ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ ደረቅ ቆሻሻ በመኪና ጭነው ያስገቡ ግለሰቦች 300,000 ብር ተቀጡ
ህዳር 11/2017 ዓ.ም
**ከአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ ደረቅ ቆሻሻን ወደ ከተማዋ በመኪና ጭነው በማስገባት ባልተፈቀደ ቦታ የጣሉ ግለሰቦች በገንዘብ መቅጣቱ አስታወቀ።
ግለሰቦቹ ከነ ተሽከርካሪአቸው በቁጥጥር ስር በማዋል በባለስልጣኑ በተሻሻለዉ የቅጣት ሰንጠረዥ 2 ደንብ ቁጥር 167/2016 ተራ ቁጥር 31.2 መሰረት እያንዳንዳቸው 100,000 /መቶ ሺህ/ ብር በድምሩ 300,000/ሦስት መቶ ሺህ/ ብር መቀጣታቸው የወረዳው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሃላፊ ሻለቃ ዋጋዬ አቶምሳ ገልፀዋል።
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማዋ ውብ፣ጽዱ እና ማራኪ ለማድረግ ቀን ከሊሊት እየሰራ ባለበት ሰዓት የአካባቢ ውበቱ ሆን ብለዉ የሚያበላሹ ግድ የለሽ ግለሠቦችን አስተማሪ ቅጣት እየቀጣ መሆኑ ባለስልጣኑ አስታውቋል።
ባለስልጣኑ የደንብ መተላለፉን የፈፀሙ ግለሰቦች ተጠያቂ እንዲሆኑ መረጃውን ለሰጡትና እገዛ ላደረጉ የከተማዉን ነዋሪዎች እያመሰገነ በቀጣይም ሁሉም የከተማው ነዋሪዎች ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው ።
ህዳር 11/2017 ዓ.ም
**ከአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ ደረቅ ቆሻሻን ወደ ከተማዋ በመኪና ጭነው በማስገባት ባልተፈቀደ ቦታ የጣሉ ግለሰቦች በገንዘብ መቅጣቱ አስታወቀ።
ግለሰቦቹ ከነ ተሽከርካሪአቸው በቁጥጥር ስር በማዋል በባለስልጣኑ በተሻሻለዉ የቅጣት ሰንጠረዥ 2 ደንብ ቁጥር 167/2016 ተራ ቁጥር 31.2 መሰረት እያንዳንዳቸው 100,000 /መቶ ሺህ/ ብር በድምሩ 300,000/ሦስት መቶ ሺህ/ ብር መቀጣታቸው የወረዳው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሃላፊ ሻለቃ ዋጋዬ አቶምሳ ገልፀዋል።
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማዋ ውብ፣ጽዱ እና ማራኪ ለማድረግ ቀን ከሊሊት እየሰራ ባለበት ሰዓት የአካባቢ ውበቱ ሆን ብለዉ የሚያበላሹ ግድ የለሽ ግለሠቦችን አስተማሪ ቅጣት እየቀጣ መሆኑ ባለስልጣኑ አስታውቋል።
ባለስልጣኑ የደንብ መተላለፉን የፈፀሙ ግለሰቦች ተጠያቂ እንዲሆኑ መረጃውን ለሰጡትና እገዛ ላደረጉ የከተማዉን ነዋሪዎች እያመሰገነ በቀጣይም ሁሉም የከተማው ነዋሪዎች ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው ።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በባለስልጣኑ በ15 ቀናት የተከናወኑ አበይት ሁነቶች በዜና
ባለስልጣኑ በመንገድ መሠረተ ልማት ጉዳት ጉዳት ባደረሱና ባበላሹ ግለሰቦችን ተጠያቂ አደረገ
ህዳር 14/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ራስ መኮነን ድልድይ አካባቢ በኦቪድ ኮነስትራክሽን ግንባታ የሚሰሩ ግለሰቦችን በመንገድና በአረንጓዴ መሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ባደረሱና ያበላሹ ግለሰቦችን በህግ ተጠያቂ አደረገ።
ባለስልጣኑ በአካባቢው በመንገድ መሠረተ ልማት ጉዳት ባደረሱና፣አረንጓዴ ቦታዎች በማበላሸትና በመርገጥ የተሠጣቸውን ቅጣት ባለመቀበል በአራዳ ክ/ከ ራስ ደስታ ፖሊስ ጣቢያ በፈፀሙት ጥፋት መሰረት በተሻሻለው የደንብ ቁጥር 167/16 መሠረት ክስ በመመስት ክትትል እያደረገ ይገኛል።
ባለስልጣኑ ክስ የመሠረተባቸው የድርጅቱ ሰራተኞ
1ኛ-አቶ ናሆም ብርሃነ ስላሴ አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት
2ኛ -አቶ ፍቅሩ ፅጌ ሰርቪስ አገልግሎት
3ኛ- አረጋይ በርሄ ፕሮጀክት ማናጀር ናቸው።
