ባለስልጣኑ በከተማው የልማት ኮሪደር አስፓልት በቸልተኝነት የደንብ መተላለፍ የፈጸመ ድርጅት 300 ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
የካቲት 17/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ዩኒቲ ሀውሲንግ የተባለ የህንፃ ግንባታ ድርጅት በኮሪደር ልማት በተሠራ እስፓልት ላይ ሃላፊነት በጎደለው ሁኔታ በማቆሸሹ በደንብ ማስከበር ባለስልጣን አፊሠሮች 300,000 /ሦስት መቶ ሺህ/ ብር መቀጣቱ ተገለፀ።
ድርጅቱ በተደጋጋሚ ግንዛቤ ተፈጥሮለት ከዚህ በፊት 100 ሺህ ብር የተቀጣ ሲሆን ድጋሚ ተመመሳሳይ ጥፋት በመፈጸሙ የቅጣቱ እጥፍ 200 ሺህ ብር በድምሩ 300,000 /ሦስት መቶ ሺህ/ ብር ተቀጥቶ ያቆሸሸውን ቦታ እንዲያፀዳ ተደርጓል ።
የከተማ አስተዳደሩ የልማት ኮሪደር ስራዋች አዲስ አበባን ውብ ጽዱ በማድረግ የከተማዉ ህዝብ እንዲጠቀምበት ፣የቱርስት መስህብና ከተማው ሌሎች በአለማችን የሚገኙ ከተሞች የደረሱበትን ዕድገት ደረጃ ለማድረስ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሌት ተቀን 7/24 በመሥራት ለህዝብ አገልግሎት በማዋል ህብረተሰቡ ተጠቃሚ ማድረጉ ይታወቃል።
የአዲስ አበባ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በደንብ ተላላፊዎች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ በመግለጽ ልማት ወዳዱ የከተማችን ነዋሪዎች አጥፊዎችን መረጃ በመስጠት የጀመረውን ጥቆማ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አቅርቧል።
መረጃው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
የካቲት 17/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ዩኒቲ ሀውሲንግ የተባለ የህንፃ ግንባታ ድርጅት በኮሪደር ልማት በተሠራ እስፓልት ላይ ሃላፊነት በጎደለው ሁኔታ በማቆሸሹ በደንብ ማስከበር ባለስልጣን አፊሠሮች 300,000 /ሦስት መቶ ሺህ/ ብር መቀጣቱ ተገለፀ።
ድርጅቱ በተደጋጋሚ ግንዛቤ ተፈጥሮለት ከዚህ በፊት 100 ሺህ ብር የተቀጣ ሲሆን ድጋሚ ተመመሳሳይ ጥፋት በመፈጸሙ የቅጣቱ እጥፍ 200 ሺህ ብር በድምሩ 300,000 /ሦስት መቶ ሺህ/ ብር ተቀጥቶ ያቆሸሸውን ቦታ እንዲያፀዳ ተደርጓል ።
የከተማ አስተዳደሩ የልማት ኮሪደር ስራዋች አዲስ አበባን ውብ ጽዱ በማድረግ የከተማዉ ህዝብ እንዲጠቀምበት ፣የቱርስት መስህብና ከተማው ሌሎች በአለማችን የሚገኙ ከተሞች የደረሱበትን ዕድገት ደረጃ ለማድረስ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሌት ተቀን 7/24 በመሥራት ለህዝብ አገልግሎት በማዋል ህብረተሰቡ ተጠቃሚ ማድረጉ ይታወቃል።
የአዲስ አበባ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በደንብ ተላላፊዎች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ በመግለጽ ልማት ወዳዱ የከተማችን ነዋሪዎች አጥፊዎችን መረጃ በመስጠት የጀመረውን ጥቆማ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አቅርቧል።
መረጃው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍7❤1🕊1
በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራዎችን ለማከናወን የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
18/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ ***
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር ለባለስልጣኑ የማዕከል ሰራተኞች የመስክ ማስተዳደር ስርዓት/ Field managements system/ በሚል የስልጠና ርዕሰ የሚሰጠው ስልጠና ሜክሲኮ በሚገኘው በተግባረዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መሰጠት ጀመረ።
ስልጠናውን ያስጀመሩት የባለስልጣኑ የስልጠና ዳይሬክተር ወ/ሮ ላቀች ሀይሌ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ በመገኘት ስራዎችን በቴክኖሎጂ ለማሳለጥ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዕውቀት መገንባት ወሳኝ ስለሆን ስልጠናው ይህንን ክፍተት የሚሞላ መሆኑን ገልፀዋል።
ስልጠናዉ ከኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ በመጡ በአቶ ሀብታሙ ጴጥሮስ Field mangement system (FMS) እና በአቶ አማኑኤል መኮንን file mangement system (FMS) ዙሪያ ለሁለት ቀናት እንደሚሰጥ ተገልፆ በተግባር የታገዘ ስልጠና እንደሆነ አስታውቀዋል።
ዘገባው የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነዉ።
18/06/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ ***
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር ለባለስልጣኑ የማዕከል ሰራተኞች የመስክ ማስተዳደር ስርዓት/ Field managements system/ በሚል የስልጠና ርዕሰ የሚሰጠው ስልጠና ሜክሲኮ በሚገኘው በተግባረዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መሰጠት ጀመረ።
ስልጠናውን ያስጀመሩት የባለስልጣኑ የስልጠና ዳይሬክተር ወ/ሮ ላቀች ሀይሌ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ በመገኘት ስራዎችን በቴክኖሎጂ ለማሳለጥ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዕውቀት መገንባት ወሳኝ ስለሆን ስልጠናው ይህንን ክፍተት የሚሞላ መሆኑን ገልፀዋል።
