ባለስልጣኑ የደጋፊ ዳይሬክቶሬቶች የ2018 በጀት አመት ካስኬዲንግ እቅድ የመፈራረም ስነ-ስርዓት አካሄደ
ነሀሴ 14/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበበ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 በጀት አመት መሪ እቅድ ካስኬዲንግ ከማዕከል ደጋፊ ዳይሬክቶሬቶች ጋር የመፈራረም ስነ-ስርዓት አካሄደ ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የድጋፍ ሰጭ ዳይሬክትሬቶቹ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ሁሉም በመተባበር ሚናውን በመወጣት ባለስልጣኑን የገፅታና ግንባታና ውጤታማነት ከፍ ማድረግ እንደሚገባ መልክት አስተላልፈዋል።
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ በባለስልጣኑ የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ባለስልጣኑ የደንብ ጥሰቶችን ከመቆጣጠር ከመከላከል በተጨማሪ በተቋም ግንባታው የተሞክሮ ማዕከል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
በ2017 በጀት የስመወገበውን ውጤት በ2018 በጀትም ለማስቀጠል እቅድ ዋና በመሆኑ ሁሉም የድርሻውን በመወጣት ውጤቱን ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የባለስልጣኑ የዕቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀደም ሲል ካስኬዲንጉን ለክፍለ ከተሞች እና ለዘርፎች ማውረዱን ጠቁመው በዛሬው ቀን ደግሞ ለደጋፊ ዳይሬክቶሬቶች እቅድ እንደሚያወርዱ ገልፀዋል ።
ከዚህ በፊት የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ በስሩ ከሚገመተው ከስልጠናና ቅድመ መከላከል ዳይሬክቶሬቶች ጋር ካስኬዲንግ እቅድ የተፈራረሙ መሆኑ ተገልጿል።
የካስኬዲንእቅዱ በሂደት ለቡድኖች እና ለባለሙያ ድረስ በማውረድ እያንዳንዱ የወረደለትን ተግባራት በማከናወን በየጊዜው በድጋፍና በግብረ-መልስ መታየት እንዳለበት ተመላክቷል።
በመጨረሻም ደጋፊ ዳይሬክቶሬቶቹ ከባለስልኑ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ጋር የ2018 በጀት ካስኬዲንግ እቅድ የወረደላቸውን ተፈራርመዋል።
መረጃው ፦የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://www.youtube.com/@AACODEENFORCEMENT
https://linktr.ee/aacodeenforcement
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ
ነሀሴ 14/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበበ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 በጀት አመት መሪ እቅድ ካስኬዲንግ ከማዕከል ደጋፊ ዳይሬክቶሬቶች ጋር የመፈራረም ስነ-ስርዓት አካሄደ ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የድጋፍ ሰጭ ዳይሬክትሬቶቹ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ሁሉም በመተባበር ሚናውን በመወጣት ባለስልጣኑን የገፅታና ግንባታና ውጤታማነት ከፍ ማድረግ እንደሚገባ መልክት አስተላልፈዋል።
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ በባለስልጣኑ የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ባለስልጣኑ የደንብ ጥሰቶችን ከመቆጣጠር ከመከላከል በተጨማሪ በተቋም ግንባታው የተሞክሮ ማዕከል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
በ2017 በጀት የስመወገበውን ውጤት በ2018 በጀትም ለማስቀጠል እቅድ ዋና በመሆኑ ሁሉም የድርሻውን በመወጣት ውጤቱን ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የባለስልጣኑ የዕቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀደም ሲል ካስኬዲንጉን ለክፍለ ከተሞች እና ለዘርፎች ማውረዱን ጠቁመው በዛሬው ቀን ደግሞ ለደጋፊ ዳይሬክቶሬቶች እቅድ እንደሚያወርዱ ገልፀዋል ።
ከዚህ በፊት የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ በስሩ ከሚገመተው ከስልጠናና ቅድመ መከላከል ዳይሬክቶሬቶች ጋር ካስኬዲንግ እቅድ የተፈራረሙ መሆኑ ተገልጿል።
የካስኬዲንእቅዱ በሂደት ለቡድኖች እና ለባለሙያ ድረስ በማውረድ እያንዳንዱ የወረደለትን ተግባራት በማከናወን በየጊዜው በድጋፍና በግብረ-መልስ መታየት እንዳለበት ተመላክቷል።
በመጨረሻም ደጋፊ ዳይሬክቶሬቶቹ ከባለስልኑ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ጋር የ2018 በጀት ካስኬዲንግ እቅድ የወረደላቸውን ተፈራርመዋል።
መረጃው ፦የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://www.youtube.com/@AACODEENFORCEMENT
https://linktr.ee/aacodeenforcement
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ
www.aacea.gov.et
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን | Home Page
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን 74/2014 ዓ.ም በአንቀጽ 47 መሰረት ተጨማሪ ተግባርና ኃላፊነት ተሰጥቶት ባለስልጣን ሆኖ የተቋቋመ ሲሆን አዋጅ ቁጥር 74/2014 መሰረት በማድረግ ባለስልጣኑ ደንብ ቁጥር 150/2015 በም/ቤት በማጸደቅ እና መዋቅራዊ ክለሳ በማድረግ ተመሠረተ።
👍3❤1
