የየተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡና የአደባባይ በዓላት ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበር አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና የምስጋና ፕሮግራም ተካሄደ
24/05/2017ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም በመጀመሪያ ግማሽ አመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡና የአደባባይ በዓላት ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበር አስተዋፅኦ ላበረከቱ ለባለድርሻ አካላት እና የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎችና የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እውቅናና የምስጋና ፕሮግራም የባለስልጣኑና የክፍለ ከተማው አመራሮች በተገኙበት የእውቅናና ምስጋና እና ፕሮግራም ተካሂዷል።
በመረሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈሪ እንደገለፁት፣ የባለስልጣኑን የውስጥ አሰራሮች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው አመራሩና ኦፊሰሩ በሰራው ጠንካራ ስራ የደንብ ጥሰት ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነፃፀር በከተማዋ 58 በመቶ ቀንሷል ብለዋል።
ተቋሙን በቴክኖሎጂ፣ በሰው ሀይል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ናቸው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሀላፊ ኮማንደር ግርማ ሰንበቱ በበኩላቸው የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም በመጀመሪያ ግማሽ አመት ከ6 ሚሊየን ብር በላይ በቅጣት እና በጨረታ ገቢ ማድረጉን ገልፀው ባሳለፍነው አመት ተመሳሳይ ወቅት የተገኘው 3 ሚሊዮን ብር እንደነበር አስታውሰዋል።
ሀላፊው በተያዘው በጀት አመቱ 6ወራት የደንብ መተላለፎች በብቃት በመከላከል እና በመቆጣጠር የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ወረዳዎች እና የተከበሩ በአላትን/የኢሬቻ፣ መስቀል እና ጥምቀት/ ያለምንም የፀጥታ ችግር ተከብሮ እንዲያልቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለ ድርሻ አካላት እና የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እውቅና መስጠት የቀጣይ ስራችን ላይ ተነሳሽነት እንደሚፈጥር ገልጿል።
በእውቅና እና ሽልማቱን ፕሮግራሙ ወረዳ1፣ወረዳ10 እና ወረዳ 8 ከ1ኛ እስከ 3ኛ በመውጣት እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
24/05/2017ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም በመጀመሪያ ግማሽ አመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡና የአደባባይ በዓላት ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበር አስተዋፅኦ ላበረከቱ ለባለድርሻ አካላት እና የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎችና የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እውቅናና የምስጋና ፕሮግራም የባለስልጣኑና የክፍለ ከተማው አመራሮች በተገኙበት የእውቅናና ምስጋና እና ፕሮግራም ተካሂዷል።
በመረሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈሪ እንደገለፁት፣ የባለስልጣኑን የውስጥ አሰራሮች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው አመራሩና ኦፊሰሩ በሰራው ጠንካራ ስራ የደንብ ጥሰት ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነፃፀር በከተማዋ 58 በመቶ ቀንሷል ብለዋል።
ተቋሙን በቴክኖሎጂ፣ በሰው ሀይል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ናቸው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሀላፊ ኮማንደር ግርማ ሰንበቱ በበኩላቸው የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም በመጀመሪያ ግማሽ አመት ከ6 ሚሊየን ብር በላይ በቅጣት እና በጨረታ ገቢ ማድረጉን ገልፀው ባሳለፍነው አመት ተመሳሳይ ወቅት የተገኘው 3 ሚሊዮን ብር እንደነበር አስታውሰዋል።
