የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.12K subscribers
1.86K photos
4 videos
1 file
54 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ትስስር ብቻውን ውጤት አይሆንም!
በስሜነህ ደስታ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከተዘጋጀው አምድ የተወሰደ

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ መልክ መደራጀቱን ተከትሎ ባለስልጣኑ በአዋጅ የተሰጠውን ስልጣንና ተግባራት በተሟላ መልኩ ማሳካት ይቻለው ዘንድ የባለ ድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ያምናል፡፡

በትስስር ከተሠሩ ሥራዎች ለአብነት ለመጥቀስ ያህል፣ ከመሬት ልማት ማኔጅመንት ቢሮ ጋር በመቀናጀት በከተማው ውስጥ የሚገኙ መሬቶች ወደ መሬት ባንክ እንዲገቡ በማድረግ በደንብ ተላላፊዎች የሚፈፀሙ መሬት ወረራዎችን የመከላከል እና የመቆጣጠር አቅምን በማሳደግ ውስን የሆነውን የመሬት ሀብት ከደንብ ተላላፊዎች መከላከል ተችሏል፡፡

ከትምህርት ቢሮን ወክለው የመጡት የተቋሙ ሀላፊ ወይዘሮ አበበች የትስስር ስምምነት ተፈራረሞ መቀመጥ ግብ አይሆንም ስለዚህ በቅንጅት በመሥራት አሠራራችን ምን ይመስላል ብሎ መገማገም እንዲሁም መወያየት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

የመማር ማስተማርን የሚያውኩ ንግድ ቤቶች ከትምህርት ቤቶች እንዲርቁ መደረጉ ጥሩ ሆኖ ሳለ ሁለት መቶ ሜትር ብቻ እንዲርቁ መደረጉ የሚያንስ ስለሆነ ችግር እንዳይፈጥር መመሪያው እንደገና ተፈትሾ የሚስካከልበት መንገድ ቢፈለግ በማለት አንስተዋል፡፡

ከንግድ ቢሮ የተሳተፉት የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ መስፍን ባለስልጣኑ ላይ እየታዩ ያሉ ለውጦች በጣም አስገራሚ መሆናቸውን ገልጸው በጋራ የሚሠሩ ሥራዎች በጣም አመርቂ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ ሌሎችም ተሳታፊ ባለድርሻ አካላትም ገንቢ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በውይይቱ መጨረሻም የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተሰጡትን አስተያየቶች እንደግባት በመውሰድ ለቀጣይ ስድስት ወር በተሻለ ሁኔታ ለመተግበር ባለስልጣኑ ተግቶ እንደሚሠራ ቃል በመግባት አስተያየት ሰጥተዋል፡፡
👍1
ህብረተሰቡ እንደሁልጊዜው ለፀጥታ አካላት ሥራ ተባባሪ እዲሆን ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

37ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 44ኛው የሚኒስትሮች ስራ አስፈፃሚ ም/ቤት ስብሰባ በሰላምና በስኬት ለማጠናቀቅ እንዲቻል በሚከናወነው የፀጥታ ስራ እና የትራፊክ ፍሰቱ የተሳለጠ እንዲሆን አሽከርካሪዎች ሌሎች ተለዋጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ጉባኤው ተጀምሮ እስከሚጠናቀ ፡-
• ከፓርላማ መብራት-በውጭ ጉዳይ ሚ/ር - መስቀል አደባባይ ፍላሚንጎ - ኦምሎፒያ - ወሎ ሰፈር - ጃፓን ኤምባሲ -ፍሬንድ ሺፕ -ቦሌ ቀለበት መንገድ -ኤርፖርት
• ከፓርላማ መብራት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር -በብሔራዊ ቤተ - መንግስት -በፍልውሃ - በብሔራዊ ቴአትር- ሜክሲኮ አደባባይ - አፍሪካ ህብረት አዳራሽ ዙሪያ ፡-
• ከፓርላማ መብራት -ብሔራዊ ቤተ-መንግስት - ወዳጅነት ፓርክ - ንግድ ማተሚያ ቤት - ሞናርክ ሆቴል-ቴዎድሮስ አደባባይ-ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል- ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን- ብሔራዊ ቴአትር -ሜክሲኮ አደባባይ - አፍሪካ ህብረት መንገዶቹ እንግዶች ሲያልፉ አሽከርካሪዎችም ሆኑ እግረኞች ለእንግዶቹ ቅድሚያ በመስጠት ተባባሪ እንዲሆኑ እና ሌሎች ተለዋጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ እያሳሰበ ፡-
• ከፓርላማ መብራት-በሸራተን ሆቴል ቁልቁለቱን-ፍልውሃና አምባሳደር ቴአትር
• መረጃ ለመስጠት በስልክ ቁጥር 011-1-11-01-11፣ 011-5-52-63-03 ፣ 011-5-52-40-77 ፣ 011-5-54-36-78 ፣ 011-5-54-36-81 እንዲሁም 987 ፣ 991 እና 916 ነፃ የስልክ መስመሮችን መጠቀም እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆ ለጉባኤው በሰላም መጠናቀቅ መላው ሠላም ወዳድ ህዝባችን ለሚያደርገው ቅን ተባባሪነት ፖሊስ አስቀድሞ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
👏3👍2
37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል፡፡

ጉባዔው "ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣ የሕይወት ዘመን፣ ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት“በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄድ ነው።

በጉባኤው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሳ ፋቂ ማህማት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶችና የሕብረቱ ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል።

የመሪዎቹ ጉባኤ የካቲት 6 እስከ 7 ቀን 2016 ዓ.ም 44ኛው የሕብረቱ የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት በመደበኛ ስብሰባ በተወያየባቸው አጀንዳዎች ላይ በስፋት የሚመክርም ይሆናል።

አህጉራዊ የሰላምና ደህንነት ጉዳይ ንግድና ትስስር፣ ተቋማዊ ማሻሻያዎች፣ ትምህርት፣ ግብርና እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ ሰብዓዊ መብቶች፣ ስርዓተ ጾታና ወጣቶችን ማብቃት እንዲሁም የተቋማትና አደረጃጀቶች ምርጫ ውይይት የሚደረግባቸው ዋነኛ አጀንዳዎች መሆናቸው ተገልጿል።
👍1
በአዲስ አበባ የታንዛንያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊየስ ኔሬሬ መታሰቢያ ሐውልት ቆመላቸው

የካቲት 10/2016 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የመታሰቢያ ሐውልቱ በአፍሪካ ህብረት ውስጥ በሚገኘው የአፍሪካ ሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት ፊት ለፊት መገንባቱ ተጠቅሷል።

“የታንዛንያ አባት” እየተባሉ የሚጠሩት ጁሊየስ ኔሬሬ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት እንዲላቀቁ በነበረው ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚነሱ ሰዎች መካከል ይጠቀሳሉ።

ታንዛንያ (በወቅቱ ታንጋኒካ) ከብሪታኒያ ቅኝ ግዛት እንድትወጣ ታንጋኒካ አፍሪካን ዩኒየን(Tanganyika African Union) የተሰኘ ፓርቲ በማቋቋም ትግል አድርገዋል።

ጁሊየስ ኔሬሬ “ያለ አንድነት አፍሪካ ምንም መጻኢ እድል የላትም” በሚለው ታዋቂ አባባላቸው ይታወቃሉ።

ትግሉም ፍሬ አፍርቶ እ.አ.አ በ1961 ታንዛንያ ከቅኝ ግዛት የወጣች ሲሆን ኔሬሬም እ.አ.አ በ1964 የመጀመሪያው የታንዛንያ ፕሬዝዳንት በመሆን እስከ እ.አ.አ 1985 አገልግለዋል።

ጁሊየስ ኔሬሬ መምህር (ሙዋሊሙ) የሚል ቅጽል ስም ያላቸው ኔሬሬ የፓን አፍሪካኒዝም አቀንቃኝ ነበሩ።

በስነ ስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ ማህማት፣ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር መሐመድ ኦውልድ ጋዙዋኒ፣ የታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን እንዲሁም የተለያዩ የአፍሪካ አገራት መሪዎች፣ የቀጣናዊ ተቋማት የስራ ኃላፊዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
👍3
37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እና 44ኛው የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ በስኬት መጠናቀቁን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታወቀ

AMN-የካቲት 11/2016 ዓ.ም
37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እና 44ኛው የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ በስኬት መጠናቀቁን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማን ሰላምና ደህንነት የበለጠ ለማጠናከር፣ የትራፊክ ፍሰቱን የተሳለጠ ለማድረግ ግብረ-ኃይሉ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከአፍሪካ ህብረት ጽ/ቤት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር በመስራቱ ለተገኘው ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብሏል መግለጫው።

ለጉባኤው የመጡ እንግዶች በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ እጀባና ጥበቃ ማድረጉን የገለፀው የጋራ ግብረ-ኃይሉ መሪዎቹም በሰላም ወደ ሀገራቸው እየተመለሱ መሆናቸውን በመግለጫው አስታውቋል፡፡

መላው የሀገራችን ሕዝብ በተለይም የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች እንግዶችን በክብር ከመቀበል ጀምሮ በየሆቴሎቹ ደረጃውን የጠበቀ መስተንግዶ በማድረግ፣ የሚያልፉባቸው መንገዶች ሲዘጉ በትዕግስት ቅድሚያ ሰጥቶ በማሳለፍ፤ ከፀጥታ ኃይሉ የሚሰጠውን መመሪያ በቅንነት በመቀበል ትብብራቸውንና አጋርነታቸውን በማሳየታቸው፤ የፀጥታና ደህንነት አመራሮችና አባላትም በጥብቅ ዲሲፕሊን እየተመሩ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በመወጣታቸው ጉባኤው ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላምና በስኬት በመጠናቀቁ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይሉ በመግለጫው ላቅ ያለ ምስጋና አቅርቧል፡፡

አዲስ አበባ፣
የካቲት 10 ቀን 2016 ዓ.ም
የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል
👍3🔥1
ባለስልጣኑ ከ 2.2 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች
ገንብቶ በዛሬው እለት ለባለቤቶቹ ቁልፍ አስረከበ።

የካቲት 12/2016 ዓ.ም
*አዲስ አበባ*

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በኮልፌ፣በንፍስ ስልክ፣እና በልደታ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤቶች በጋራ በመሆን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ላይ የ3 አቅመ ደካማ አባዎራዎች 5 ክፍል ቤት በመገንባት በዛሬው ዕለት የባለስልጣኑ የክፍለ ከተማ አመራሮች በተገኙበት አስመረቀ።

የዕለቱን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ክላስተሩን እያስተባበሩ ያሰሩት የኮልፌ ክፍለ ከተማ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ እንዳሉት የተገነባው መኖሪያ ቤት ከ 2.2 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት መሆኑን ገልፀዋል

አቶ አበራ በመክፈቻ ንግግራቸው ባለስልጣኑ በክረምት የጀመረው የሰው ተኮር በጎ ተግባራት በበጋም አጠናክሮ መቀጠሉን እና በዚህ በጎ ተግባር ላይ የተሳተፍ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ኃላፊዎች ፣ ኦፊሰሮች እና ባለሀብቶችን አመስግነዋል ።

አክለውም የደንብ ጥሰቶችን እንዳይከሰት አስቀድሞ የቅድመ መከላከል ስራ በመስራት እና ተከስቶም ሲገኝ አስፈላጊውን እርምጃ እየተወሰደ በዛው ጎን ለጎን በሰው ተኮር ስራዎች የነቃ ተሳትፎ በማድረግ በተለያዩ የበጎ ስራዎች ተቋማችን እንደሚሳተፍ አስታውቀው አሁን ያሰረከብነውን የቤት ግንባታ በመፍጠንና በመፍጠር ላይ ሆነን በአጭር ጊዜ ውስጥ ገንብተን ለቤት ባለቤቶቹ እንዳስረከቡ አስታውቀዋል::

የዕለቱ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎ ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሪት ሀብታሟ ባልቻ እንዳሉት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት በተጨማሪ እንደዚህ አይነት ሰው ተኮር ተግባራት ላይ ሲሳተፍ የመጀመሪያው እንዳልሆነ እና በዛሬው ዕለት ለ 3 አባወራዎች ቤት ገንብቶ ማስረከቡ የሚበረታታ ተግባር ነው ሲሉ ተናግረዋል ።

በዛሬው እለት የቤት ቁልፍ ከተረከቡት የቤት ባለቤቶች አቶ ባዮ ደሜ እንዳሉት ከዚህ ቀደም ክረምት በመጣ ቁጥር በችግር ሲኖሩ እንደነበር ገልፀው አሁን በተደረገለቸው በጎ ተግባር እንደተደሰቱ ገልፀው ለባለስልጣን መስሪያ ቤት እና ተግባሩ ላስተባበሩ አካላት ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በመጨረሻም በስራው ላይ ጉልዕ አስተዋፅኦ ላደረጉ ክፍለ ከተሞች እና ግለሰቦች የምስጋና የምስክር ወረቀትና ስጦታ በማበርከት ለቤቱ ለባለቤቶቹ ቁልፍ በማስረከብ ፕሮግራሙ ተጠናቋል ።

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።

የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement

የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT

የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen

ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ!
ባለስልጣኑ ከ 2.2 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች
ገንብቶ በዛሬው እለት ለባለቤቶቹ ቁልፍ አስረከበ።

የካቲት 12/2016 ዓ.ም
*አዲስ አበባ*

የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በኮልፌ፣በንፍስ ስልክ፣እና በልደታ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤቶች በጋራ በመሆን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ላይ የ3 አቅመ ደካማ አባዎራዎች 5 ክፍል ቤት በመገንባት በዛሬው ዕለት የባለስልጣኑ የክፍለ ከተማ አመራሮች በተገኙበት አስመረቀ።

የዕለቱን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ክላስተሩን እያስተባበሩ ያሰሩት የኮልፌ ክፍለ ከተማ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ እንዳሉት የተገነባው መኖሪያ ቤት ከ 2.2 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት መሆኑን ገልፀዋል።

አክለውም የደንብ ጥሰቶችን እንዳይከሰት አስቀድሞ የቅድመ መከላከል ስራ በመስራት እና ተከስቶም ሲገኝ አስፈላጊውን እርምጃ እየተወሰደ በዛው ጎን ለጎን በተለያዩ የበጎ ስራዎች ተቋማችን እንደሚሳተፍ አስታውቀው አሁን ያሰረከብነውን የቤት ግንባታ በመፍጠንና በመፍጠር ላይ ሆነን በአጭር ጊዜ ውስጥ ገንብተን ለቤት ባለቤቶቹ እንዳስረከቡ አስታውቀዋል።

በዛሬው እለት የቤት ቁልፍ ከተረከቡት የቤት ባለቤቶች አቶ ባዮ ደሜ እንዳሉት ከዚህ ቀደም ክረምት በመጣ ቁጥር በችግር ሲኖሩ እንደነበር ገልፀው አሁን በተደረገለቸው በጎ ተግባር እንደተደሰቱ ገልፀው ለባለስልጣን መስሪያ ቤት እና ተግባሩ ላስተባበሩ አካላት ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በመጨረሻም በስራው ላይ ጉልዕ አስተዋፅኦ ላደረጉ ክፍለ ከተሞች እና ግለሰቦች የምስጋና የምስክር ወረቀትና ስጦታ በማበርከት ለቤቱ ለባለቤቶቹ ቁልፍ በማስረከብ ፕሮግራሙ ተጠናቋል ።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሮክቶሬት ነው።

ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።

የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement

የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT

የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen

ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ
👍3😁1