስም ንብረት ዝውውር ክፍያ ማለትም አሹራ 4 በመቶ እና የቴምብር ቀረጥ 2 በመቶ ከጠቅላላ የቤቱ ሽያጭ ዋጋ ተሰልቶ ከመጋቢት17 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እንዲከፈልም ቢሮ አዟል።
ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገው የቤት ሽያጭ ዋጋ ተመን መሻሩንም ቢሮ ጠቅሷል።
በፍርድ ቤት እና በባንክ ሃራጅ ሽያጭ የስም ንብረት ዝውውር የሚጠየቅባቸው ይዞታዎችን በተመለከተ ይዞታ አገልግሎትና መብት ፈጠራ ደንብ ላይ በተቀመጠው አግባብ ተፈጻሚ ይሆናል ተብሏል።
ይህ ማሻሻያ መምሪያ ከመውጣቱ በፊት የስም ንብረት ዝውውር አገልግሎት ጠይቀው በሂደት ላይ ሆኖ ክፍያ የፈጸሙ ተጋልጋዮች በቀድሞ አሰራር በከፈሉት ክፍያ መሰረት ይስተናገዳሉ ተብሏል።
ግንባታቸው ያልተጠናቀቁ ህንፃዎች የትመና ስራ የሚሰራላቸው ግንባታው በደረሰበት ወይም አሁን ላይ ባለበት ግንባታ ደረጃ እንደሚሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ያሳወቃል።
❤16🔥1😁1
#ሲሚንቶ
" ከዛሬ ጀምሮ በሚኒስትር መ/ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ቀርቷል " - ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።
በዚህም ወቅት " ከዚህ ቀደም በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ከዛሬ ጀምሮ ቀርቷል " ብለዋል።
አምራቾች በራሳቸዉ ኃላፊነት በሚመርጧቸዉ አከፋፋዮችና ቸርቻሪዎች በኩል ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡
የሲሚንቶ ገበያዉን ለማረጋጋት ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል ይደረጋል ያሉ ሲሆን የአፈጻጸም ሪፖርት ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በማያቀርቡ በማናቸዉም የሲሚንቶ አምራች ላይ " የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ሚኒስትሩ " አዲሱን ዉሳኔና አቅጣጫ ተከትሎ በግብይት ሰንሰለቱ የደላላ ጣልቃ ገብነት የከሰመ፣ ለመንግስት ፕሮጀክቶችና ለተጠቃሚዉ ህብረተሰብ አስተማማኝ የሲሚንቶ አቅርቦት የተረጋገጠ፣ አምራቾችም ተገቢዉን ትርፍ እያገኙ የከምፓኒዎቻቸዉን ዘላቂ ዕድገት የሚያስቀጥሉበት እንዲሆን " ብለዋል።
የግብይት ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ ከካሽ ክፍያ ነጻ ሆኖ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እንዲፈጸም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በውይይት መድረኩ ወቅት አምራቾች የምርት አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ተብሏል።
ሲሚንቶ አምራቾች አዲሱን ውሳኔ በማክበር እንደሚተገብሩ ተናግረው ነገር ግን የማምረቻ ግብዓት ፣ የኃይል አቅርቦትና ተያያዥ ችግሮች እንዲፈቱላቸዉ ጠይቀዋል፡፡
" ከዛሬ ጀምሮ በሚኒስትር መ/ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ቀርቷል " - ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።
በዚህም ወቅት " ከዚህ ቀደም በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ከዛሬ ጀምሮ ቀርቷል " ብለዋል።
አምራቾች በራሳቸዉ ኃላፊነት በሚመርጧቸዉ አከፋፋዮችና ቸርቻሪዎች በኩል ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡
የሲሚንቶ ገበያዉን ለማረጋጋት ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል ይደረጋል ያሉ ሲሆን የአፈጻጸም ሪፖርት ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በማያቀርቡ በማናቸዉም የሲሚንቶ አምራች ላይ " የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ሚኒስትሩ " አዲሱን ዉሳኔና አቅጣጫ ተከትሎ በግብይት ሰንሰለቱ የደላላ ጣልቃ ገብነት የከሰመ፣ ለመንግስት ፕሮጀክቶችና ለተጠቃሚዉ ህብረተሰብ አስተማማኝ የሲሚንቶ አቅርቦት የተረጋገጠ፣ አምራቾችም ተገቢዉን ትርፍ እያገኙ የከምፓኒዎቻቸዉን ዘላቂ ዕድገት የሚያስቀጥሉበት እንዲሆን " ብለዋል።