ሀላፊው በተያዘው በጀት አመቱ 6ወራት የደንብ መተላለፎች በብቃት በመከላከል እና በመቆጣጠር የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ወረዳዎች እና የተከበሩ በአላትን/የኢሬቻ፣ መስቀል እና ጥምቀት/ ያለምንም የፀጥታ ችግር ተከብሮ እንዲያልቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለ ድርሻ አካላት እና የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እውቅና መስጠት የቀጣይ ስራችን ላይ ተነሳሽነት እንደሚፈጥር ገልጿል።
በእውቅና እና ሽልማቱን ፕሮግራሙ ወረዳ1፣ወረዳ10 እና ወረዳ 8 ከ1ኛ እስከ 3ኛ በመውጣት እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍3👏1
ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር አከናወነ።
26-05 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም ተካሄደ
የመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ንቁ በሆነ መንፈስ ሳምንቱን በጥሩ ሁኔታ ዉጤታማ ስራ ለማከናወንና በየሳምንቱ ከሰራተኞቻችን ጋር እንደቤተሰብ እየተማማርን እና እየተመካከርን ሳምንቱ ሙሉ ወርቃማ እንዲሆንልን መልካም ምኞት በመለዋወጥ እርስ በእርሳችን የምንመካከርበት፣ የምንማማርበት፣ ልምድ የምንለዋወጥበት መድረክ መሆኑን ገልጸዋል ።
በዕለቱ የባለስልጣኑ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ላቀች ሀይሌ የራሳቸውን የህይወትና የትምህርት እና የስራ ተሞክሮና ልምዳቸውን ለሌሎች አስተማሪ በሆነ መልኩ አጋርተዋል።
ራስን ሁል ጊዜ በዕውቀት ማዳበር ፣ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ጋር መልካም ግንኙኘት መኖር ፣ለባለሙያ ልምድን ማጋራት እና ስራን በትብብር ፣ በአንድነት እና ዝቅ ብሎ መስራት ዉጤታማ እንደሚያደርግ በመድረኩ ገልጸዋል ፡፡
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
26-05 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም ተካሄደ
የመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ንቁ በሆነ መንፈስ ሳምንቱን በጥሩ ሁኔታ ዉጤታማ ስራ ለማከናወንና በየሳምንቱ ከሰራተኞቻችን ጋር እንደቤተሰብ እየተማማርን እና እየተመካከርን ሳምንቱ ሙሉ ወርቃማ እንዲሆንልን መልካም ምኞት በመለዋወጥ እርስ በእርሳችን የምንመካከርበት፣ የምንማማርበት፣ ልምድ የምንለዋወጥበት መድረክ መሆኑን ገልጸዋል ።
በዕለቱ የባለስልጣኑ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ላቀች ሀይሌ የራሳቸውን የህይወትና የትምህርት እና የስራ ተሞክሮና ልምዳቸውን ለሌሎች አስተማሪ በሆነ መልኩ አጋርተዋል።
ራስን ሁል ጊዜ በዕውቀት ማዳበር ፣ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ጋር መልካም ግንኙኘት መኖር ፣ለባለሙያ ልምድን ማጋራት እና ስራን በትብብር ፣ በአንድነት እና ዝቅ ብሎ መስራት ዉጤታማ እንደሚያደርግ በመድረኩ ገልጸዋል ፡፡
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍9❤4
ባለስልጣኑ የቀሪ ስድሰት ወራት የተከለሰ የእቅድ ውይይት አካሄደ
26-05 -2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የቀጣይ ስድስት ወራት የተከለሰ ዕቅድ ውይይት ከማዕከሉ ዳይሬክተሮች እና ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለሥልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ባለፈው ስድስት ወራት በነበረን አፈፃፀም የታዩ ጥንካሬዎች በማስቀጠል የታዩ ክፍተቶችን በመለየት በቀጣይ ወራት የመፈጸምና የማስፈፀም አቅምን በማጎልበት ውጤታማ ውጤታማ ተግባር መከናወን ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2017 በጀት ዓመት የጣይ ስድስት ወራት የተከለሰ እቅድ ሰነድ በባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል ።
