የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለሁለት ወራት ያሰለጠናቸው ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሮችን አሰመረቀ
30/09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከ2ሺህ በላይ የ6ተኛ ዙር ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሮችን ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና የካቤኔ አባላላታቸው በተገኙበት በድምቀት አስመረቀ።
ሰልጣኞቹ ላለፉት ሁለት ወራት በንድፈ-ሃሳብ እና በወታደራዊ ስልጠና በኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ አፓስቶ ካምፓስ ሰልጥነው በብቃት ማጠናቀቃቸውን የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ የዛሬ ተመራቂዎች የትምህርት ደረጃቸው ዲግሪና ከዚያ በላይ የሆኑ 2074 ኦፊሰሮች መሆናቸውን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ አሳውቀዋል።
ሰልጣኞቹ ለ192 ሰዓታት የንድፈ ሃሳብ ስልጠና እና ለ239 ሰዓታት የወታደራዊ ስልጠና በማካሄድ በድምሩ ለ431 ሰዓታት 2074 ተመራቂ ኦፊሰሮች ስልጠናው በሚፈለገው ዲስፕሊን መሠረት አሰልጥኖ ለምረቃ ብቁ ማድረጉን የኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል እና የኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ፕሬዘዳንት መስፍን አበበ አስታውቀዋል።
ባለስልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ የመፈፀምና የማስፈፀም አቅሙን እያላቀ ከተማ አስተዳደሩ በሚፈልገው ልክ ተልዕኮውን እየተወጣ የሚገኝ ተቋም መሆኑን የገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ክብር ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ሲሆን ትልቅ መሰጠትና ብቃት ለሚጠይቀው የመስክ ስራ እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ አሳስበዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ ከተማችን አዲስ አበባ እያስመዘገበች ባለችው ሁሉን አቀፍ ልማት ለነዋሪዎቿ ምቹ እየሆነች ነው።
ይህንንም ልማት በህግና ደንብ መመራት እንዲችል በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂና በሎጀስቲክ በመደገፍ ላይ እንገኛለን።
ከተማዋ በቀን ብቻ ሳይሆን በምሽትም ጭምር እንቅስቃሴዋ ያልተገደበ እንዲሆን ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሩን በሶስት ሺፍት በማሰማራት ህግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ ለመስራት አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል።
በህዝብ ዘንድ ክብር የሚጎናፀፍ አገልግሎት ለመስጠት በዲሲፕሊን ታንፃችሁ ህዝባችሁን በማሳተፍና በማስተባበር ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ አደራ እያልኩ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ብለዋል።
ዘገባው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
30/09/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከ2ሺህ በላይ የ6ተኛ ዙር ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሮችን ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና የካቤኔ አባላላታቸው በተገኙበት በድምቀት አስመረቀ።
ሰልጣኞቹ ላለፉት ሁለት ወራት በንድፈ-ሃሳብ እና በወታደራዊ ስልጠና በኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ አፓስቶ ካምፓስ ሰልጥነው በብቃት ማጠናቀቃቸውን የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ የዛሬ ተመራቂዎች የትምህርት ደረጃቸው ዲግሪና ከዚያ በላይ የሆኑ 2074 ኦፊሰሮች መሆናቸውን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ አሳውቀዋል።
ሰልጣኞቹ ለ192 ሰዓታት የንድፈ ሃሳብ ስልጠና እና ለ239 ሰዓታት የወታደራዊ ስልጠና በማካሄድ በድምሩ ለ431 ሰዓታት 2074 ተመራቂ ኦፊሰሮች ስልጠናው በሚፈለገው ዲስፕሊን መሠረት አሰልጥኖ ለምረቃ ብቁ ማድረጉን የኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል እና የኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ፕሬዘዳንት መስፍን አበበ አስታውቀዋል።
ባለስልጣኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ የመፈፀምና የማስፈፀም አቅሙን እያላቀ ከተማ አስተዳደሩ በሚፈልገው ልክ ተልዕኮውን እየተወጣ የሚገኝ ተቋም መሆኑን የገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ክብር ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ሲሆን ትልቅ መሰጠትና ብቃት ለሚጠይቀው የመስክ ስራ እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ አሳስበዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ ከተማችን አዲስ አበባ እያስመዘገበች ባለችው ሁሉን አቀፍ ልማት ለነዋሪዎቿ ምቹ እየሆነች ነው።
ይህንንም ልማት በህግና ደንብ መመራት እንዲችል በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂና በሎጀስቲክ በመደገፍ ላይ እንገኛለን።
ከተማዋ በቀን ብቻ ሳይሆን በምሽትም ጭምር እንቅስቃሴዋ ያልተገደበ እንዲሆን ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሩን በሶስት ሺፍት በማሰማራት ህግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ ለመስራት አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል።
በህዝብ ዘንድ ክብር የሚጎናፀፍ አገልግሎት ለመስጠት በዲሲፕሊን ታንፃችሁ ህዝባችሁን በማሳተፍና በማስተባበር ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ አደራ እያልኩ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ብለዋል።
ዘገባው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍10❤3
ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር አከናወነ
02-10 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት አካሄደ፡፡
የመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ለስድስተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ምርቃት ፕሮግራም በደመቀ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ከስልጠናው ሂደት ጀምሮ እስከ ምርቃት ፕሮግራም መሳካት የበከሉላቸውን ላበረከቱ አካላትና ለመላው የደንብ ማስከበር ሰራተኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
የወርቃማ ሰኞ መድረክ ሳምንቱን ንቁ ሆነን ዉጤታማ ስራ ለማከናወንና በየሳምንቱ ከሰራተኞቻችን ጋር እንደቤተሰብ እየተማማርን መልካም ምኞት በመለዋወጥ እርስ በእርሳችን ምንማማርበት፣ ልምድ የምንለዋወጥበት መሆኑን ገልጸዋል ።
በዕለቱ የባለስልጣኑ የኢንስፔክሽን እና ቁጥጥር ባለሙያ አቶ አባትነህ ውባለም የራሳቸውን የህይወት፣ የትምህርት እና የስራ ተሞክሮና ልምዳቸውን ለሌሎች አስተማሪ በሆነ መልኩ አጋርተዋል።
በተጨማሪም የተቋም ግንባታ ምንነት በሚል ርዕስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ በማቅረብ እውቀት አጋርተዋል ።
ውጤታማ የተቋም ግንባታ የረጅም ጊዜ ስኬትን ለማስመዝገብ፣ አዎንታዊ ግንኙነትን ለመፍጠር እና ለሰራተኞችም ሆነ ለማህበረሰቡ የበለጸገ አከባቢ ለመፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አቶ አባትነህ አስረድተዋል ።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
02-10 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት አካሄደ፡፡
የመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ለስድስተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ምርቃት ፕሮግራም በደመቀ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ከስልጠናው ሂደት ጀምሮ እስከ ምርቃት ፕሮግራም መሳካት የበከሉላቸውን ላበረከቱ አካላትና ለመላው የደንብ ማስከበር ሰራተኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
የወርቃማ ሰኞ መድረክ ሳምንቱን ንቁ ሆነን ዉጤታማ ስራ ለማከናወንና በየሳምንቱ ከሰራተኞቻችን ጋር እንደቤተሰብ እየተማማርን መልካም ምኞት በመለዋወጥ እርስ በእርሳችን ምንማማርበት፣ ልምድ የምንለዋወጥበት መሆኑን ገልጸዋል ።
በዕለቱ የባለስልጣኑ የኢንስፔክሽን እና ቁጥጥር ባለሙያ አቶ አባትነህ ውባለም የራሳቸውን የህይወት፣ የትምህርት እና የስራ ተሞክሮና ልምዳቸውን ለሌሎች አስተማሪ በሆነ መልኩ አጋርተዋል።
በተጨማሪም የተቋም ግንባታ ምንነት በሚል ርዕስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ በማቅረብ እውቀት አጋርተዋል ።