የግብይት ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ ከካሽ ክፍያ ነጻ ሆኖ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እንዲፈጸም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በውይይት መድረኩ ወቅት አምራቾች የምርት አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ተብሏል።
ሲሚንቶ አምራቾች አዲሱን ውሳኔ በማክበር እንደሚተገብሩ ተናግረው ነገር ግን የማምረቻ ግብዓት ፣ የኃይል አቅርቦትና ተያያዥ ችግሮች እንዲፈቱላቸዉ ጠይቀዋል፡፡
❤11👎2👍1
የጋራ መኖሪያ ቤቶች ቀሪ የማጠናቀቂያ ስራ በሚፈለገው ፍጥነት እየተሰራ መሆኑ ምልከታ ተደረገ።
የጋራ መኖሪያ ቤቶች ቀሪ የማጠናቀቂያ ስራ በሚፈለገው ፍጥነት እየተሰራ መሆኑ እና ነዋሪው ወደ ቤቱ እንዲገባ ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ ስለመሆኑ ዛሬ ምልከታ ተደረገ።
በምልከታው በ40/60 እና በ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚገኙበት በአራብሳ ሳይት ሶስት አምስት እና ስድስት ፤ በበሻሌ እና በአያት 2 ጨፌ ሳይት ያሉበትን የስራ እንቅስቃሴ ለማየት ተችሏል።
አቶ አብረሃም ታደሰ የአዲስ አበባ ብልፅግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ እና የከተማው አስተባባሪ ኮሚቴ አባል በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት ቀንና ምሽት 7/24 እየሰሩ ያሉ ተቋራጮች ያሉበት አፈፃፀም ጥሩ ለውጥ ያለው መሆኑን በምልከታው ማየታቸውን ገልፀው ነገር ግን ሁሉም ጋር ተመሳሳይ ፍጥነት አለመኖሩን ተናግረዋል።
የመሰረተ ልማት አቅራቢ ተቋማት ማለትም የቤቶች ፣ የመንገዶች የውሀ እና የመብራት ስራ በየእለቱ እየቀረበ እንዲገመገም እና ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮች በየቀኑ እንዲቀርቡ ኃላፊው አሳስበው በየቀኑ ለውጥ ያለው ስራ ለማየት የስራ ባህሉም 7/24 ሆኖ ይቀጥል ብለዋል።
በምልከታው የታዩ የበር ፣ የመስኮት፣ የሳኒተሪ ፣ የፍሳሽ ፣ የመንገድ እና ሌሎችም የሚጎሉ ስራዎች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ኃላፊው አሳስበዋል።
በጉብኝቱ አቶ አብረሀም ታደሰን ጨምሮ የቢሮው እና የኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ከመንገድ ፣ ከውሀ ፣ ከመብራት የመጡ የመሰረተ ልማት ቅንጅት ተቋማት ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል ።
የጋራ መኖሪያ ቤቶች ቀሪ የማጠናቀቂያ ስራ በሚፈለገው ፍጥነት እየተሰራ መሆኑ እና ነዋሪው ወደ ቤቱ እንዲገባ ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ ስለመሆኑ ዛሬ ምልከታ ተደረገ።
በምልከታው በ40/60 እና በ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚገኙበት በአራብሳ ሳይት ሶስት አምስት እና ስድስት ፤ በበሻሌ እና በአያት 2 ጨፌ ሳይት ያሉበትን የስራ እንቅስቃሴ ለማየት ተችሏል።
አቶ አብረሃም ታደሰ የአዲስ አበባ ብልፅግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ እና የከተማው አስተባባሪ ኮሚቴ አባል በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት ቀንና ምሽት 7/24 እየሰሩ ያሉ ተቋራጮች ያሉበት አፈፃፀም ጥሩ ለውጥ ያለው መሆኑን በምልከታው ማየታቸውን ገልፀው ነገር ግን ሁሉም ጋር ተመሳሳይ ፍጥነት አለመኖሩን ተናግረዋል።
የመሰረተ ልማት አቅራቢ ተቋማት ማለትም የቤቶች ፣ የመንገዶች የውሀ እና የመብራት ስራ በየእለቱ እየቀረበ እንዲገመገም እና ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮች በየቀኑ እንዲቀርቡ ኃላፊው አሳስበው በየቀኑ ለውጥ ያለው ስራ ለማየት የስራ ባህሉም 7/24 ሆኖ ይቀጥል ብለዋል።
በምልከታው የታዩ የበር ፣ የመስኮት፣ የሳኒተሪ ፣ የፍሳሽ ፣ የመንገድ እና ሌሎችም የሚጎሉ ስራዎች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ኃላፊው አሳስበዋል።
በጉብኝቱ አቶ አብረሀም ታደሰን ጨምሮ የቢሮው እና የኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ከመንገድ ፣ ከውሀ ፣ ከመብራት የመጡ የመሰረተ ልማት ቅንጅት ተቋማት ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል ።
❤5👏3👍1