የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.1K subscribers
1.79K photos
4 videos
1 file
53 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣኑ በተሰሩ የልማት  የደንብ መተላለፍ በሚፈፅሙ ግለሰቦች ላይ የሚወስደው እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ ገለፀ

ትናንት ሀምሌ 19/2016 በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች በመሰረተ ልማት ላይ ጉዳት ያደረሱ ግለሰቦች በደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ክትትልና ህዝቡ በሰጠው ጥቆማ መሰረት በደንብ ጥሰት ተቀጥተዋል።

በዚህም መሰረት ፦                       
               
1.ቦሌ ክ/ከተማ

የኮቨርስቶን መንገድ የሠበረ  አንድ ተሽከርካሪ  5,000  ብር ተቀጥቷል። እንዲሁም በዚሁ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ተረፈ ምርት (ቆሻሻ) በዋና መንገድ ላይ ያወረደ ተሽከርካሪ  50,000 ብር ተቀጥቷል።

2. ቂርቆስ ክ/ከተማ
ሞተር ሳይክል በእግረኛ መንገድ ላይ ያቆመ ግለሰብ 3,000 ብር ተቀጥቷል።

አካባቢያቸዉን ያቆሸሹ ሁለት ሱቆች በአጠቃላይ 20,000 ብር ሲቀጡ፣ አከባቢውን ያቆሸሸ አንድ የፅዳት ማህበር 20,000 ብር ተቀጥቷል።

3. ልደታ ክ/ከተማ ደግሞ አንድ ተሽከርካሪ መንገድ የማበላሸት ተግባር በመፈፀሙ 50,000 ብር ተቀጥቷል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በልማት ስራም ሆነ በመሰረተ ልማት ጥበቃ ዙሪያ ከከተማው ነዋሪ ጋር እጅና ጓንት በመሆን  ፅዱ፣ ውብ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ የሆነች አዲስ አበባን እውን ለማድረግ የጀመረውን ተግባር አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።
👍14👏3
በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል ኢትዮጵያውያን የጀመሩት ስራ ማሳካት እንደምንችል የሚያረጋጥ መሆኑ ተገለፀ

ነሀሴ 17/2016 ዓ.ም
*አዲስ አበባ*

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራሮች እና ሰራተኞች በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል በተያዘው መርሀ-ግብርን መሰረት «የምትተከል ሃገር፣ የሚያፀና ትውልድ » በሚል መሪቃል የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አከናወኑ፡፡

የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 02 ልዩ ቦታው የካ ጣፎ ገብርኤል ቤተ ክርስቱያን አካባቢ በተዘጋጀው የችግኝ ቦታዎች ላይ ከጠዋት 12:00 በመገኘት የአረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡

የባለስልጣኑ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አመራሮች እና ኦፊሰሮች ከጠዋት 12:00 ሰዓት ጀምሮ በየክፍለ ከተማቸው በልዩ ልዩ በተዘጋጁ አካባቢዎች ችግኝ ተክለዋል፡፡

በፕሮግራሙ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በጠቅላይ ሚ/ር ክቡር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለከተማውና ለአካባቢ ውበት ከፍተኛ ጠቀሜታ ከመኖሩ በላይ ኢትዮጵያውያን የጀመሩት ስራ ማሳካት እንደምንችል ያረጋገጥንበት መሆኑ ገልፀዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ቀደም ብሎ 15000/አስራ አምስት ሺህ/ ችግኝኞች መትከሉ ይታወቃል፡፡

ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
1