የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተሻሻሉ የቅጣት እርከኖችን ይፋ አደረገ
አዲስ አበባ ከተማን በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ፣ጽዱና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የአረንጓዴ ስፍራዎች ፣ፓርኮች መንገዶች እና የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እየተገነቡ ይገኛሉ፡፡
ይህንን ተከትሎ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነትና የልማቶቹን ዘላቂነት ለማስቀጥል ያግዛሉ የተባሉ አዳዲስ ደንቦች ይፋ ተደርገዋል፡፡
ደንቦችን በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና የአዲስ አበባ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በጽዳትና ተያያዥ ህገ-ወጥ ተግባራት ዙሪያ ቀድሞ ሲጠቀምበት በነበረው ደንብ ቁጥር 150/2015 ላይ የነበረውን የቅጣት እርከኖቹን በማሻሻል ወደ ተግባር መግባቱን ተናግረዋል።
የቅጣት እርከኖቹን ለህብረተሰቡ ዝርዝር መረጃ በመስጠት በመረጃ እጦት ለቅጣት እንዳይዳረግ ግንዛቤ መፍጠር ይገባል ብለዋል።
በዚህም ከ2ሺ ብር እስከ 100ሺህ ብር የቅጣት እርከኖች በግለሰቦችና በተቋማት ላይ መጣሉን ተናግረዋል።
በዚህም መሠረት :-
*ማንኛውም ሰው ያመነጨውን ደረቅ ቆሻሻ በግቢው ውስጥ በአግባቡ አለመያዝ፤በዓይነት አለመለየት፤ ማዝረክረክ፤ ለጤናና የአካባቢ ገጽታ በሚጎዳ መልኩ ማከማቸት፤ ለግለሰብ 2 ሺህ ብር ለድርጅት 50 ሺህ ብር
*ማንኛውም የጽዳት አገልግሎት ሰጭ ድርጅት/ማህበር ደረቅ ቆሻሻ ሲሰበስብ ገጽታ ካበላሸ 25 ሺህ ብር
*በተቀመጠው ስታንዳርድ መሰረት ለደንበኛው ተገቢውን አገልግሎት ካልሰጠ 50 ሺ ብር
*ከጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ እውቅና ውጭ የአገልግሎት ክፍያ ከደንበኛው ከተቀበለ 50 ሺ ብር
*ጊዜያዊ የደረቅ ቆሻሻ ማስቀመጫ ቦታዎችን እስከ 5 ሜትር ዙሪያ ድረስ ጽዱ ካላደረገ 50 ሺ ብር
* ማንኛውም በመንገድ የሚንቀሳቀስ ሰው የሲጋራ ቁርጥራጭ፣ የሶፍት ወረቀት፣ ፌስታል፣ የጫት ገለባ፣ የፍራፍሬ ተረፈ-ምርቶች፣የትራንስፖርት ቲኬት፣የሞባይል ካርዶችን፣ የማስቲካና ከረሜላ ሽፋኖች፣ የመሳሰሉት ጥቃቅን ደረቅ ቆሻሻን ባልተፈቀደ ቦታ ወይም በፓርኮች፣ በአረንጓዴ ቦታ፣ በኮሪደር ከጣለ 2 ሺ ብር
*ከመኖሪያ ቤት ወይም ከድርጅት ግቢ ውጭ ያለውን የአካባቢ ንጹህና አረንጓዴ አድርጎ አለመጠበቅ ከመኖሪያ ቤት አጥር ግቢ ውጭ እስከ 5 ሜትር ርቀት አለማጽዳት፤20 ሺ ብር
*ከድርጅት/ተቋም አጥር ግቢ ውጭ እስከ 10 ሜትር አለማጽዳት፤ 100 ሺ ብር
*ወቅታዊና ልዩ ዝግጅት አከናውኖ በዓሉ ሲጠናቀቅ በዕለቱና ወዲያው ዝግጅቱ የተከናወነበትን አካባቢ ከቆሻሻ ያላጸዳ የፕሮግራሙ አዘጋጅ፤ 50 ሺ ብር
*ዓመታዊ፤ ወርሃዊና ሳምንታዊ የእምነት በዓላት ሲከናወኑ ዝግጅቱ ሲጠናቀቅ የዝግጅቱ ባለቤት በዕለቱና ወዲያው አካባቢውን ካላጸዳ፤20 ሺ ብር የሚቀጡ መሆኑም ተመላክቷል ።
አዲስ አበባ ከተማን በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ፣ጽዱና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የአረንጓዴ ስፍራዎች ፣ፓርኮች መንገዶች እና የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እየተገነቡ ይገኛሉ፡፡
ይህንን ተከትሎ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነትና የልማቶቹን ዘላቂነት ለማስቀጥል ያግዛሉ የተባሉ አዳዲስ ደንቦች ይፋ ተደርገዋል፡፡
ደንቦችን በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና የአዲስ አበባ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በጽዳትና ተያያዥ ህገ-ወጥ ተግባራት ዙሪያ ቀድሞ ሲጠቀምበት በነበረው ደንብ ቁጥር 150/2015 ላይ የነበረውን የቅጣት እርከኖቹን በማሻሻል ወደ ተግባር መግባቱን ተናግረዋል።
የቅጣት እርከኖቹን ለህብረተሰቡ ዝርዝር መረጃ በመስጠት በመረጃ እጦት ለቅጣት እንዳይዳረግ ግንዛቤ መፍጠር ይገባል ብለዋል።
በዚህም ከ2ሺ ብር እስከ 100ሺህ ብር የቅጣት እርከኖች በግለሰቦችና በተቋማት ላይ መጣሉን ተናግረዋል።
በዚህም መሠረት :-
*ማንኛውም ሰው ያመነጨውን ደረቅ ቆሻሻ በግቢው ውስጥ በአግባቡ አለመያዝ፤በዓይነት አለመለየት፤ ማዝረክረክ፤ ለጤናና የአካባቢ ገጽታ በሚጎዳ መልኩ ማከማቸት፤ ለግለሰብ 2 ሺህ ብር ለድርጅት 50 ሺህ ብር