ስልጠናዉ ከኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ በመጡ በአቶ ሀብታሙ ጴጥሮስ Field mangement system (FMS) እና በአቶ አማኑኤል መኮንን file mangement system (FMS) ዙሪያ ለሁለት ቀናት እንደሚሰጥ ተገልፆ በተግባር የታገዘ ስልጠና እንደሆነ አስታውቀዋል።
ዘገባው የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነዉ።
👍18
የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት በ6 ወር የሥራ አፈፃፀም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት እውቅና ሰጠ
የካቲት 18-2017 ዓ.ም
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር አስተዳደር ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት በ6 ወር የሥራ አፈፃፀም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተቋማት ፣ወረዳዎችና ፈፃሚዎች የእውቅና የምስጋና ፕሮግራም አካሄዷል፡፡
በበጀት ዓመቱ 6 ወራት ውስጥ ህገ ወጥ የመሬት ወረራ፣ ህገ ወጥ ንግድ፣ ያለ ፈቃድ ማስታወቂያ መለጠፍ፣ ህገ ወጥ እርድ እንዲሁም አዋኪ ድርጊቶችን ህግና አሰራር በጠበቀ መንገድ አስተማሪ እርምጃ በመወስድ የከተማዋን ብሎም የክ/ከተማችንን ህግና ስርዓትን በማስፈን የህብረተሰቡን በሁሉ አቀፍ የተረጋጋ እንቅስቃሴ እንዲኖር ማድረግ መቻሉን የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ ደጀኔ ነጋሮ ገልፀዋል፡፡
በመድርኩ ተሳታፊዎች ሀሳብ አስተያየት እንዲሁም ጥያቄዎች አንስተው ከመድረክ መሪው በቂ ምላሽ ተሰቶበት በቀሩት ሥራዎች በቀጣይ የሚሰራ መሆኑን መግባባት ላይ ተደረሷል፡፡
በ6 ወር የሥራ አፈፃፀም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎች የእውቅና የተሰጠ ሲሆን በዚህም መሠረት፡-
1ኛ ወረዳ 1 ደንብ ማስከበር አስተዳደር ጽ/ቤት
2ኛ የወረዳ 4 ደንብ ማስከበር አስተዳደር ጽ/ቤት
3ኛ የወረዳ-10 ደንብ ማስከበር አስተዳደር ጽ/ቤት በመወጣት ዋንጫና ሠርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል፡፡
የካቲት 18-2017 ዓ.ም
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር አስተዳደር ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት በ6 ወር የሥራ አፈፃፀም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተቋማት ፣ወረዳዎችና ፈፃሚዎች የእውቅና የምስጋና ፕሮግራም አካሄዷል፡፡
በበጀት ዓመቱ 6 ወራት ውስጥ ህገ ወጥ የመሬት ወረራ፣ ህገ ወጥ ንግድ፣ ያለ ፈቃድ ማስታወቂያ መለጠፍ፣ ህገ ወጥ እርድ እንዲሁም አዋኪ ድርጊቶችን ህግና አሰራር በጠበቀ መንገድ አስተማሪ እርምጃ በመወስድ የከተማዋን ብሎም የክ/ከተማችንን ህግና ስርዓትን በማስፈን የህብረተሰቡን በሁሉ አቀፍ የተረጋጋ እንቅስቃሴ እንዲኖር ማድረግ መቻሉን የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ ደጀኔ ነጋሮ ገልፀዋል፡፡
በመድርኩ ተሳታፊዎች ሀሳብ አስተያየት እንዲሁም ጥያቄዎች አንስተው ከመድረክ መሪው በቂ ምላሽ ተሰቶበት በቀሩት ሥራዎች በቀጣይ የሚሰራ መሆኑን መግባባት ላይ ተደረሷል፡፡
በ6 ወር የሥራ አፈፃፀም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎች የእውቅና የተሰጠ ሲሆን በዚህም መሠረት፡-
1ኛ ወረዳ 1 ደንብ ማስከበር አስተዳደር ጽ/ቤት
2ኛ የወረዳ 4 ደንብ ማስከበር አስተዳደር ጽ/ቤት
3ኛ የወረዳ-10 ደንብ ማስከበር አስተዳደር ጽ/ቤት በመወጣት ዋንጫና ሠርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል፡፡
👍6
ፕሬስ ሪሊዝ
የወንዝ ዳርቻ ልማትን ከብክለት በሚከላከል ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ግንዛቤ ሊሰጥ ነው።
19/06/2017 ዓ.ም
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር "የወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል" በሚል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ነገ ሀሙስ በ20/06/2017 ዓ.ም ጉርድ ሾላ በሚገኘው አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ቢሮ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ግንዛቤ እንሚፈጠር የባለስልጣኑ ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ አስታወቁ።
በግንዛቤ ስልጠናው ላይ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የቅድመ መከላከልና መስክ ክትትል፣ ቁጥጥር ኦፊሰሮች የባለስልጣኑ ባለሙያዎች፣ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ስልጠናው ተሳታፊዎች እንደሚሆኑ አቶ የምስራች ገልፀዋል።
በቀጣይም ለከተማው ህብረተሰብ፣ ለባለድርሻ አካላት፣ ለአደረጃጀቶችና በጎ ፈቃደኞች ስለ ደንቡ ግንዛቤዎች በስፋት እንደሚፈጠር ጠቁመዋል።
ጥቆማው ፦ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
