ባለስልጣኑ የተመደቡት አመራር ከተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች ጋር ትውውቅ አደረጉ
ጥር 19/2017 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በምክትል ስራ-አስኪያጅ ማዕረግ የስልጠና እና የቅድመ መከላከል ዘርፍ ሃላፊ ሆነው ወደ ተቋሙ የተመደቡት አቶ ንጋቱ ዳኛቸውን ከተቋሙ የማዕከልና የክፍ ለከተማ አመራሮች በተገኙበት ከመላው የባለስልጣኑ ሰራተኞች ጋር ትውውቅ አደረጉ።
በመድረኩ የቀድሞ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅነት ያገለገሉና አሁን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት የተሾሙት ኮማንደር አህመድ መሀመድን የሽኝት ፕሮግራም ተደርጓል።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ወደ ተቋሙ ተመድበው ለመጡት አቶ ንጋቱ ዳኛቸውን ወደ ተቋሙ እንኳን ደና መጡ በማለት ከተቋሙ ለተዘዋወሩት ኮ/ር አህመድ መሀመድን ለባለስልጣኑ ስኬት ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበው መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።
ተቋሙ ውስጥ ያለው አንድነት ለስራዎች መሳካት ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን በቆየሁበት ጊዜ መረዳት ችያለው በማለት ለተደረገኝ የሽኝት ፕሮግራም ከልብ አመሰግናለሁ ሲሉ የቀድሞ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ የአሁኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ኮማንደር አህመድ መሀመድ ገልጸዋል ።
በቀጣይ የተጀመሩ ስራዎችን ከአመራሩና ከሰራተኞ ጋር በጋራ በመሆን በማስቀጠልና በማከናወን ውጤታማ በመሆን የተሰጣቸውን ሀላፊነት በአግባቡ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ተናግረዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
ጥር 19/2017 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በምክትል ስራ-አስኪያጅ ማዕረግ የስልጠና እና የቅድመ መከላከል ዘርፍ ሃላፊ ሆነው ወደ ተቋሙ የተመደቡት አቶ ንጋቱ ዳኛቸውን ከተቋሙ የማዕከልና የክፍ ለከተማ አመራሮች በተገኙበት ከመላው የባለስልጣኑ ሰራተኞች ጋር ትውውቅ አደረጉ።
በመድረኩ የቀድሞ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅነት ያገለገሉና አሁን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት የተሾሙት ኮማንደር አህመድ መሀመድን የሽኝት ፕሮግራም ተደርጓል።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ወደ ተቋሙ ተመድበው ለመጡት አቶ ንጋቱ ዳኛቸውን ወደ ተቋሙ እንኳን ደና መጡ በማለት ከተቋሙ ለተዘዋወሩት ኮ/ር አህመድ መሀመድን ለባለስልጣኑ ስኬት ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበው መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።
ተቋሙ ውስጥ ያለው አንድነት ለስራዎች መሳካት ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን በቆየሁበት ጊዜ መረዳት ችያለው በማለት ለተደረገኝ የሽኝት ፕሮግራም ከልብ አመሰግናለሁ ሲሉ የቀድሞ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ የአሁኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ኮማንደር አህመድ መሀመድ ገልጸዋል ።
በቀጣይ የተጀመሩ ስራዎችን ከአመራሩና ከሰራተኞ ጋር በጋራ በመሆን በማስቀጠልና በማከናወን ውጤታማ በመሆን የተሰጣቸውን ሀላፊነት በአግባቡ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ተናግረዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
👍14🤔5
ባለስልጣኑ የደንብ መተላለፎችን በካሜራና በመገናኛ ራዲዮ በመታገዝ የቅድመ መከላከልና የቁጥጥር ስራ እንደሚጀመር ተገለፀ
23/05 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ የታገዘ ስማርት ቢሮ ለመስራት የሁለቱ ተቋማት አመራሮችና ዳይሬክተሮች በተገኙበት ውይይት ተካሂዷል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የከተማችንን ፈጣን እድገት ጋር የዘመነ የደንብ ጥሰቶችንና ህገወጥ ተግባራት የመከላከል ስራ ለማከናወን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ትግበራ ለማድረግና ወደ ተግባር ለመግባትና የሚያስፈልጉ ግባአቶቸን በማሟላት ሰራዎችን ለመጀመር እቅድ ተዘጋጅቶ እንቅስቃሴ መጀመሩ ገልጸዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ የማነ ደሳለኝ በቴክኖሎጂ ተቋሙ ለማዘመን፣ ወጪን ለመቀነስ፣ እና አገልግሎት ለማሻሻል የሚረዱ ቴክኖሎጂ ለመጠቀም የሚረዱ ፋይል ማኔጅመንት፣ ስማርት ኦፊስ፣ፊልድ ማኔጅመንት፣አሴት ማኔጅመንት እና ሌሎች ቴክኖሎጂዎች ለመዘርጋት ስራዎች መጀመራቸው ተናግረዋል ።
