ባለስላጣኑ በደንብ ቁጥር 179/2017 እና በደንብ ቁጥር 180/2017 ዙርያ ስልጠና ሰጠ
መጋቢት 22/2017ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሰው ኃይል ስምሪት በልዩ ሁኔታ ለማመጣጠን የወጣ የዝውውርና ምደባ ደንብ ቁጥር 179/2017 እና በወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣውን በደንብ ቁጥር 180/2017 ዙርያ ከማዕከል እስከ ወረዳ ላሉ ሰራተኞች በባለስልጣኑ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ስልጠና ሰጥተዋል፡፡
የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው የስልጠናው ዓላማ በወንዝ ዳርቻ ብክለትና እንክብካቤ የወጣውን ደንብ ሀሉም ሰራተኞች በመገንዘብ ለከተማው ህዝብ ያለውን ፋይዳ ተደራሽ ለማድረግ እንዲያስችል እና የሰው ኃይል ውስንነት ያለባቸው ቦታዎችን ተመጣጣኝ የሰው ኃይል እንዲኖራቸው ለማድረግ የወጣውን ደንብ ለይ የሚሰጠውን ስልጠና መሆኑ ገልፀው ሰለጣኞች በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል ፡፡
በወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣውን ደንብ ቁጥር 180/2017 ዙርያ የተዘጋጀ ሰነድ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠና ዳይሬክቶሬት የስልጠና ባለሙያ በአቶ ዮናኤል ለታ አቅርበዋል ።
በሰነዱ የወንዞችና የወንዞች ዳርቻን ስለማልማት፣ወንዝና የወንዝ ዳርቻ ከብክለት ስለመከላከል ፣ስለ ተከለከሉ ተግባራት ፣ ስለ ወንዝና ወንዝ ዳርቻ አስተዳደራዊ ቅጣት በሰፊው ገለፃ ተደርጓል
በሌላ መልኩ የሰው ሀይል ስምሪትን በልዮ ሀኔታ ለማመጣጠን የወጣውን ደንብ ቁጥር 179/2017 ስልጠና የሰጡት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የሰው ሀይል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ይልማ ሲሆኑ በመንግስት መስሪያ ቤቶች የሰው ሃብት ስምሪቱን ለማመጣጠን እንዲቻል የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሰው ሀብት መረጃዎችን ማደራጀት እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
በስልጠናው ከመቶ ስልሳ ፐርሰንት በላይ የሰው ኃይል ከተሟላላቸው ላይ ዝቅተኛ የሰው ኃይል ቁጥር ወዳላቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች በልዩ ሁኔታ በማዛወር ወይም በመመደብ የተሻለ አገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር በማስቻል የተገልጋዩን እርካታ ከፍ ማድረግ እንዲያስችል ደንቡ መደንገጉን አስገንዝበዋል ።
በለስልጠናው ሰለ ደንቡ ጠቅላላ ድንጋጌ፣ ስለ ዝውውርና ምደባ አፈጻጸም፣ ስለ አብይ ኮሚቴ አባላት እና ተግባርና ኃላፊነት፣ በዝውውር አፈጻጸም የሠራተኛ መብቶችንና ግዴታዎች ጨምሮ ዝርዝር ጉዳዮችን ላይ ሰፋ ባለ አቀራረብ ገለጻ አድርገዋል፡፡
ከመድረኩ በሁለቱም ደንብ ቁጥሮች ዙርያ በተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በአሰልጣኞቹ ምላሽ ተሰጥቶበት ስልጠናው ተጠናቋል።
ዘገባው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
መጋቢት 22/2017ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሰው ኃይል ስምሪት በልዩ ሁኔታ ለማመጣጠን የወጣ የዝውውርና ምደባ ደንብ ቁጥር 179/2017 እና በወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣውን በደንብ ቁጥር 180/2017 ዙርያ ከማዕከል እስከ ወረዳ ላሉ ሰራተኞች በባለስልጣኑ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ስልጠና ሰጥተዋል፡፡
የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው የስልጠናው ዓላማ በወንዝ ዳርቻ ብክለትና እንክብካቤ የወጣውን ደንብ ሀሉም ሰራተኞች በመገንዘብ ለከተማው ህዝብ ያለውን ፋይዳ ተደራሽ ለማድረግ እንዲያስችል እና የሰው ኃይል ውስንነት ያለባቸው ቦታዎችን ተመጣጣኝ የሰው ኃይል እንዲኖራቸው ለማድረግ የወጣውን ደንብ ለይ የሚሰጠውን ስልጠና መሆኑ ገልፀው ሰለጣኞች በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል ፡፡
በወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት ለመከላከል የወጣውን ደንብ ቁጥር 180/2017 ዙርያ የተዘጋጀ ሰነድ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስልጠና ዳይሬክቶሬት የስልጠና ባለሙያ በአቶ ዮናኤል ለታ አቅርበዋል ።