*ማንኛውም የጽዳት አገልግሎት ሰጭ ድርጅት/ማህበር ደረቅ ቆሻሻ ሲሰበስብ ገጽታ ካበላሸ 25 ሺህ ብር
*በተቀመጠው ስታንዳርድ መሰረት ለደንበኛው ተገቢውን አገልግሎት ካልሰጠ 50 ሺ ብር
*ከጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ እውቅና ውጭ የአገልግሎት ክፍያ ከደንበኛው ከተቀበለ 50 ሺ ብር
*ጊዜያዊ የደረቅ ቆሻሻ ማስቀመጫ ቦታዎችን እስከ 5 ሜትር ዙሪያ ድረስ ጽዱ ካላደረገ 50 ሺ ብር
* ማንኛውም በመንገድ የሚንቀሳቀስ ሰው የሲጋራ ቁርጥራጭ፣ የሶፍት ወረቀት፣ ፌስታል፣ የጫት ገለባ፣ የፍራፍሬ ተረፈ-ምርቶች፣የትራንስፖርት ቲኬት፣የሞባይል ካርዶችን፣ የማስቲካና ከረሜላ ሽፋኖች፣ የመሳሰሉት ጥቃቅን ደረቅ ቆሻሻን ባልተፈቀደ ቦታ ወይም በፓርኮች፣ በአረንጓዴ ቦታ፣ በኮሪደር ከጣለ 2 ሺ ብር
*ከመኖሪያ ቤት ወይም ከድርጅት ግቢ ውጭ ያለውን የአካባቢ ንጹህና አረንጓዴ አድርጎ አለመጠበቅ ከመኖሪያ ቤት አጥር ግቢ ውጭ እስከ 5 ሜትር ርቀት አለማጽዳት፤20 ሺ ብር
*ከድርጅት/ተቋም አጥር ግቢ ውጭ እስከ 10 ሜትር አለማጽዳት፤ 100 ሺ ብር
*ወቅታዊና ልዩ ዝግጅት አከናውኖ በዓሉ ሲጠናቀቅ በዕለቱና ወዲያው ዝግጅቱ የተከናወነበትን አካባቢ ከቆሻሻ ያላጸዳ የፕሮግራሙ አዘጋጅ፤ 50 ሺ ብር
*ዓመታዊ፤ ወርሃዊና ሳምንታዊ የእምነት በዓላት ሲከናወኑ ዝግጅቱ ሲጠናቀቅ የዝግጅቱ ባለቤት በዕለቱና ወዲያው አካባቢውን ካላጸዳ፤20 ሺ ብር የሚቀጡ መሆኑም ተመላክቷል ።
በሩብ ዓመቱ በእቅድ መሰረት ቀን ከሌት በመስራት ውጤት ውጤታማ ስራዎች መሰራቱ ተገለፀ
መስከረም 26/2017 ዓ.ም
*አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የልደታ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤቱ በ2017 በጀት የአንደኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀሙ ገመገ።
በመድረኩ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ፣የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የባለስልጣኑ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፍሁን አሉላ እና የክ/ከተማው የፅ/ቤቱ ሃላፊ እና ሌሎች አመራሮች እንዲሁም ጠቅላላ የክፍለ ከተማው ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።
በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የልደታ ክፍለ ከተማ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ ያለፉትን የአደባባይ በዓላት ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቁ እቅድ በማውጣት ውይይት በማድረግ እንዲሁም ከተለያዮ የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት የደንብ ማስከበር ፅ/ቤቱ በርካታ ስራዎች በአግባቡ ስራችሁን ስለተወጣችሁ ውጤት ተገኝቷልና እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በበኩላቸው ባለስልጣኑ በከተማ አስተዳደሩ ኃላፊነቶች ተሰቶት እየሰራ የሚገኝ ተቋም መሆኑን ገልፀው ያለፉትን የመስቀል እና የኢሬቻ በዓላት ላይ እንዲሁም በልማት ኮሊደር ስራዎች ላይ የሰራናቸው ስራዎች ይበል የሚያሰኙ መሆናቸውን ገልፀው በቀጣይም በደንብ መተላለፎች በመከላከሉም ረገድ የተሻለ ለውጥ ለማምጣት በዚሁ ትጋት ልንሰራ ይገባል ብለዋል።
በእለቱ ልደታ ክፍለ ከተማ ለነዋሪዎች ውብ፣ ፅዱ እና ምቹ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልፀው፤ባሳለፍነው ሩብ ዓመት የደንብ መተላለፎችን ከመቀነስ አንፃር እቅድ ይዘን ቀን ከሌት በመስራት ውጤት መገኘቱና ለቀጣይ ወራት ስራዎች ለማሳካት እቅድ ከማቀድ ጀምሮ የቅድመ ዝግት ተግባራት መከናወኑ የተናገሩት የፅ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ካሴ ናቸው ።
በእለቱ የፅ/ቤቱን የሩብ አመት አፈፃፀም በሰነድ የቅድመ መከላከል እና ስልጠና ስራዎች አስተባባሪ አቶ ሙሉቀን እንየው የቀረበ ሲሆን በሰነዱ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
በመጨረሻም ጉልህ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላትና ፅ/ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ልጆች የምስጋና እና ስጦታ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው:- አዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