አክለውም ቢሮው ከባለስልጣናኑ ጋር በመተባበር ለስራው መሳካት የሚያስፈልጉ የሰው ሃይሉን በማብቃትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ሰፊ በማድረግ ተቋሙን ስማርት ቢሮ ለማድረግ በቀጣይም በሙሉ አቅም በማገዝ እንደሚሰራ ተናግረዋል ።
ባለስልጣኑ የደንብ መተላለፎችን በካሜራና በመገናኛ ራዲዮ በመጠቀም መረጃ መሠረት በማድረግ የቅድመ መከላከልና የቁጥጥር ስራ እንደሚጀመር ተጠቁሟል።
ቴክኖሎጂው መሳሪያዎች እና ስርዓቶች የደህንነት እና የግንኙነት ስርዓቶች በማሻሻል በተቋማት ውስጥ የሚገኙ የግንኙነት ስርዓቶች በቪዲዮ ኮንፈረንስ በመደገፍ አገልግሎትን ለማሻሻል እንደሚረዳ በውይይቱ መድረኩ ተገልጿል ።
በመጨረሻም ለስራው መሳካት በተነሱ ሀሳቦች ላይ ውይይት ተካሂዶ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በፍጥነት ተግባራዊ ለማድረግ የቀጣይ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
23/05 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ የታገዘ ስማርት ቢሮ ለመስራት የሁለቱ ተቋማት አመራሮችና ዳይሬክተሮች በተገኙበት ውይይት ተካሂዷል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የከተማችንን ፈጣን እድገት ጋር የዘመነ የደንብ ጥሰቶችንና ህገወጥ ተግባራት የመከላከል ስራ ለማከናወን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ትግበራ ለማድረግና ወደ ተግባር ለመግባትና የሚያስፈልጉ ግባአቶቸን በማሟላት ሰራዎችን ለመጀመር እቅድ ተዘጋጅቶ እንቅስቃሴ መጀመሩ ገልጸዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ የማነ ደሳለኝ በቴክኖሎጂ ተቋሙ ለማዘመን፣ ወጪን ለመቀነስ፣ እና አገልግሎት ለማሻሻል የሚረዱ ቴክኖሎጂ ለመጠቀም የሚረዱ ፋይል ማኔጅመንት፣ ስማርት ኦፊስ፣ፊልድ ማኔጅመንት፣አሴት ማኔጅመንት እና ሌሎች ቴክኖሎጂዎች ለመዘርጋት ስራዎች መጀመራቸው ተናግረዋል ።
አክለውም ቢሮው ከባለስልጣናኑ ጋር በመተባበር ለስራው መሳካት የሚያስፈልጉ የሰው ሃይሉን በማብቃትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ሰፊ በማድረግ ተቋሙን ስማርት ቢሮ ለማድረግ በቀጣይም በሙሉ አቅም በማገዝ እንደሚሰራ ተናግረዋል ።
ባለስልጣኑ የደንብ መተላለፎችን በካሜራና በመገናኛ ራዲዮ በመጠቀም መረጃ መሠረት በማድረግ የቅድመ መከላከልና የቁጥጥር ስራ እንደሚጀመር ተጠቁሟል።
ቴክኖሎጂው መሳሪያዎች እና ስርዓቶች የደህንነት እና የግንኙነት ስርዓቶች በማሻሻል በተቋማት ውስጥ የሚገኙ የግንኙነት ስርዓቶች በቪዲዮ ኮንፈረንስ በመደገፍ አገልግሎትን ለማሻሻል እንደሚረዳ በውይይቱ መድረኩ ተገልጿል ።
በመጨረሻም ለስራው መሳካት በተነሱ ሀሳቦች ላይ ውይይት ተካሂዶ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በፍጥነት ተግባራዊ ለማድረግ የቀጣይ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
"የምንሰጠው አገልግሎት በቅንነትና በፍትሀዊነት ከብልሹ አሰራርና ከሙስና የጸዳ ሊሆን ይገባል" ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ
24/05 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት "ስነምግባርና መልካም አስተዳደር ለተሻለ አገልግሎት አሰጣጥ " በሚል መሪ ቃል የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የአንደኛ ዙር ስልጠና ተሰጠ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋም ግንባታ ስራችንን ስናከናውን ስነ-ምግባርን በመላበስ የሚጠበቅብንን ሙያዊ ኃላፊነት በአግባቡ መውጣትና ስራዎችን ሰንሰራና ህብረተሰቡን ስናገለግል በቅንነት፣በፍትሀዊነት እና በቅልጥፍና አገለግሎት በመስጠትና ሁሉም አካል ራሱን ከብልሹ አሰራርና ከሙስና የጸዳ በማድረግ ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡
አክለውም በከተሞችን እየተከናወነ የሚገኙት የኮሪደር ልማት ስራዎች ላይ ኦፊሰሩ ከአመራሩ የሚሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ በመወጣት ያለውን አቅም ያሳየበትና በከተማ ደረጃ ተቋማችን እውቅና ያገኘበት መሆኑንና በቀጣይም ተጠናክሮ ሊሰራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል ።