ባለስልጣኑ በከተማችን ውስጥ የሚገኙ በግንባታ ስራ ላይ የተሠማሩ ድርጅቶችና ሰራተኞች የከተማ አስተዳደሩ ያወጣቸውን ህግና ደንቦችና አሰራሮችን በመከተል በመንግስትና በህዝብ ሀብት የተገነቡ መሠረተ ልማቶችን በመጠበቅና እንዲሠሩ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
ባለስልጣኑ በደንብ ተላላፊዎች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ አሳውቋል።
ህዳር 14/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ራስ መኮነን ድልድይ አካባቢ በኦቪድ ኮነስትራክሽን ግንባታ የሚሰሩ ግለሰቦችን በመንገድና በአረንጓዴ መሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ባደረሱና ያበላሹ ግለሰቦችን በህግ ተጠያቂ አደረገ።
ባለስልጣኑ በአካባቢው በመንገድ መሠረተ ልማት ጉዳት ባደረሱና፣አረንጓዴ ቦታዎች በማበላሸትና በመርገጥ የተሠጣቸውን ቅጣት ባለመቀበል በአራዳ ክ/ከ ራስ ደስታ ፖሊስ ጣቢያ በፈፀሙት ጥፋት መሰረት በተሻሻለው የደንብ ቁጥር 167/16 መሠረት ክስ በመመስት ክትትል እያደረገ ይገኛል።
ባለስልጣኑ ክስ የመሠረተባቸው የድርጅቱ ሰራተኞ
1ኛ-አቶ ናሆም ብርሃነ ስላሴ አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት
2ኛ -አቶ ፍቅሩ ፅጌ ሰርቪስ አገልግሎት
3ኛ- አረጋይ በርሄ ፕሮጀክት ማናጀር ናቸው።
ባለስልጣኑ በከተማችን ውስጥ የሚገኙ በግንባታ ስራ ላይ የተሠማሩ ድርጅቶችና ሰራተኞች የከተማ አስተዳደሩ ያወጣቸውን ህግና ደንቦችና አሰራሮችን በመከተል በመንግስትና በህዝብ ሀብት የተገነቡ መሠረተ ልማቶችን በመጠበቅና እንዲሠሩ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
ባለስልጣኑ በደንብ ተላላፊዎች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ አሳውቋል።
ባለስልጣኑ በአገልግሎት አሰጣጥ እና ደንበኞች አያያዝ ላይ ስልጠና ሰጠ:
ህዳር 26/2017
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠና ጥናት ዳይሬክቶሬት ከፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በደንበኞች አገልግሎት አስጣጥ እና አያያዝ ዙሪያ ለማእከል እና ክፍለ ከተማ ሲቪል ሰራተኞች በባለስልጣኑ መሰብሰባያ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻ ንግግራቸው ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከከተማ አስተዳደሩ የተጣለበት ህዝብን በቅንነት በታማኝነት አገልግሎትን በጥራት የመስጠት ኃላፊነትን በመወጣት ላይ የሚገኝ ተቋም እንደመሆኑ እንደነዚ አይነት ስልጠናዎች መዘጋጀታቸው ይበል የሚያሰኝ ተግባር ነው ብለዋል::
በመ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የቅድመ መከላከል እና ስልጠና ዘርፍ ኃላፊ ኮ/ር አህመድ መሀመድ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን ጤናማ ለማድረግ ስልጠናዎች መሰጠታቸው ትልቁን ድርሻ እንዳለው ገልፀዋል::
ስልጠናው ከትምህርት ተቋማት ከምናገኘው እውቀት ባሻገር እንደነዚህ አይነት ስልጠናዎች መዘጋጀታቸው ስራችንን ብቁ እና ተወዳዳሪ ከማድረግ አኳያ ትልቅ አስተዋፆ እንዳለው መረዳት እንደሚገባ ገልፀው ከዛሬው ስልጠና ትምህርት ወስዳችሁ ቅን ታዛዥ ታማኝ የሆነ አገልጋይ እንድትሆኑ መልክቴን አስተላልፋለው በማለት የመክፈቻ ንግግራቸውን አስተላልፈዋል::
የአገልግሎት አሰጣጥ እና የደንበኛ አያያዝ ስልጠና ሰነዱን ያቀረቡት ወ/ሮ ሰላማዊት ይመር ስለ አገልግሎት አሰጣጥ ምንነት, ስለ ተገልጋይ ስነ-ልቦና አረዳድ ክህሎት, ስለ አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት እንዴት ማዘመን ይቻላል,በሚል አቅርበዋል።
ስልጠናው የደንበኛን ቅሬታ ማስተናገጃ መንገዶችን በትክክል ከመረዳት እና የመፍቻ መንገዶች ጋር በተያያዘ እንዲሁም ስለ አጠቃላይ ፅንሰ ሀሳቡ በማንሳት የተቋሙን ባህሪ መሰረት በማድረግ ተሰጥቷል ::
በመጨረሻም ተሳታፊዎችም የመንግስት ተቋም የራሱ የሆነ የአሰራር ስርአት እና የህግ ማዕቀፍ ያለው በመሆኑ አገልግሎት አሰጣጡ ያንን ማዕከል ያደረገ እንዲሆንና ሰራተኞችም ስራችን በጥራት በመከወን እና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት ይገባናል የሚሉ ሀሳብ አስተያየት ሰጥተዋል::
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም የባለስልጣኑ የኦንላይን ቅሬታ መቀበያ ፎርም ለማግኘት የተዘጋጀ ሊንክ እና አተገባበር በተመለከተ በተቋሙ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ አቶ ሚሊዮን ካሳሁን ተዋውቋል::
ምክትል ስራ አስኪያጅ ኮ/ር አህመድ መሀመድ ስልጠናው መሰጠቱ በቀጣይ ከኛ ምን ይጠበቃል የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ እና ስልጠናው ወደ ተግባርም መቀየር እንደሚያስፈልግ ተገንዝበን የአገልግሎት አሰጣጣችንን ልናሻሽል ልናዘምን እንደሚገባ ገልፀዋል።
ህዳር 26/2017
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠና ጥናት ዳይሬክቶሬት ከፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በደንበኞች አገልግሎት አስጣጥ እና አያያዝ ዙሪያ ለማእከል እና ክፍለ ከተማ ሲቪል ሰራተኞች በባለስልጣኑ መሰብሰባያ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመክፈቻ ንግግራቸው ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከከተማ አስተዳደሩ የተጣለበት ህዝብን በቅንነት በታማኝነት አገልግሎትን በጥራት የመስጠት ኃላፊነትን በመወጣት ላይ የሚገኝ ተቋም እንደመሆኑ እንደነዚ አይነት ስልጠናዎች መዘጋጀታቸው ይበል የሚያሰኝ ተግባር ነው ብለዋል::
በመ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የቅድመ መከላከል እና ስልጠና ዘርፍ ኃላፊ ኮ/ር አህመድ መሀመድ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን ጤናማ ለማድረግ ስልጠናዎች መሰጠታቸው ትልቁን ድርሻ እንዳለው ገልፀዋል::
ስልጠናው ከትምህርት ተቋማት ከምናገኘው እውቀት ባሻገር እንደነዚህ አይነት ስልጠናዎች መዘጋጀታቸው ስራችንን ብቁ እና ተወዳዳሪ ከማድረግ አኳያ ትልቅ አስተዋፆ እንዳለው መረዳት እንደሚገባ ገልፀው ከዛሬው ስልጠና ትምህርት ወስዳችሁ ቅን ታዛዥ ታማኝ የሆነ አገልጋይ እንድትሆኑ መልክቴን አስተላልፋለው በማለት የመክፈቻ ንግግራቸውን አስተላልፈዋል::
የአገልግሎት አሰጣጥ እና የደንበኛ አያያዝ ስልጠና ሰነዱን ያቀረቡት ወ/ሮ ሰላማዊት ይመር ስለ አገልግሎት አሰጣጥ ምንነት, ስለ ተገልጋይ ስነ-ልቦና አረዳድ ክህሎት, ስለ አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት እንዴት ማዘመን ይቻላል,በሚል አቅርበዋል።
ስልጠናው የደንበኛን ቅሬታ ማስተናገጃ መንገዶችን በትክክል ከመረዳት እና የመፍቻ መንገዶች ጋር በተያያዘ እንዲሁም ስለ አጠቃላይ ፅንሰ ሀሳቡ በማንሳት የተቋሙን ባህሪ መሰረት በማድረግ ተሰጥቷል ::
በመጨረሻም ተሳታፊዎችም የመንግስት ተቋም የራሱ የሆነ የአሰራር ስርአት እና የህግ ማዕቀፍ ያለው በመሆኑ አገልግሎት አሰጣጡ ያንን ማዕከል ያደረገ እንዲሆንና ሰራተኞችም ስራችን በጥራት በመከወን እና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት ይገባናል የሚሉ ሀሳብ አስተያየት ሰጥተዋል::
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም የባለስልጣኑ የኦንላይን ቅሬታ መቀበያ ፎርም ለማግኘት የተዘጋጀ ሊንክ እና አተገባበር በተመለከተ በተቋሙ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ አቶ ሚሊዮን ካሳሁን ተዋውቋል::
ምክትል ስራ አስኪያጅ ኮ/ር አህመድ መሀመድ ስልጠናው መሰጠቱ በቀጣይ ከኛ ምን ይጠበቃል የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ እና ስልጠናው ወደ ተግባርም መቀየር እንደሚያስፈልግ ተገንዝበን የአገልግሎት አሰጣጣችንን ልናሻሽል ልናዘምን እንደሚገባ ገልፀዋል።