በሰነዱ ባለፉት ስድስት ወራት የተቋም ግንባታ ፣የሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በስፋት መስራት እና በከተማዋ የሚታዪ ደንብ ተላላፊዎች ላይ ህጋማዊ እርምጃ መወሰዱን ተጠቅሰዋል፡፡
ባለስልጣኑ ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድ ሰው ተኮር ሰራዎችን በማከናወን አስራ አንድ የአቅመ ደካማ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቶቹ ማስረከቡ በሪፖርቱ ተገልጿል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
26-05 -2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የቀጣይ ስድስት ወራት የተከለሰ ዕቅድ ውይይት ከማዕከሉ ዳይሬክተሮች እና ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለሥልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ባለፈው ስድስት ወራት በነበረን አፈፃፀም የታዩ ጥንካሬዎች በማስቀጠል የታዩ ክፍተቶችን በመለየት በቀጣይ ወራት የመፈጸምና የማስፈፀም አቅምን በማጎልበት ውጤታማ ውጤታማ ተግባር መከናወን ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2017 በጀት ዓመት የጣይ ስድስት ወራት የተከለሰ እቅድ ሰነድ በባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል ።
በሰነዱ ባለፉት ስድስት ወራት የተቋም ግንባታ ፣የሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በስፋት መስራት እና በከተማዋ የሚታዪ ደንብ ተላላፊዎች ላይ ህጋማዊ እርምጃ መወሰዱን ተጠቅሰዋል፡፡
ባለስልጣኑ ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድ ሰው ተኮር ሰራዎችን በማከናወን አስራ አንድ የአቅመ ደካማ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቶቹ ማስረከቡ በሪፖርቱ ተገልጿል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍7❤3
የደንብ ማስከበር ተልዕኮን ለማስፈፀም በስነ-ምግባር የታነፀ ኦፊሰርን መገንባት እንደሚገባ ተገለፀ።
27/05/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተሰጠውን ተልዕኮ ለመወጣት በስነ-ምግባር የታነፀ እና ሌብነትን የሚፀየፍ ኦፊሰርን ለማብቃት የሚያስችል ግምገማዊ ስልጠና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አዳራሽ አካሄደ።
በግምገማዊ ስልጠናው የሁሉም ወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ቡድን መሪ፣ ተባባሪ አካላትና አጠቃላይ ኦፊሰሮች ተካፋይ ሆነዋል።
መድረኩን ያስጀመሩት የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ ዓለሙ እንደተናገሩት ኦፊሰሩን ለተልዕኮ ዝግጁ ለማድረግ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በመስጠት፣ ለማብቃት እየተሠራ እንደሚገኝና ውጤታማ ስራዎችንም ማከናወን እየተቻለ መሆኑን ገልፀዋል።
የመድረኩ የክብር እንግዳ የሆኑት የክፍለ ከተማው ሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባህሩ በቀለ እንዳሉት ተቋሙ ከጊዜ ወደጊዜ እራሱን በማዘመን የደንብ መተላለፎችንና የፀጥታ ስራዎችን በብቃት በመወጣት ተልዕኮውን እየፈፀመ እንደሚገኝና በቀጣይም አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
ግምገማዊ ስልጠናውን የሰጡት እና የተዘጋጀውን ሰነድ ያቀረቡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ሲሆኑ ስነ-ምግባርና ብልሹ አሠራርን ከመልካም አስተዳደር አንፃር በመቃኘት ለችግሩ መፍትሔ ማስቀመጥና ተጠያቂነትን ማስፈን የስልጠናው ዓላማ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በመሆኑም ባለስልጣኑ ፈፃሚውንና ኦፊሰሩን ከስነ-ምግባርና ብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የከተማ አስተዳደሩን ተልዕኮ ከዳር እንዲያደርስ የተለያዩ የአቅም ግንባታ እና ግምገማዊ ስልጠናዎችን እየሠጠ እንደሚገኝና በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በስልጠናው ያነጋገርናቸው ሠልጣኞች እንደገለፁት፦ ማህበረሰቡን በመልካም ስነ-ምግባር በማገልገል ዘላቂ አጋርነቱን ማረጋገጥ እንድንችል ስልጠናው በርካታ ግንዛቤዎችን ያስገነዘበ መሆኑን አስረድተዋል።