በሰነዱ የወንዞችና የወንዞች ዳርቻን ስለማልማት፣ወንዝና የወንዝ ዳርቻ ከብክለት ስለመከላከል ፣ስለ ተከለከሉ ተግባራት ፣ ስለ ወንዝና ወንዝ ዳርቻ አስተዳደራዊ ቅጣት በሰፊው ገለፃ ተደርጓል
በሌላ መልኩ የሰው ሀይል ስምሪትን በልዮ ሀኔታ ለማመጣጠን የወጣውን ደንብ ቁጥር 179/2017 ስልጠና የሰጡት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የሰው ሀይል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ይልማ ሲሆኑ በመንግስት መስሪያ ቤቶች የሰው ሃብት ስምሪቱን ለማመጣጠን እንዲቻል የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሰው ሀብት መረጃዎችን ማደራጀት እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
በስልጠናው ከመቶ ስልሳ ፐርሰንት በላይ የሰው ኃይል ከተሟላላቸው ላይ ዝቅተኛ የሰው ኃይል ቁጥር ወዳላቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች በልዩ ሁኔታ በማዛወር ወይም በመመደብ የተሻለ አገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር በማስቻል የተገልጋዩን እርካታ ከፍ ማድረግ እንዲያስችል ደንቡ መደንገጉን አስገንዝበዋል ።
በለስልጠናው ሰለ ደንቡ ጠቅላላ ድንጋጌ፣ ስለ ዝውውርና ምደባ አፈጻጸም፣ ስለ አብይ ኮሚቴ አባላት እና ተግባርና ኃላፊነት፣ በዝውውር አፈጻጸም የሠራተኛ መብቶችንና ግዴታዎች ጨምሮ ዝርዝር ጉዳዮችን ላይ ሰፋ ባለ አቀራረብ ገለጻ አድርገዋል፡፡
ከመድረኩ በሁለቱም ደንብ ቁጥሮች ዙርያ በተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በአሰልጣኞቹ ምላሽ ተሰጥቶበት ስልጠናው ተጠናቋል።
ዘገባው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ባለስልጣኑ የወንዞችና የወንዞች ዳርቻ ብክለት ለመከላከል የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 አፈጻጸምን ገመገመ
23/07/2027ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በጋራ በመሆን የወንዞችና የወንዞች ዳርቻ ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 አፈጻጸም የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የክ/ከተማ ጽ/ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት አፈጻጸም ሪፓርት በማቅረብ አፈጻጸሙን ገመገመ።
በውይይቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በቅንጅት የመስራት ሂደቱ ያመጣው ውጤት መልካም መሆኑን ጠቅሰው ሪፖርቱን በመጠምገም በቀጣይ በትኩረት መሰራት በሚገባቸው ነጥቦች ግብአት ለመውሰድ መሆኑ ገልፀዋል።
በመድረኩ የወንዝ ዳርቻ ልማትና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ በሳምንት ውስጥ የተሰሩ ተግባራትን አፈፃፀም ሪፖርት ሰነድ በባለስልጣኑ የቁጥጥር እና ኢንሰፔክሽን ባለሙያ አቶ አባትነህ ውባለ ቀርቧል።
በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርት ሰነድ መሠረት ከቤቱ በክፍተት በታዩ እና በቀጣይም መስተካከል የሚገባቸውና ፣ ድጋፍ በሚያስፈልጋቸው ነጥቦች ላይ ሀሳብ፣ አስተያየት እና ጥያቄዎችን በማንሳት ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱ የአዲስ አበባ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ ደንቡን ተግባራዊ ከማድረግ አንጻር የተሄደበት መንገድ ከተጠበቀው በላይ መሆኑን በመግለጽ ጠንካራውን ጎን የበለጠ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል።
አክለውም በቀጣይም ግንዛቤ የማስጨበጥ እና ከሌሎች ከቀሩ ተቋማት ጋር በቅንጅት የመስራት ሂደት ላይ አሁንም ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱ መቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል።
በመጨረሻም በተቋማቱ የበላይ አመራሮች የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
23/07/2027ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በጋራ በመሆን የወንዞችና የወንዞች ዳርቻ ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 አፈጻጸም የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የክ/ከተማ ጽ/ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት አፈጻጸም ሪፓርት በማቅረብ አፈጻጸሙን ገመገመ።
በውይይቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በቅንጅት የመስራት ሂደቱ ያመጣው ውጤት መልካም መሆኑን ጠቅሰው ሪፖርቱን በመጠምገም በቀጣይ በትኩረት መሰራት በሚገባቸው ነጥቦች ግብአት ለመውሰድ መሆኑ ገልፀዋል።
በመድረኩ የወንዝ ዳርቻ ልማትና ብክለት ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ በሳምንት ውስጥ የተሰሩ ተግባራትን አፈፃፀም ሪፖርት ሰነድ በባለስልጣኑ የቁጥጥር እና ኢንሰፔክሽን ባለሙያ አቶ አባትነህ ውባለ ቀርቧል።
በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርት ሰነድ መሠረት ከቤቱ በክፍተት በታዩ እና በቀጣይም መስተካከል የሚገባቸውና ፣ ድጋፍ በሚያስፈልጋቸው ነጥቦች ላይ ሀሳብ፣ አስተያየት እና ጥያቄዎችን በማንሳት ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱ የአዲስ አበባ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ ደንቡን ተግባራዊ ከማድረግ አንጻር የተሄደበት መንገድ ከተጠበቀው በላይ መሆኑን በመግለጽ ጠንካራውን ጎን የበለጠ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል።
አክለውም በቀጣይም ግንዛቤ የማስጨበጥ እና ከሌሎች ከቀሩ ተቋማት ጋር በቅንጅት የመስራት ሂደት ላይ አሁንም ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱ መቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል።
በመጨረሻም በተቋማቱ የበላይ አመራሮች የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ባለስልጣኑ ያልተጣራ ፍሳሽ በመልቀቅ ወንዝን የበከሉ ሁለት ተቋማት እያንዳንዳቸው 1,000,000 ብር በመቅጣት እርምጃ መውሰዱን ገለፀ
24/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በልደታ ክ/ከተማ 2 ፍሳሽን ወደ ወንዝን በመልቀቅ ወንዝ የበከሉ ሁለት ተቋማት እያንዳንዳቸው 1,000,000 ብር በድምሩ 2,000,000/ሁለት ሚሊዮን ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን ገለፀ።
ባለስልጣኑ ቢጂ አይ ኢትዮጲያ እና ሞሀ የለስላሳ መጠጦች ማምረቻ ድርጅቶች የሚለቁት ፍሳሽ በተደረገለት የናሙና ምርመራ ወንዝን የሚበክል መሆኑን የተረጋገጠ ሲሆን በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።
ወንዞችን ከብክለት የፀዱ ከማድረግ አንፃር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በጋራ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎችን በስፋት እየሰጡ መሆኑ ገልፀዋል።
በግንዛቤው መሠረት ተቋማትና ግለሰቦች ከህገወጥ ተግባራቸው ሊቆጠቡ ባለመቻላቸው አስተዳደራዊ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተመላክቷል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን
ለተጨማሪ መረጃ፦
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
24/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በልደታ ክ/ከተማ 2 ፍሳሽን ወደ ወንዝን በመልቀቅ ወንዝ የበከሉ ሁለት ተቋማት እያንዳንዳቸው 1,000,000 ብር በድምሩ 2,000,000/ሁለት ሚሊዮን ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን ገለፀ።
ባለስልጣኑ ቢጂ አይ ኢትዮጲያ እና ሞሀ የለስላሳ መጠጦች ማምረቻ ድርጅቶች የሚለቁት ፍሳሽ በተደረገለት የናሙና ምርመራ ወንዝን የሚበክል መሆኑን የተረጋገጠ ሲሆን በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።
ወንዞችን ከብክለት የፀዱ ከማድረግ አንፃር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በጋራ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎችን በስፋት እየሰጡ መሆኑ ገልፀዋል።
በግንዛቤው መሠረት ተቋማትና ግለሰቦች ከህገወጥ ተግባራቸው ሊቆጠቡ ባለመቻላቸው አስተዳደራዊ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተመላክቷል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን
ለተጨማሪ መረጃ፦
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT