የደንብ መተላለፍን በመቀነስ የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገበው ክፍለ ከተማ ልምዱን አጋራ
27/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
ባለስልጣኑ በ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ክፍለ ከተሞች 25% የደንብ ጥሰትን እንዲቀንሱ ያወረደውን መሪ እቅድ 50.4% በመቀነስ 100% አስመዝግቦ ውጤታማ የሆነው የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት ልምዱን ለሌሎች ክፍለ ከተሞች አጋርቷል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተመራው የልምድ ልውውጥ ልዑካን ቡድን የተቋሙን ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የማዕከል ዳይሬክተሮችና የ11ዱንም ክፍለ ከተማ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኜ ሂርጳሳ የልምድ ልውውጥ ልዑካን ቡድኑን የጽ/ቤታቸው፣የአመራራቸውና የሰራተኛው ቅንጅታዊ አሰራር ልምድና ተሞክሯቸውን በዝርዝር አስቃኝተዋል።
ስትራቴጂካዊ የሆነ የአመራር ስልትን በመንደፍ ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ ድረስ ስራዎችን በቅንጅት መምራት በመቻሉ የደንብ ጥሰትን ከእቅዱ በላይ ለመቀነስ ማስቻሉን አቶ ዳኜ አስገንዝበዋል።
በተለይ የቁጥጥርና ኢኒስፔክሽን፣ የቅድመ መከላከልና የግብረ-ኃይል ቡድኑ እስከ ወረዳ ድረስ ባደረገው ጥልቅ ድጋፍና ክትትል ዘጠኙንም የደንብ መተላለፎች ላይ አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።
የተሰሩ ስራዎችንም የካይዘን ፍልስፍናን ተግባራዊ በማድረግ መረጃዎችን በማጥራት፣ ማደራጀት፣ ማንፃት፣ ማቀናጀትና ማዝለቅ የተቻለ መሆኑን በልምድ ልውውጡ ተመላክቷል።
የልምድ ልውውጡ ተሳታፊ አካላትም ክፍለ ከተማው በ2017 ግማሽ ዓመት ቀዳሚ እንዲሆን ያበቃውን አፈፃፀም በአካል ወርደን በማየታችን ውጤቱ የሚገባውና እኛም በርካታ ልምዶችን የቀሰምንበት ነው በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ጽ/ቤቱ በሪፎርም ስራም በክፍለ ከተማው ካሉ 36 ሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር ተወዳድሮ በአንደኛነት ማጠናቀቁ በእርግጥም ሌሎች ክፍለ ከተሞች ልምዱን በመቅሰም የተቋሙን ራዕይ እውን ለማድረግ የሚያስችል ቁመና ላይ እንደሚገኝ ማሳያ መሆኑን የገለፁት የልምድ ልውውጥ ቡድኑን የመሩት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልፀዋል።
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የተገኘውን ሁሉን አቀፍ የላቀ አፈፃፀም ጠምሮ በመቀመር ከማዕከል እስከ ወረዳ ብሎም ሌሎች የከተማ አስተዳደሩና የክልል ከተማ ተቋማት ጭምር እንዲጋሩት ማድረግ እንደሚገባ ዋና ስራ አስኪያጁ በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
27/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
ባለስልጣኑ በ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ክፍለ ከተሞች 25% የደንብ ጥሰትን እንዲቀንሱ ያወረደውን መሪ እቅድ 50.4% በመቀነስ 100% አስመዝግቦ ውጤታማ የሆነው የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት ልምዱን ለሌሎች ክፍለ ከተሞች አጋርቷል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተመራው የልምድ ልውውጥ ልዑካን ቡድን የተቋሙን ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የማዕከል ዳይሬክተሮችና የ11ዱንም ክፍለ ከተማ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኜ ሂርጳሳ የልምድ ልውውጥ ልዑካን ቡድኑን የጽ/ቤታቸው፣የአመራራቸውና የሰራተኛው ቅንጅታዊ አሰራር ልምድና ተሞክሯቸውን በዝርዝር አስቃኝተዋል።
ስትራቴጂካዊ የሆነ የአመራር ስልትን በመንደፍ ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ ድረስ ስራዎችን በቅንጅት መምራት በመቻሉ የደንብ ጥሰትን ከእቅዱ በላይ ለመቀነስ ማስቻሉን አቶ ዳኜ አስገንዝበዋል።
በተለይ የቁጥጥርና ኢኒስፔክሽን፣ የቅድመ መከላከልና የግብረ-ኃይል ቡድኑ እስከ ወረዳ ድረስ ባደረገው ጥልቅ ድጋፍና ክትትል ዘጠኙንም የደንብ መተላለፎች ላይ አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።
የተሰሩ ስራዎችንም የካይዘን ፍልስፍናን ተግባራዊ በማድረግ መረጃዎችን በማጥራት፣ ማደራጀት፣ ማንፃት፣ ማቀናጀትና ማዝለቅ የተቻለ መሆኑን በልምድ ልውውጡ ተመላክቷል።
የልምድ ልውውጡ ተሳታፊ አካላትም ክፍለ ከተማው በ2017 ግማሽ ዓመት ቀዳሚ እንዲሆን ያበቃውን አፈፃፀም በአካል ወርደን በማየታችን ውጤቱ የሚገባውና እኛም በርካታ ልምዶችን የቀሰምንበት ነው በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ጽ/ቤቱ በሪፎርም ስራም በክፍለ ከተማው ካሉ 36 ሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር ተወዳድሮ በአንደኛነት ማጠናቀቁ በእርግጥም ሌሎች ክፍለ ከተሞች ልምዱን በመቅሰም የተቋሙን ራዕይ እውን ለማድረግ የሚያስችል ቁመና ላይ እንደሚገኝ ማሳያ መሆኑን የገለፁት የልምድ ልውውጥ ቡድኑን የመሩት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልፀዋል።
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የተገኘውን ሁሉን አቀፍ የላቀ አፈፃፀም ጠምሮ በመቀመር ከማዕከል እስከ ወረዳ ብሎም ሌሎች የከተማ አስተዳደሩና የክልል ከተማ ተቋማት ጭምር እንዲጋሩት ማድረግ እንደሚገባ ዋና ስራ አስኪያጁ በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍3