የመድረኩን ውይይት የመሩት የክፍለ ከተማው የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መብራቱ ደሴ እንደተናገሩት የደንብ ማስከበር ኦፊሰር በህዝቡ ተመልምሎ ሠልጥኖ መልሶ ህዝቡን የሚያገለግል በመሆኑ ሁልጊዜ እራሱን ከብልሹ አሠራር እየጠበቀ ህብረተሰቡን በታማኝነት ሊያገለግል እንደሚገባ ተናግረዋል።
አክለውም በከተማዋ ውስጥ ያለውን ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ስራዎች የተሳለጡ እንዲሆኑ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሩ ሚና የላቀ በመሆኑ በቀጣይም በትጋት ተልዕኮውን እንዲወጣ አሳስበዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
27/05/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተሰጠውን ተልዕኮ ለመወጣት በስነ-ምግባር የታነፀ እና ሌብነትን የሚፀየፍ ኦፊሰርን ለማብቃት የሚያስችል ግምገማዊ ስልጠና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አዳራሽ አካሄደ።
በግምገማዊ ስልጠናው የሁሉም ወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማው የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ቡድን መሪ፣ ተባባሪ አካላትና አጠቃላይ ኦፊሰሮች ተካፋይ ሆነዋል።
መድረኩን ያስጀመሩት የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ ዓለሙ እንደተናገሩት ኦፊሰሩን ለተልዕኮ ዝግጁ ለማድረግ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በመስጠት፣ ለማብቃት እየተሠራ እንደሚገኝና ውጤታማ ስራዎችንም ማከናወን እየተቻለ መሆኑን ገልፀዋል።
የመድረኩ የክብር እንግዳ የሆኑት የክፍለ ከተማው ሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባህሩ በቀለ እንዳሉት ተቋሙ ከጊዜ ወደጊዜ እራሱን በማዘመን የደንብ መተላለፎችንና የፀጥታ ስራዎችን በብቃት በመወጣት ተልዕኮውን እየፈፀመ እንደሚገኝና በቀጣይም አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
ግምገማዊ ስልጠናውን የሰጡት እና የተዘጋጀውን ሰነድ ያቀረቡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ሲሆኑ ስነ-ምግባርና ብልሹ አሠራርን ከመልካም አስተዳደር አንፃር በመቃኘት ለችግሩ መፍትሔ ማስቀመጥና ተጠያቂነትን ማስፈን የስልጠናው ዓላማ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በመሆኑም ባለስልጣኑ ፈፃሚውንና ኦፊሰሩን ከስነ-ምግባርና ብልሹ አሠራር እራሱን በመጠበቅ የከተማ አስተዳደሩን ተልዕኮ ከዳር እንዲያደርስ የተለያዩ የአቅም ግንባታ እና ግምገማዊ ስልጠናዎችን እየሠጠ እንደሚገኝና በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በስልጠናው ያነጋገርናቸው ሠልጣኞች እንደገለፁት፦ ማህበረሰቡን በመልካም ስነ-ምግባር በማገልገል ዘላቂ አጋርነቱን ማረጋገጥ እንድንችል ስልጠናው በርካታ ግንዛቤዎችን ያስገነዘበ መሆኑን አስረድተዋል።
የመድረኩን ውይይት የመሩት የክፍለ ከተማው የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መብራቱ ደሴ እንደተናገሩት የደንብ ማስከበር ኦፊሰር በህዝቡ ተመልምሎ ሠልጥኖ መልሶ ህዝቡን የሚያገለግል በመሆኑ ሁልጊዜ እራሱን ከብልሹ አሠራር እየጠበቀ ህብረተሰቡን በታማኝነት ሊያገለግል እንደሚገባ ተናግረዋል።
አክለውም በከተማዋ ውስጥ ያለውን ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ስራዎች የተሳለጡ እንዲሆኑ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሩ ሚና የላቀ በመሆኑ በቀጣይም በትጋት ተልዕኮውን እንዲወጣ አሳስበዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍12