የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.1K subscribers
1.81K photos
4 videos
1 file
53 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
የወንዝ ዳርቻ ልማትን ከማፋጠንና ብክለትን ከመከላከል ጋር ተያይዞ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ

መጋቢት 4/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወንዝ ዳርቻ ልማትን ከማፋጠንና ብክለትን ከመከላከል ጋር ተያይዞ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል።

በክፍለ ከተማው አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት እና በደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አዘጋጅነት በተካሄደው መድረክ አመራሮች፣ የደንብና የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

በዕለቱም በደንብ ቁጥር 180/2017 አሰራርና አደረጃጀት ዙሪያ ማብራሪያ ሰነድ ቀርቦ ከተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት ተሰጥቶበታል።

የክፍለ ከተማው ምክትል ስራ አስፈጻሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ድላየሁ ታምሬ የዲፕሎማሲና የቱሪዝም ከተማ የሆነችውን አዲስ አበባ ወንዞቿን ማልማትና ከብክለት መጠበቅ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል።

አቶ ድላየሁ አክለውም ወንዞችን ከኮሪደር ልማቱ ጋር በማቀናጀት ለልማትና ለመዝናኛነት ማዋል አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።

የክፍለ ከተማው አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስፋው ፋራህ በበኩላቸው የአካባቢ ብክለትን በመከላከል የከተማዋ ወንዞችን በጋራ በማልማት የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል።

የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ አለሙ እንደገለፁት ህግና ስርዓትን በማስከበር፣ ግንዛቤ በመፍጠር እንዲሁም ህጋዊ እርምጃ በመውሰድ ወንዞችን ከብክለት ለመጠበቅ በቅንጅት መስራት አለብን ብለዋል።
👍51
ባለስልጣኑ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ በሚበክሉ አካላት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ መቀጠሉን ገለጸ

04/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት በዛሬው እለት 5,775,000/አምስት ሚሊየን ሰባት መቶ ሰባ አምስት ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡

ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 1,595,000 ብር፣ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ 1,150,000 ብር፣በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ 1,050,000 ብር ፤በአራዳ ክፍለ ከተማ 650,000 ብር፣አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 640,000 ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።

በተያያዘ ዜና በቦሌ ክ/ከተማ 300,000 ብር ፤በአቃቂ ክ/ከተማ 300,000 ብር በልደታ ክፍለ ከተማ 70,000 ብር ፣በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ 20,000 ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።

ባለስልጣኑ በአጠቃላይ በዛሬው እለት 27 ድርጅቶች እና 15 ግለሰቦች በመቅጣት በድምሩ 5,775,000/አምስት ሚሊየን ሰባት መቶ ሰባ አምስት ሺህ/ ብር በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ማድረጉን ገልጿል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍9👏65
ባለስልጣኑ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ በሚበክሉ አካላትን ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አስጠነቀቀ

05/07/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በዛሬው እለትም በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት 3,176,000/ሶስት ሚሊየን አንድ መቶ ሰባ አምስት ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡

ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ 800,000 ብር፣ በልደታ ክፍለ ከተማ 750,000 ብር፣በነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 426,000 ብር ፤በቦሌ ክፍለ ከተማ 300,000 ብር፣አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 300,000 ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።

በተያያዘ ዜና በኮልፌ ክ/ከተማ 300,000 ብር ፤በአቃቂ ክ/ከተማ 300,000 ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።

በአጠቃላይ በዛሬው እለት 7 ድርጅቶች እና 5 ግለሰቦችን በመቅጣት በድምሩ 3,176,000/ሶስት ሚሊየን አንድ መቶ ሰባ አምስት ሺህ/ ብር በመቅጣት ለመንግስት ገቢ መደረጉን ተገልጿል።

ባለስልጣኑ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ በሚበክሉ አካላትን ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ያስጠነቀቀ ሲሆን ድርጊቱን በሚፈጽሙ አካላት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👏11👍21
የሀዘን መግለጫ

የአዲስ አበበ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ 11 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሃላፊ በነበሩት በወ/ሮ መሰሉ ገ/ወልድ ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።

ባለስልጣኑ ለቤተሰባቸው ፣ለስራ ባልደረቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን ይመኛል።

የቀብር ስነ-ስርዓታቸው በዛሬው እለት በቅዱስ ዮሴፍ ቤተ-ክርስቲያን ከቀኑ 6 ሰዓት የሚፈጸም
ይሆናል።
😭11👎2