ውጤታማ የተቋም ግንባታ የረጅም ጊዜ ስኬትን ለማስመዝገብ፣ አዎንታዊ ግንኙነትን ለመፍጠር እና ለሰራተኞችም ሆነ ለማህበረሰቡ የበለጸገ አከባቢ ለመፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አቶ አባትነህ አስረድተዋል ።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍7❤4
ብልሹ አሰራርን ለመታገል የተባባሪ አካላት ሚና ጉልህ መሆኑ ተገለጸ
05-10 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከአስራ አንዱም ክ/ከተማ እና ከ119 ወረዳ ብልሹ አሰራርን ለመታገል ለተመለመሉ ተባባሪ አካላት "ብልሹ አሰራርን በጋራ ለመታገል የተባባሪ አካላት ሚና" በሚል መሪ ቃል የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዋጅና በመመሪያ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ከስነ-ምግባር ጉደለትና ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ እንዲያከናውን የተባባሪ አካላት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ ገልጸዋል ።
አክለውም የተቋሙ ሰራተኛና ኦፊሰሩ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ ጥሰትን ፣ የኮሪደር ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅና የወንዝ ዳር ብክለትን በመከላከልና በመቆጣጠር ሂደት ራሱን ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል ።
የስነምግባር ችግር እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የተዘጋጀው የስልጠና ሰነድ በባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ እዬብ ከበደ ቀርቧል።
በሰነዱ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አሁናዊ ያለበት ሁኔታ ፣ ብልሹ አሰራርን ከመታገል አንጻር የተባባሪዎች አካላት ሚና እንዲሁም የስነ-ምግባርና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል መከናወን ያለባቸው ተግባራት በዝርዝር ቀርበዋል።
ተቋማችን ከብልሹ አሰራርና ከስነ ምግባር ጉድለት በጻዳ መልኩ ሰራዎችን ለማከናወንና አንዳንድ ችግር የሚታይባቸውን አካላት ተጠያቂ ለማድረግ የተባባሪ አካላት ሚና ጉልህ እንደመሆኑ ወጥ በሆነ ሁኔታ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አቶ እዬብ አስገንዝበዋል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶ መድረኩ ተጠናቋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
05-10 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከአስራ አንዱም ክ/ከተማ እና ከ119 ወረዳ ብልሹ አሰራርን ለመታገል ለተመለመሉ ተባባሪ አካላት "ብልሹ አሰራርን በጋራ ለመታገል የተባባሪ አካላት ሚና" በሚል መሪ ቃል የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዋጅና በመመሪያ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ከስነ-ምግባር ጉደለትና ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ እንዲያከናውን የተባባሪ አካላት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ ገልጸዋል ።
አክለውም የተቋሙ ሰራተኛና ኦፊሰሩ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ ጥሰትን ፣ የኮሪደር ልማቶችን ደህንነት በመጠበቅና የወንዝ ዳር ብክለትን በመከላከልና በመቆጣጠር ሂደት ራሱን ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል ።
የስነምግባር ችግር እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል የተዘጋጀው የስልጠና ሰነድ በባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ እዬብ ከበደ ቀርቧል።
በሰነዱ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አሁናዊ ያለበት ሁኔታ ፣ ብልሹ አሰራርን ከመታገል አንጻር የተባባሪዎች አካላት ሚና እንዲሁም የስነ-ምግባርና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል መከናወን ያለባቸው ተግባራት በዝርዝር ቀርበዋል።
ተቋማችን ከብልሹ አሰራርና ከስነ ምግባር ጉድለት በጻዳ መልኩ ሰራዎችን ለማከናወንና አንዳንድ ችግር የሚታይባቸውን አካላት ተጠያቂ ለማድረግ የተባባሪ አካላት ሚና ጉልህ እንደመሆኑ ወጥ በሆነ ሁኔታ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አቶ እዬብ አስገንዝበዋል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶ መድረኩ ተጠናቋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
❤2👍1