መስከረም 26/2017 ዓ.ም
*አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የልደታ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤቱ በ2017 በጀት የአንደኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀሙ ገመገ።
በመድረኩ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ፣የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የባለስልጣኑ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፍሁን አሉላ እና የክ/ከተማው የፅ/ቤቱ ሃላፊ እና ሌሎች አመራሮች እንዲሁም ጠቅላላ የክፍለ ከተማው ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።
በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የልደታ ክፍለ ከተማ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ ያለፉትን የአደባባይ በዓላት ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቁ እቅድ በማውጣት ውይይት በማድረግ እንዲሁም ከተለያዮ የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት የደንብ ማስከበር ፅ/ቤቱ በርካታ ስራዎች በአግባቡ ስራችሁን ስለተወጣችሁ ውጤት ተገኝቷልና እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በበኩላቸው ባለስልጣኑ በከተማ አስተዳደሩ ኃላፊነቶች ተሰቶት እየሰራ የሚገኝ ተቋም መሆኑን ገልፀው ያለፉትን የመስቀል እና የኢሬቻ በዓላት ላይ እንዲሁም በልማት ኮሊደር ስራዎች ላይ የሰራናቸው ስራዎች ይበል የሚያሰኙ መሆናቸውን ገልፀው በቀጣይም በደንብ መተላለፎች በመከላከሉም ረገድ የተሻለ ለውጥ ለማምጣት በዚሁ ትጋት ልንሰራ ይገባል ብለዋል።
በእለቱ ልደታ ክፍለ ከተማ ለነዋሪዎች ውብ፣ ፅዱ እና ምቹ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልፀው፤ባሳለፍነው ሩብ ዓመት የደንብ መተላለፎችን ከመቀነስ አንፃር እቅድ ይዘን ቀን ከሌት በመስራት ውጤት መገኘቱና ለቀጣይ ወራት ስራዎች ለማሳካት እቅድ ከማቀድ ጀምሮ የቅድመ ዝግት ተግባራት መከናወኑ የተናገሩት የፅ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ካሴ ናቸው ።
በእለቱ የፅ/ቤቱን የሩብ አመት አፈፃፀም በሰነድ የቅድመ መከላከል እና ስልጠና ስራዎች አስተባባሪ አቶ ሙሉቀን እንየው የቀረበ ሲሆን በሰነዱ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
በመጨረሻም ጉልህ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላትና ፅ/ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ልጆች የምስጋና እና ስጦታ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው:- አዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
የሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ይካሄዳል
መስከረም 27/2017 ዓ.ም
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ይካሔዳል፡፡
በኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 58 ንዑስ አንቀፅ (2) እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 24 ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአንድ ዓመት የሥራ ጊዜ ከመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መሆኑ ተደንግጓል፡፡
በድንጋጌው መሰረት የ6ኛው ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የተጠናቀቀ ሲሆን 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓትም የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት በተገኙበት ዛሬ ከቀኑ 8 ሠዓት ጀምሮ ይካሄዳል ተብሏል፡፡
በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይም የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት ለሁለቱ የፌዴራል መንግሥት ምክር ቤቶች ዓመታዊ ሥራቸውን መጀመራቸውን በማብሰር የፌዴራል መንግሥቱን ዓመታዊ ዕቅድ ያቀርባሉ።
የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደሚገኙም ተጠቁሟል፡፡
መስከረም 27/2017 ዓ.ም
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ይካሔዳል፡፡
በኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 58 ንዑስ አንቀፅ (2) እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 24 ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአንድ ዓመት የሥራ ጊዜ ከመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መሆኑ ተደንግጓል፡፡
በድንጋጌው መሰረት የ6ኛው ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የተጠናቀቀ ሲሆን 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓትም የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት በተገኙበት ዛሬ ከቀኑ 8 ሠዓት ጀምሮ ይካሄዳል ተብሏል፡፡
በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይም የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት ለሁለቱ የፌዴራል መንግሥት ምክር ቤቶች ዓመታዊ ሥራቸውን መጀመራቸውን በማብሰር የፌዴራል መንግሥቱን ዓመታዊ ዕቅድ ያቀርባሉ።
የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደሚገኙም ተጠቁሟል፡፡
ባለስልጣኑ በ2017 በጀት ዓመት በመጀመሪያ ሩብ አመት የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ገመገመ
27/01/2017ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 የመጀመሪያ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የባለስልጣኑ የበላይ ኃላፊዎች በተገኙበት ከማዕከሉ ፕሮሰስ ካውንስል አባላት ጋር በዛሬው እለት ተገምግሟል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ ክትትል ፣ ቁጥጥርና እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ እና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍና የድጋፍ ሰጪ ዳይሬክተሮች የ2017 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በሩብ ዓመቱ የታዪ ክፍተቶች ያጋጠሙ ችግሮችን እና ጠንካራ ጎኖች ቀርበው ውይይት ተደርጓል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ ስራዎች በጥንካሬ የሚገለፁ መሆናቸው ገልፀው በቀጣይ ሁሉም ሰራተኞች እና በየደረጃው ያሉ አመራሮች በቁርጠኝነት በመስራት አሁን ላይ የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል ከተማችን ደንብ መተላለፎች የቀነሰባት ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው ።
27/01/2017ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 የመጀመሪያ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የባለስልጣኑ የበላይ ኃላፊዎች በተገኙበት ከማዕከሉ ፕሮሰስ ካውንስል አባላት ጋር በዛሬው እለት ተገምግሟል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ ክትትል ፣ ቁጥጥርና እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ እና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍና የድጋፍ ሰጪ ዳይሬክተሮች የ2017 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በሩብ ዓመቱ የታዪ ክፍተቶች ያጋጠሙ ችግሮችን እና ጠንካራ ጎኖች ቀርበው ውይይት ተደርጓል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ ስራዎች በጥንካሬ የሚገለፁ መሆናቸው ገልፀው በቀጣይ ሁሉም ሰራተኞች እና በየደረጃው ያሉ አመራሮች በቁርጠኝነት በመስራት አሁን ላይ የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል ከተማችን ደንብ መተላለፎች የቀነሰባት ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው ።