የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.1K subscribers
1.81K photos
4 videos
1 file
53 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
የልደታ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በወረዳ 05 የአቅመ ደካማ እናት የቤት እድሳት አስጀመረ

16/11/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራና ምክትል ስራ አስኪያጆች በተገኙበት በወረዳ 05 ነዋሪ የሆኑ አቅመ ደካማ ወ/ሮ አስታጥቃ ቢሻው ቤት በ90 ቀን እቅድ ውስጥ አድሶ ለማስረከብ አስጀምረዋል።

ተቋሙ በ90 ቀናት እቅድ ውስጥ የችግኝ ተከላ፣ የማዕድ ማጋራት፣ የደም ልገሳና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ የማድረግ ስራዎችን አጠናክሮ እየሠራ እንደሚገኝ ሻለቃ ዘሪሁን አስታውሰው፤ የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የአቅ ደካማ እናት ቤትን በአጭር ቀናት ውስጥ አድሶ ለማስረከብ ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ተናግረዋል።

ባለስልጣኑ የ2017 በጀት ዓመትእቅድ አፈፃፀም በላቀ ውጤት በማጠናቀቅ ከከተማው አስተዳደር ሴክተር ተቋማት ጋር ተወዳድሮ 1ኛ በመውጣት የመኪና ሽልማት በማግኘቱ ለተገኘው ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የህብረተሰብ ክፍሎችና አጠቃላይ የተቋሙ አመራሮች፣ ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮችና ባለሙያዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍74👎1👏1
ባለስልጣኑ በ2017 አፈፃፀሙ ያገኘውን የእውቅናና ሽልማት በ2018 በጀት አመት ለማስቀጠል ከ11ዱም ክፍለ ከተማ አመራሮች ጋር ተወያየ

ሀምሌ 16/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2017 በጀት ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተካሄደ ምዘና ከተቋማት ( ካቢኔ አባል ካልሆኑ ) በጣም ከፍተኛ ውጤት በማምጣት አንደኛ ደረጃ በማግኘቱ የመኪና ሽልማት መሸለሙን አስመልክቶ የባለስልጣኑ ማኔጅመንት አባላት ደስታውን በመግለጽ ውጤቱ ለማስቀጠል ከ11ዱም ክፍለ ከተማ አመራሮች ጋር ውይይት ተካሄደ።

የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ይህ የዕውቅናና ሽልማት መምጣት የቻለው ከላይ እስከታች የሚገኝ አመራርና ሰራተኛ በትጋት፣ በቅንጅት፣በትብብር በተለይም የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሩ የተሰጠውን ተልዕኮ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል በአግባቡ በመወጣቱ በመሆኑ የክፍለ ለከተማ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል ።

አክለውም ውጤቱ ለቀጣይ ስራ አቅም የሚሆን ሲሆን ለውጤቱ መመዝገብ አስተዋጽዎ ላደረጋችሁ የክፍለ ከተማ ና የወረዳ የደንብ ጽ/ቤት ኃላፊዎቹ ሰራተኞችና ኦፊሰሮቻችን በሙሉ ምስጋና በማቅረብ እንኳን ደስ ያላችሁ የድካም ውጤት በመሆኑ ምስጋና ይገባችኋል በማለት ደስታቸውን አጋርተዋል።

የደስታው ተካፋይ የሆኑ የክፍለ ከተማ አመራሮች 2017 በጀት አመት ከፍተኛ ለውጥ የታየበት የከተማ አስተዳደሩን የልማት ስራዎች የተጠበቁበት እና የደንብ ጥሰቶች የቀነሱበት በመሆኑን ውጤቱን ይጠብቁት እንደነበር እና በቀጣይ አመትም ለማስቀጠል እንደሚሰሩ ተናግረዋል ።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍41
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የምሽት የንግድ ተቋማት ሰላማዊ ግብይት እየተካሄደ እንደሚገኝ ተገለፀ

16- 11- 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከከተማው ንግድ ቢሮ ጋር በመሆን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የንግድ ተቋማት የምሽት ስራዎች እንቅስቃሴ ምልከታ አካሂደዋል።

የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምሽት የንግድ እንቅስቃሴ ወቅት የደንብ ጥሰት እንዳይኖር የምሽት ምድብ በመመደብ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን የምሽት ስራው የሚያስተጓጉል የደንብ ጥሰትና የፀጥታ ችግር እንዳላጋጠመ ገልፀዋል።

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደተናገሩት ከተማችን አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረትና የበርካታ ሃገራት ኢምባሲዎች መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን ይህንን የሚመጥን የምሽት ንግድ እንቅስቃሴ እንዲኖራት እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ይህም በከተማዋን አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዘርፍ ይበልጥ የሚያነቃቃ ነው ብለዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው የምሽት የንግድ እንቅስቃሴ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው የፀጥታ ችግር እንዳይኖር ህብረተሰቡን በባለቤትነት በማሳትፍ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለው የምሽት ግብይት ለንግዱ ማህበረሰብ እና በትራንስፖርት ለተሰማሩት ከሚያበረክተው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በተጨማሪ ማህበራዊ መስተጋብር ከማሳደግ አንፃር ትልቅ ሚና አለው ብለዋል።

በተለያዩ ጊዜያት በሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ በክፍለ ከተማው የሚገኙ የንግድ ተቋማት እስከ ምሽቱ 4 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አቶ አድማሱ ገልፀው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎችም ያለምንም ስጋት እንዲገበያዩ ጠይቀዋል።
👍61