የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
993 subscribers
1.5K photos
4 videos
1 file
51 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በቴክኖሎጂ የታገዘ የባለጉዳይ የቅሬታ ማቅረቢያ ፎርም ይፋ አደረገ።

*አዳስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተቋሙ ላይ የሚፈጠሩ ቅሬታዎችን መቀበል የሚያስችል ባር ኮድ የያዘ ፎርም ይፋ አደረገ።

ተቋሙ የአሰራር ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በማዘመንና ከመቼውም ጊዜ በላይ የህብረተሰብ አገልጋይነቱን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን የቅሬታ ማቅረቢያ ፎርም ይፋ በማድረጉ ማንኛውም ባለጉዳይ በተቋሙ ላይ ያለውን ቅሬታ በቀላሉ በማቅረብ ቅሬታው መፈታቱን መከታተል እንደሚች ያሳወቁት የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ ናቸው።

አክለውም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ 9995 የተባለ ነፃ የስልክ መስመር እንዳለውና የተለያዩ ጥቆማዎችን እንደሚቀበልና ከህብረተሰቡ ጋር ተቀራርቦ እየሠራ እንደሚገኝ አስታውሰዋል።
በአካል ጉዳተኞች ፅንሰ ሀሳብ እና በወጡ የህግ ማዕቀፎች ላይ ስልጠና ተሰጠ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአካል ጉዳተኞች ፅንሰ ሀሳብ፣ በአካል ጉዳተኞች ዙርያ በወጡ የህግ ማዕቀፎች እና አካል ጉዳተኞችን አካቶ ሰለመስራት ከሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር ለሁሉም ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች የቅድመ መከላከል ሽፍት መሪዎች ፣ አስተባባሪዎች እና የስልጠና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ፡፡

ለዜጎች የተሰጠውን መብት የአካል ጉዳተኞችም መብት በመሆኑ አካል ጉዳተኞችን በማንኛውም የማህበራዊ ጉዳዮች ታሳቢ በማደረግ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸው የባለስልጣኑ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ላቀች ሀይሌ ተናግረዋል ፡፡

በስልጠናው ባለስልጣኑ በአካል ጉዳተኞችን ዙርያ የሚጠበቅበት ጉዳዮች በርካታ ቢሆኑም በዋናነት የግንባታ ተረፈ ምርቶችን በእግረኛ መንገድ ላይ እንዳይቀመጡ በመከታተልና እርምጃ በመውሰድ ፣ ህገወጥ የጎዳና ላይ ንግዶችን በመከላከል መንገዶች ለአካል ጉዳተኞች ምቹ እንድሆኑ በማድረግ እና በተለያዩ ጉዳዮች ለይ አካል ጉዳተኞችን በማገዝ ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣት እንደለበት ተገልጿል ፡፡

በስልጠናው በአካል ጉዳተኞች ፅንሰ ሀሳብ ፣ በአካል ጉዳት ዙርይ የወጡ አለም አቀፍ ህጎች ፣ሀገር አቀፍ ህጎች እና ከአካል ጉዳት ጋር ተያያዥነት ያላቸው ፓሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን አስመልክቶ ሰፊ ግንዛቤ ተሰጥቷል፡

ዘገባው ፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
የከተማው ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የባለስልጣኑ የ2017 ዓ.ም ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገመገመ

ህዳር 05/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዋጅ በተሰጠው ስልጣንና ተግባር ተቋሙ እያከናወነ ያለ ተግባራት እና ያለበት ሁኔታ በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የፍትህና መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴዎች የመስክ ምልከታ በማድረግ የተሰራውን ስራ በተመለከተ የባለስልጣኑ ሀላፊዎችና የሚመለከታቸው የስራ ክፍል ዳይሬክተሮችና ቡድን መሪዎች በተገኙበት ገመገመ።

በግምገማው በሩብ ዓመቱ በቅንጅት ለመስራት በእቅዶች ላይ በመወያየት ከባለድርሻ አካላት ጋር ስምምነት ሰነድ መፈራረም መቻሉ እና ወደ ስራ መገባቱ፣ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዬች ዙሪያ ለፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እና ለሲቪል ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች መሰጠታቸውን፣በቁጥጥርና እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍም በሩብ ዓመቱ በአብዛኛው የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ ሂደት ላይ እንዳለ፣ በበጎ ተግባራት በተመለከተ የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ እንዲሁም ወላጅ ያጡ ህፃናትን እርዳታ ማድረግ መቻሉን በጥንካሬ ተነስቷል።

የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት የፍትህ እና መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ መሉነህ ደሳለኝ ተቋሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ገልፀው አሁንም በርካታ ስራዎች እንደሚቀሩ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የማዘመን ስራዎች ላይ ትኩረት ተሰቶ ሊሰራ እንደሚገባ ገልፀዋል።

በባለስልጣኑ የሚሰጡ አስተያየቶችን መነሻ በማድረግ ክፍተቶችን ለመሙላት ያለው ተነሳሽነት እና ፈጣን ምላሽ ይበል የሚያሰኝ መሆኑን ገልፀው ሊቀጥል እንደሚገባ ተናግረዋል።

በተጨማሪም የቋሚ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ወርቅነሸ ምትኩ ባለስልጣኑ የኮሪደር ልማት ላይ የተሰጠውን ድርሻና የተወጣበት መንገድ በጠቅላይ ሚኒስተሩም ዘንድ እውቅና የተሰጠበት መሆኑ የሚበረታታና በቀጣይ ተጠናክሮ መቀጠል የሚገባው እንደሆነ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተለያዩ የደንብ መተላላፎችን በከተማው ላይ ወቅቱን ጊዜውንና ባህሪውን እየቀያየሩ የሚሰሩ ስራዎች መኖራቸውንና ተቋሙ በቁርጠኝነት አሁንም የደንብ መተላለፎችን ለመቀነስ አጠናክሮ እየሰራ እንደሆነና በጋራ ከሚሰራቸው አካላት ጋር እንዲሁም ከከተማው ነዋሪ ጋር ያለውን ቅንጅታዊ ስራን በቀጣይም በማጠናከር የሚታዩ ክፍተቶች ላይ አጠንክረን እንሰራለን ብለዋል።

ዘገባው:-የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።