የወንዝ ዳርቻ ልማትን ከብክለት በሚከላከል ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ግንዛቤ ሊሰጥ ነው።
19/06/2017 ዓ.ም
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር "የወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል" በሚል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ነገ ሀሙስ በ20/06/2017 ዓ.ም ጉርድ ሾላ በሚገኘው አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ቢሮ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ግንዛቤ እንሚፈጠር የባለስልጣኑ ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ አስታወቁ።
በግንዛቤ ስልጠናው ላይ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የቅድመ መከላከልና መስክ ክትትል፣ ቁጥጥር ኦፊሰሮች የባለስልጣኑ ባለሙያዎች፣ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ስልጠናው ተሳታፊዎች እንደሚሆኑ አቶ የምስራች ገልፀዋል።
በቀጣይም ለከተማው ህብረተሰብ፣ ለባለድርሻ አካላት፣ ለአደረጃጀቶችና በጎ ፈቃደኞች ስለ ደንቡ ግንዛቤዎች በስፋት እንደሚፈጠር ጠቁመዋል።
ጥቆማው ፦ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍11
ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ስልታዊና ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ
የካቲት 19/2017 ዓ.ም
**አዲስ አባባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በስነ-ምግባር፣ ፀረ-ሙስና እና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
በስልጠናው በሙስና መከላከል ስነ- ምግባራዊ አመራር፣ በጥቅም ግጭት እና አስቸኳይ ሙስና መከላከል ስልታዊና ቅንጅታዊ አሰራር ዙሪያ ሲሆን በፀረ-ሙስናና ብልሹ አሰራሮች የቀጣይ እቅዶችን ዙሪያ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ስልጠናውን የሰጡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና የፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ተቋሙ በሰጠው ስልጠናና ግንዛቤ መሠረት በቀጣይ የስነ-ምግባር ችግር በሚታይባቸው ሰራተኞች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በስልጠናው የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ኮማንደር ግርማ ሰንበቶ እንደተናገሩት ኦፊሰሩን ከብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የተሰጠዉን ተልዕኮ ከዳር ማድረስ እንዳለበት ገልጸዋል።
አክለውም ኦፊሰሩ ሙስናን በመከላከል በኩል ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው በመግለጽ ኦፊሰሩ በሚሰጡ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እውቀት በመጨመር ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ስልታዊና ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል።
በስልጠናው ላይ የክፍለ ከተማውና የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ባለሙያ፣ ተባባሪ አካላትና አጠቃላይ ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።
የካቲት 19/2017 ዓ.ም
**አዲስ አባባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በስነ-ምግባር፣ ፀረ-ሙስና እና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
በስልጠናው በሙስና መከላከል ስነ- ምግባራዊ አመራር፣ በጥቅም ግጭት እና አስቸኳይ ሙስና መከላከል ስልታዊና ቅንጅታዊ አሰራር ዙሪያ ሲሆን በፀረ-ሙስናና ብልሹ አሰራሮች የቀጣይ እቅዶችን ዙሪያ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ስልጠናውን የሰጡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና የፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ተቋሙ በሰጠው ስልጠናና ግንዛቤ መሠረት በቀጣይ የስነ-ምግባር ችግር በሚታይባቸው ሰራተኞች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በስልጠናው የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ኮማንደር ግርማ ሰንበቶ እንደተናገሩት ኦፊሰሩን ከብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የተሰጠዉን ተልዕኮ ከዳር ማድረስ እንዳለበት ገልጸዋል።
አክለውም ኦፊሰሩ ሙስናን በመከላከል በኩል ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው በመግለጽ ኦፊሰሩ በሚሰጡ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እውቀት በመጨመር ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ስልታዊና ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል።
በስልጠናው ላይ የክፍለ ከተማውና የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ባለሙያ፣ ተባባሪ አካላትና አጠቃላይ ኦፊሰሮች ተገኝተዋል።
👍3