ለባለስልጣኑ አመራር እና ኦፊሰሮች በኢትዮጵያ ፓሊስ ዩኒቨርስቲ ስልጠና ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ውይይት ተካሄደ
15/12/ 2017 ዓ.ም
ሰንዳፋ
በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ-አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸዉ የተመራው የልዑካን ቡድን በቀጣይ ለባለስልጣኑ አመራሮች እና ነባር የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ውይይት ተካሄደ፡፡
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸዉ በዉይይቱ ላይ በቀጣይ ለአመራሩ እና ለነባር ኦፊሰሩ የሚሰጠው ስልጠና በስነ_ ምግባር ፣ በህግ ፣ ከኮምንኬሽንና ተግባቦት ዙሪያ ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅና የወንዝ ዳር ብክለትን በመከለከልና በመቆጣጠር ሂደት አዲስ አበባን ከተማ ያማከለ ስልጠና እንደሚሆን ገልፀዋል።
በፓሊስ ዩኒቨርሲቲው ለሰልጣኝ አመራሮቹና ነባር ኦፊሰሮቹ የሚሰጠዉ ስልጠና ለስራቸው አጋዥ ብሎም አበረታች እንደሚሆን በማንሳት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎቹ ለአመራሮቹ እና ፈጻሚ አካላት የመፈጸም አቅማቸውን ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚረዳ እንዲሁም በቀጣይ ለሚሰጡ ተልእኮዎች ዝግጁ እንደሚያደርጋቸዉ በውይይቱ ላይ ሀሳባቸውን ገልጸዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ምክትል ፕሬዝዳት ረዳት ኮሚሽነር ደረጄ ተስፋዬ ለአባላቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ፖሊስ ዩኒቨርሲቲው ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር አብሮ የመስራት ልምዱን ከበፊቱ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
አክለውም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው ስራቸዉን በአግባቡ እንዲያከናውኑ የሚችሉበትን በቂ ዕውቀት የሚያገኙበት ስልጠና ልምድና እውቀቱ ባላቸው አሰልጣኞች እንደሚያዘጋጁ ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአመራር ስልጠና አቅም ግንባታ ማዕከል መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ኮማንደር ፍቃዱ ጌታቸው በውይይቱ ወቅት ከራሱ በላይ ህዝብን ጥቅም የሚያስቀድም ከህዝቡ በፊት እሞታለሁ ብሎ ተጨንቆ ለሀገሩና ለህዝቡ የሚሰራ ሰራተኛ ለመፍጠር እንሰራለን ብለዋል ።
በዉይይቱ የባለስልጣኑ የስልጠና ዳይሬክቶሬት የሆኑት ወ/ሮ ላቀች ሀይሌ በስልጠና አሰጣጥ እና በሚሰጡ የስልጠና ሰነዶች ርዕሶች ዙሪያ ገለፃ አድርገዋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
15/12/ 2017 ዓ.ም
ሰንዳፋ
በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ-አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸዉ የተመራው የልዑካን ቡድን በቀጣይ ለባለስልጣኑ አመራሮች እና ነባር የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ውይይት ተካሄደ፡፡
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸዉ በዉይይቱ ላይ በቀጣይ ለአመራሩ እና ለነባር ኦፊሰሩ የሚሰጠው ስልጠና በስነ_ ምግባር ፣ በህግ ፣ ከኮምንኬሽንና ተግባቦት ዙሪያ ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅና የወንዝ ዳር ብክለትን በመከለከልና በመቆጣጠር ሂደት አዲስ አበባን ከተማ ያማከለ ስልጠና እንደሚሆን ገልፀዋል።
በፓሊስ ዩኒቨርሲቲው ለሰልጣኝ አመራሮቹና ነባር ኦፊሰሮቹ የሚሰጠዉ ስልጠና ለስራቸው አጋዥ ብሎም አበረታች እንደሚሆን በማንሳት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎቹ ለአመራሮቹ እና ፈጻሚ አካላት የመፈጸም አቅማቸውን ይበልጥ ለማጎልበት እንደሚረዳ እንዲሁም በቀጣይ ለሚሰጡ ተልእኮዎች ዝግጁ እንደሚያደርጋቸዉ በውይይቱ ላይ ሀሳባቸውን ገልጸዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ምክትል ፕሬዝዳት ረዳት ኮሚሽነር ደረጄ ተስፋዬ ለአባላቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ፖሊስ ዩኒቨርሲቲው ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር አብሮ የመስራት ልምዱን ከበፊቱ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
አክለውም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው ስራቸዉን በአግባቡ እንዲያከናውኑ የሚችሉበትን በቂ ዕውቀት የሚያገኙበት ስልጠና ልምድና እውቀቱ ባላቸው አሰልጣኞች እንደሚያዘጋጁ ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአመራር ስልጠና አቅም ግንባታ ማዕከል መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ኮማንደር ፍቃዱ ጌታቸው በውይይቱ ወቅት ከራሱ በላይ ህዝብን ጥቅም የሚያስቀድም ከህዝቡ በፊት እሞታለሁ ብሎ ተጨንቆ ለሀገሩና ለህዝቡ የሚሰራ ሰራተኛ ለመፍጠር እንሰራለን ብለዋል ።
በዉይይቱ የባለስልጣኑ የስልጠና ዳይሬክቶሬት የሆኑት ወ/ሮ ላቀች ሀይሌ በስልጠና አሰጣጥ እና በሚሰጡ የስልጠና ሰነዶች ርዕሶች ዙሪያ ገለፃ አድርገዋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤6👍2