የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.1K subscribers
1.79K photos
4 videos
1 file
53 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
የዛሬ ጀምበር ወጥታ እስክትጠልቅ  ስድስት መቶ ሚሊዮን ችግኞችን ልንተክል ኢትዮጵያውያን ሁሉ አቅደን ነበር። ያሰብነውን ሳናሳካ ጀምበር የሚጠልቅብን አይደለንምና በአንድ ጀምበር 615.7 ሚሊዮን ችግኞችን መትከል ችለናል።

ህፃናት ተስፋቸውን ተክለዋል። ወጣቶች ጽናተቸውን አሳይተዋል። አረጋውያን ውርስ አኑረዋል። ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ ከቤታቸው ወጥተው የማይደበዝዝ አሻራ አኑረዋል። በማበራችን እና በመጽናታችን በአለም በሌላ ስፍራ በአንድ ጀምበር ያልተደረገውን እኛ ኢትዮጵያውያን አድርገነዋል። ዛሬ ለአየር ንብረት ለውጥ ሚዛን ጥበቃ ቆመን ውለናል። የአፈር መራቆትን ለመመከት ተሰልፈን ውለናል። የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ስንደክም ውለናል። ምድራችንን አረንጓዴ ለማልበስ ልምላሜን ለመመለስ ሳንበገር ሰርተናል። ፈጣሪም ረድቶን ለዛሬዋ ጀምበር ያሰብነውን አሳክተናል።

ዛሬ 29.1 ሚሊዮን ዜጎች በ318.4 ሄክታር በጂኦስፓሻል መረጃ በተገኘባቸው ስፍራዎች ላይ ችግኞችን ተክለዋል። እስካሁን በመረጃ ቋት ከተመዘገበው ውጭ የተተከሉ ችግኞች መረጃ በተከታታይ የሚገለፅ ይሆናል።

ለአስደማሚው የኢትዮጵያውያን ኅበረት እና ጽናት እነሆ ምስጋና። ለስኬታችን የእቅድ፣ የክትትል እና የመረጃ አውታር በመሆን በትጋት የሰራችሁ አመራሮች ባለሞያዎች እና የሚዲያ ተቋማት ምስጋና ይገባችኋል። ምኞት ተግባራችን ሁሉ የተሻለች ኢትዮጵያን በኅብረት ገንብቶ ማቆየት ነው። ይኽንኑ እንቀጥላለን።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የረዳን ፈጣሪ ይመስገን!!
እንኳን ደስ አለን!

ኢትዮጵያውያን የዛሬ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅደን 615.7 ሚሊዮን ችግኞችን መትከል የቻልን ሲሆን ከዚህም ውስጥ እንደ አዲስ አበባ 6 ሚሊዮን አቅደን 9.9 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ተክለናል::

የከተማችን ነዋሪ የመሪችንን ጥሪ ተቀብሎ ማልዶ በመነሳት በአስደናቂ አፈፃፀም ከእቅድ በላይ ችግኞችን በመትከል ታሪክ የማይዘነጋው ታላቅ ገድል በመፈጸሙ ታላቅ አክብሮት ከምስጋና ጋር የሚገባው ሲሆን በተጨማሪም ይህ እንዲሳካ ያስተባበራችሁ እና የደከማችሁ አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞቻችን በራሴና በከተማ አስተዳደራችን ስም ላመሰግናችሁ እወዳለሁ::

ይህ ዛሬ ያሳየነውን የተባበረ ክንድ የሚያመጣውን ለውጥ በሌሎች የልማት ስራዎቻችን ላይ በመድገም የሃገራችንን ብልፅግና እውን እንድናደርግ ጥሪዬን አቀርባለሁ::
የምትተክል ሀገር የሚያጸና ትውልድ!

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
3👍2👏1
"የህዳሴ ግድባችን በትናንትናው ዕለት 3ኛው እና 4ኛውን ተርባይኖች ሥራ አስጀመርን። ሌሎቹ ዩኒቶች በተቀመጠላቸው እቅድ መሰረት በመከናወን ላይ ይገኛሉ"።

መከናወንን የሰጠን ፈጣሪ ይመስገን!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ
👍3
ባለስልጣኑ መሬት የወረሩ እና ባልተፈቀደ ቦታ ሽንት የሸኑ 22 ግለሰቦች መቅጣቱ አስታወቀ

ነሀሴ 20/2016 ዓ.ም
**አዲስ አበባ6**

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የህዝብና የመንግስት የሆነ መሬት በህገወጥ መንገድ የወረሩ ግለሰቦች እና በከተማው ባልተፈቀደ ቦታ ሽንት የሸኑ 22 ግለሰቦች መቅጣቱ አስታወቀ።

ባለስልጣኑ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረደ 11 ባልታፋቃደ ቦታ ሽንታቸው ሸንተው አካባቢ ያቆሸሹ 22 ግለሰቦች በባለስልጣኑ በተሻሻለዉ የቅጣት ሰንጠረዥ 2 ደንብ ቁጥር 167/2016 መሰረት 22 ሰዎች እያንዳንዳቸው 2000 ሺህ ብር አጣቃላይ 44000 ሺህ ብር በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ማደረጉ ገልጿል ።

በተጨማሪም በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 የህዝብና የመንግስት የሆነ መሬት በህገወጥ መንገድ በመውረር ታጥሮ የነበረ 5 ቦታዎች በአጠቃላይ 2,200 ካሬ ሜትር መሬት በአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እርምጃ መወሰዱ ባለስልጣኑ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በህገ ወጦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለፀ ሲሆን ሆን ብለዉ ደንብ የሚተላለፉ አንዳንድ ግድ የሌሽና ስግብግብ ግለሠቦች ልማት ወዳዱ የከተማችን ነዋሪዎች በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ጠይቋል።

ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የትዊተር/X/ ሚዲያ ገፃችን
https://x.com/Addis_Denb?t=u8wW3qnxWk48GYzJ4RD96Q&s=09
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ!
👍8💔2
እንኳን ደስ አላቹ እንኳን ደስ አለን!!!

ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ እውቅና ተሰጠው

            ነሐሴ 25/2016 ዓ.ም
            **አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ አበባ ከተማ በተሰራው የልማት ኮሪደር ስራዎች ላደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከኢትትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ የፌደራልና እና የከተማው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት እውቅና እና የወርቅ ሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆነ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጁ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በከተማው የልማት ኮሪደር ስራዎች ከተጀመረባቸው ጊዜ አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ በ7/24 እየሰራ በከተማ አስተዳደሩ በተያዘው እቅድ መሰረት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ተናግረዋል፡፡

ባለስልጣኑ በተለይ በተሰራው የኮሪደር ልማቶች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ እና ውበቱና ጽዳቱ ለማስጠበቅ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር እና በደንቡ መሰረት አስተማሪ ቅጣት በመቅጣት ደንብ እያስከበረ መሆኑ ገልጸዋል፡፡

ዋና ስራ-አስኪያጁ ለተቋማቸው በተሰጠው እውቅና አመስግነው በለቀጣይ የበለጠ ስራ ለመስራት ትልቅ መነቃቃትን አንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡

ዋና ስራ-አስኪያጁ ባለስልጣኑ በተሰጠው እውቅና እና የወርቅ ሰርተፊኬት የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራሮች፣ኦፊሮች፣መላው የጠቋሙ ሰራተኞች እና ባለድርሻ አካሎቻችን ለስራችሁ ውጤት አግኝታችኋልና እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡

ዘገባው ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍13