Condominuim Market in Addis Ababa
3.63K subscribers
2.34K photos
60 videos
10 files
1K links
በዚህ የቴሌግራም Chanel
ከ10,000 ተከታይ በላይ ባለው facebook page
በቀን እስከ 500 ሰው ጎብኚ ብለው condoaddis.etsecurities.com
በማስታወቂያ ክፍያ ቤትዎን እና መኪናዎን መሸጥ ፣ ማከራየት ይችላሉ ኮሚሽን መክፈል ለማይፈልጉ
buy ads here https://telega.io/c/condoaddis
0913587955
መረጃ ለመላክና ለጥያቄ
@antget1
Download Telegram
👍3🔥2
እንኳን አደረሳችሁ
ውድ የ @condoaddis ቤተሰቦች
👍21
ለተጠባባቂ የማህበር ቤት ተመዝጋቢዎች በሙሉ

የአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ በ20/80 እና በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም ተመዝጋቢ ሆነው የቤት ተጠቃሚ ለመሆን በመጠባበቅ ላይ የሚገኙትን በ70/30 በጋራ ህንፃ መኖሪያ ቤት ህ/ሥራ ማህበር በፈቃደኝነት አደራጅቶ የቤት ተጠቃሚ ለማድረግ በመመሪያ ቁጥር 1/2013 መሠረት ፈላጊዎችን መመዝገባችን ይታወቃል፡፡

በዚሁ መሠረት ቀደም ሲል ተመዝግባችሁ ለተጠባባቂነት እጣ በወጣላችሁ ቅደም ተከተል መሠረት ስማችሁ በዚህ ማስታወቂያ ላይ የወጣ ሲሆን ተመዝጋቢዎች ከ10/1/2017 እስከ 17/01/2017 ዓ.ም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ቅድመ ሁኔታዎች በሟሟላት ባሉት 7 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ብቻ በቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የጋራ መኖሪያ እና ቤት ህብረት ስራ ማህበራት ዳይሬክቶሬት ዘውትር በስራ ሰአት 6ኛ ፎቅ በመቅረብ ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡ ተመዝጋቢዎች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መረጃዎች ለምዝገባ በሚመጡበት ጊዜ አሟልተው እንዲመጡ እናሳስባለን፡፡

Read more
2👍1
በድጋሚ የወጣ ማስታወቂያ

ቀደም ሲል  በወጣ ማስታወቂያ በማህበር ቤት ተደልድላችሁ በ16/01/17 ዓ.ም በቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ 11ኛ ፎቅ በመገኘት ኦረንቴሽን እንድትወስዱ እና ወደ ህብረት ስራ ኮሚሽን እንድትሄዱ መባሉ ይታወቃል።

ነገር  ግን የኦረንቴሽኑ ቀን ወደ ቅዳሜ በ18/01/17  ከጠዋቱ 2:30 መቀየሩን እናሳውቃለን።

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር  ቢሮ
Condoaddis.com
👍1
የቻነላችን ሜምበር በመሆን በአዲስ አበባ ከተማ በርካሽ የሽያጭ ዋጋ የሚገኙ ቤቶችን ያግኙ

የመጀመሪያው ይኸው👇👇 https://youtube.com/shorts/kcy0QUDasJ0?si=z0KX6SERtVttLgYa
👍4
በጣም ቅናሽ ኮንዶሚኒየም
አድራሻ ቱሉ ዲምቱ በሸገር
#ስፋት 29 ካሬ ሜትር
1ኛ ወለል ላይ
ፊኒሺንግ የተሰራ
ዲጂታል ካርታ የያዘ
ዋጋ 1.7 ሚሊዮን ብር

ስልኩን ያግኙ👇👇
Https://www.condoaddis.com/28092024-1
1
የቤት ዋጋ በዓመታት
House price in years

https://youtube.com/shorts/1uhcNKiphPE?si=6xc_ZLQhnesPZR0Z
🤔2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤቶቹ ከሰሞኑ ይህንን አቤቱታ አሰምተው ነበር:-
<< እነዚህ በምስሉ የሚታዩትና ቁጥራቸው ከ7,000 በላይ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ናቸው።መኖሪያ ቤቶቹ ቦሌ አያት 2 ይገኛሉ ለተጠቃሚዎች ከተላለፉ 6 ዓመታትን አስቆጥረዋል
ነገር ግን አንድም መሠረተ ልማት ባለመሟላቱ ሁሉም ኮሚቴ አቋቁሞ እስከ አዲስ አበባ ከንቲባ ጽ/ቤት ድረስ ብዙ ጥረት ቢደረግም ሰሚ ጠፍቶ ሰው ቤት እያለው በኪራይ ቤት ለመኖር ተገዷል።ህንፃዎቹ እስከ 15 ፎቅ ከፍታ አላቸው።
ቤቶቹ በሸያጭ የተላለፉልን የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን መሠረታዊ የሚባሉ ጉዳዮችን ሳይሰራ በመሆኑ ወደ ቤታችን መግባት አልቻልንም።
1.የውስጥ ለውስጥ መንገድ አልተሠራም።በዚህም እድሳት እንኳን ለመስራት አስቸግሮናል።
2. የውሃና መብራት ቆጣሪ አልተገጠመም

3. የፍሳሽ ማስወገጃ አልተሰራለትም።በዚህ ምክንያት ለፓርኪንግ የተሰራው 2 እና 3 ቤዝመንት በፍስሽ ተሞልቶ ይገኛል።

4. ከግማሽ በሚልቁት ቤቶች  ላይ መሠራት የነበረበት የኤሌክትሪክ ዝርጋታ እና የኢንተርኔት ኬብል ዝርጋታ አልተሠሩም።

5.ከ1800 በላይ ቤቶቾ በርና አልሙኒየም መስኮቶች አልተገጠሙም።
6. ህንፃዎቹ እስከ 15 ፎቅ ድረስ ከፍታ ስላላቸው ሊፍት የለም።
7. በግቢው ውስጥ የኢትዮ ቴሌኮምም ሆነ የሳፋሪ ኮም ኔትወርክ አይሰራም።ማንም ሄዶ ኮኔክሽኑንም ሆነ ድምፁን ማረጋገጥ ይችላል።በተጨማሪም በቤቶች ልማት ቤቱ ላይ መጠናቀቅ የነበረባቸው
  - መፀዳጃ ቤት(ሴራሚክና መቀመጫ)
  - ኪችን(ሴራሚክና ሲንክ) አልተሠሩም።
  -የጣራ ፍሳሽ ስራ አልተከናወነላቸውም>>ብለዋል።

ጨምረው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እስከ ጥቅምት 30/2017 እንድትገቡ የሚል ማስጠንቀቂያ መስጠቱ እንዳሳዘናቸውም ተናግረዋል።
የከተማውን ከንቲባ ጭምር ጠይቀው እንደነበር ይታወሳል።
👍31