ፍሳሽ ቆሻሻን በመልቀቅ ወንዝ የበከለ ድርጅት 300 ሺህ ብር ተቀጣ
28/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመቀናጀት በዛሬው ዕለት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ይህን ደንብ ተላልፎ በተገኘ ቫይብስ ሆቴልና ስፓ/Vibes Hotel & Spa/ ድርጅት ላይ በደንብ ቁጥር 180/17 የቅጣት ሰንጠረዥ 1 ተራ ቁጥር 3 ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀ ድርጅት 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በተደደጋጋሚ በመገናኛ ብዙኃንና በመድረኮች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ፈጥሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ በጀት በመመደብ ከተማዋን ውብ ጽዱና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የወንዝ ዳርቻና የኮሪደር ልማት 7/24 በመስራት የወንዞች ዳርቻ የማስዋብ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።
ህብረተሰቡም መንግስት ከፍተኛ ወጪ አውጥቶ ያለማቸውን ሀብቶች እንዲንከባከብና ደንብ ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲገኝ በ9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን አቅርቧል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ በየትኛውም የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ዙሪያ የሚደረጉ የደንብ መተላለፎችን እንደማይታገስና እርምጃውንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
28/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመቀናጀት በዛሬው ዕለት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ይህን ደንብ ተላልፎ በተገኘ ቫይብስ ሆቴልና ስፓ/Vibes Hotel & Spa/ ድርጅት ላይ በደንብ ቁጥር 180/17 የቅጣት ሰንጠረዥ 1 ተራ ቁጥር 3 ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀ ድርጅት 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በተደደጋጋሚ በመገናኛ ብዙኃንና በመድረኮች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ፈጥሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ በጀት በመመደብ ከተማዋን ውብ ጽዱና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የወንዝ ዳርቻና የኮሪደር ልማት 7/24 በመስራት የወንዞች ዳርቻ የማስዋብ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።
ህብረተሰቡም መንግስት ከፍተኛ ወጪ አውጥቶ ያለማቸውን ሀብቶች እንዲንከባከብና ደንብ ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲገኝ በ9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን አቅርቧል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ በየትኛውም የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ዙሪያ የሚደረጉ የደንብ መተላለፎችን እንደማይታገስና እርምጃውንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍6
ግንፍሌ ወንዝ ውስጥ ቆሻሻ የጣለው ድርጅት 100 ሺህ ብር ተቀጣ
28/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ግንፍሌ ወንዝ ውስጥ ቆሻሻ የጣለው የኢትጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጠቅላይ ቤተክነት የሠንበት ት/ቤት ማደራጃና መምሪያ የማህበረ ቅዱሳን ተቋም በከተማ አስተዳደሩ የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 በመተላለፍ ደረቅ ቆሻሻን ወደ ወንዝ በመጣሉ 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር ተቀጥቷል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በተደደጋጋሚ በመገናኛ ብዙኃንና በመድረኮች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠሩ ይታወሳል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ዙሪያ ደንብ የሚተላለፉ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ
28/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ግንፍሌ ወንዝ ውስጥ ቆሻሻ የጣለው የኢትጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጠቅላይ ቤተክነት የሠንበት ት/ቤት ማደራጃና መምሪያ የማህበረ ቅዱሳን ተቋም በከተማ አስተዳደሩ የወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 በመተላለፍ ደረቅ ቆሻሻን ወደ ወንዝ በመጣሉ 100,000/አንድ መቶ ሺህ/ ብር ተቀጥቷል።
ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በተደደጋጋሚ በመገናኛ ብዙኃንና በመድረኮች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠሩ ይታወሳል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ዙሪያ ደንብ የሚተላለፉ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ
👏5👍3❤2👎1