በመድረኩን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ ተስፋዬ ባለፋት ስድስት ወራት እንደ ተቋም በተሰጠን ተልዕኮ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎቻችን በማጠናከር ህብረተሰቡ ከደንብ መተላለፍ ቅጣት አንዲጠበቅና ህገወጥነትን እንዲጸየፍ የማድረግ ስራ እያከናወነ አልፎ የሚመጡትን ደንብ ተላላፊዎች በመከላከል በመቆጣጠርና እርምጃ በመውሰድ በክ/ከተማው የሚታይ የነበሩ ደንብ ጥሰቶችን 60% መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል ።
በግማሽ ዓመቱ በክፍለ ከተማው ከአራት ሺ በላይ ደንብ ተላላፊዎችን በመቅጣት ከ20ሚሊዮን ብር በላይ ለፋይናንስ ገቢ ማድረግ መቻሉን ኃላፊው ገልፀዋል ።
በተጨማሪም ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድ ሰው ተኮር ሰራዎችን በማከናወን ወላጅ አልባ ህጻናትን መንከባከብና መደረገፍ እንዲሁም ሁለት የአቅመ ደካማ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቱ ማስረከባቸውን ኃላፊው ተናግረዋል።
የስነምግባርና መልካም አስተዳደር ብልሹ አሰራርን ቀድሞ ለመከላከል እንዲቻል የተዘጋጀው የግምገማዊ ስልጠና ሰነድ በባለስልጣኑ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ ቀርቧል።
የስነምግባርና ብልሹ አሰራር ችግር ለተቋማችን ገጽታ ግንባታ ያለውን ተጽዕኖ በመገንዘብ በዚህ ድርጊት የሚሳተፉትን ጠንካራ የተጠያቂነት ስርዓት መዘርጋትና ሁሉም አካል ብልሹ አሰራርን ሊታገለው እንደሚያስፈልግ አቶ እዬብ ከበደ ገልጸዋል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶበት ቀጣይ የስራ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ ተስፋዬ ተሰጥቶበታል ስልጠናው በሁለተኛ ዙር ለቀሩት ኦፊሰሮች በነገው ዕለት እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችለል ።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
24/05 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት "ስነምግባርና መልካም አስተዳደር ለተሻለ አገልግሎት አሰጣጥ " በሚል መሪ ቃል የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የአንደኛ ዙር ስልጠና ተሰጠ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋም ግንባታ ስራችንን ስናከናውን ስነ-ምግባርን በመላበስ የሚጠበቅብንን ሙያዊ ኃላፊነት በአግባቡ መውጣትና ስራዎችን ሰንሰራና ህብረተሰቡን ስናገለግል በቅንነት፣በፍትሀዊነት እና በቅልጥፍና አገለግሎት በመስጠትና ሁሉም አካል ራሱን ከብልሹ አሰራርና ከሙስና የጸዳ በማድረግ ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡
አክለውም በከተሞችን እየተከናወነ የሚገኙት የኮሪደር ልማት ስራዎች ላይ ኦፊሰሩ ከአመራሩ የሚሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ በመወጣት ያለውን አቅም ያሳየበትና በከተማ ደረጃ ተቋማችን እውቅና ያገኘበት መሆኑንና በቀጣይም ተጠናክሮ ሊሰራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል ።
በመድረኩን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ ተስፋዬ ባለፋት ስድስት ወራት እንደ ተቋም በተሰጠን ተልዕኮ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎቻችን በማጠናከር ህብረተሰቡ ከደንብ መተላለፍ ቅጣት አንዲጠበቅና ህገወጥነትን እንዲጸየፍ የማድረግ ስራ እያከናወነ አልፎ የሚመጡትን ደንብ ተላላፊዎች በመከላከል በመቆጣጠርና እርምጃ በመውሰድ በክ/ከተማው የሚታይ የነበሩ ደንብ ጥሰቶችን 60% መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል ።
በግማሽ ዓመቱ በክፍለ ከተማው ከአራት ሺ በላይ ደንብ ተላላፊዎችን በመቅጣት ከ20ሚሊዮን ብር በላይ ለፋይናንስ ገቢ ማድረግ መቻሉን ኃላፊው ገልፀዋል ።
በተጨማሪም ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድ ሰው ተኮር ሰራዎችን በማከናወን ወላጅ አልባ ህጻናትን መንከባከብና መደረገፍ እንዲሁም ሁለት የአቅመ ደካማ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቱ ማስረከባቸውን ኃላፊው ተናግረዋል።
የስነምግባርና መልካም አስተዳደር ብልሹ አሰራርን ቀድሞ ለመከላከል እንዲቻል የተዘጋጀው የግምገማዊ ስልጠና ሰነድ በባለስልጣኑ የስነምግባርና ጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዬብ ከበደ ቀርቧል።
የስነምግባርና ብልሹ አሰራር ችግር ለተቋማችን ገጽታ ግንባታ ያለውን ተጽዕኖ በመገንዘብ በዚህ ድርጊት የሚሳተፉትን ጠንካራ የተጠያቂነት ስርዓት መዘርጋትና ሁሉም አካል ብልሹ አሰራርን ሊታገለው እንደሚያስፈልግ አቶ እዬብ ከበደ ገልጸዋል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶበት ቀጣይ የስራ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ ተስፋዬ ተሰጥቶበታል ስልጠናው በሁለተኛ ዙር ለቀሩት ኦፊሰሮች በነገው ዕለት እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችለል ።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
የየተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡና የአደባባይ በዓላት ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበር አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና የምስጋና ፕሮግራም ተካሄደ
24/05/2017ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም በመጀመሪያ ግማሽ አመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡና የአደባባይ በዓላት ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበር አስተዋፅኦ ላበረከቱ ለባለድርሻ አካላት እና የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎችና የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እውቅናና የምስጋና ፕሮግራም የባለስልጣኑና የክፍለ ከተማው አመራሮች በተገኙበት የእውቅናና ምስጋና እና ፕሮግራም ተካሂዷል።
በመረሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈሪ እንደገለፁት፣ የባለስልጣኑን የውስጥ አሰራሮች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው አመራሩና ኦፊሰሩ በሰራው ጠንካራ ስራ የደንብ ጥሰት ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነፃፀር በከተማዋ 58 በመቶ ቀንሷል ብለዋል።
ተቋሙን በቴክኖሎጂ፣ በሰው ሀይል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ናቸው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሀላፊ ኮማንደር ግርማ ሰንበቱ በበኩላቸው የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም በመጀመሪያ ግማሽ አመት ከ6 ሚሊየን ብር በላይ በቅጣት እና በጨረታ ገቢ ማድረጉን ገልፀው ባሳለፍነው አመት ተመሳሳይ ወቅት የተገኘው 3 ሚሊዮን ብር እንደነበር አስታውሰዋል።
ሀላፊው በተያዘው በጀት አመቱ 6ወራት የደንብ መተላለፎች በብቃት በመከላከል እና በመቆጣጠር የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ወረዳዎች እና የተከበሩ በአላትን/የኢሬቻ፣ መስቀል እና ጥምቀት/ ያለምንም የፀጥታ ችግር ተከብሮ እንዲያልቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለ ድርሻ አካላት እና የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እውቅና መስጠት የቀጣይ ስራችን ላይ ተነሳሽነት እንደሚፈጥር ገልጿል።
በእውቅና እና ሽልማቱን ፕሮግራሙ ወረዳ1፣ወረዳ10 እና ወረዳ 8 ከ1ኛ እስከ 3ኛ በመውጣት እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
24/05/2017ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም በመጀመሪያ ግማሽ አመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡና የአደባባይ በዓላት ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበር አስተዋፅኦ ላበረከቱ ለባለድርሻ አካላት እና የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎችና የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እውቅናና የምስጋና ፕሮግራም የባለስልጣኑና የክፍለ ከተማው አመራሮች በተገኙበት የእውቅናና ምስጋና እና ፕሮግራም ተካሂዷል።
በመረሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈሪ እንደገለፁት፣ የባለስልጣኑን የውስጥ አሰራሮች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው አመራሩና ኦፊሰሩ በሰራው ጠንካራ ስራ የደንብ ጥሰት ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነፃፀር በከተማዋ 58 በመቶ ቀንሷል ብለዋል።
ተቋሙን በቴክኖሎጂ፣ በሰው ሀይል እና በአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ናቸው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሀላፊ ኮማንደር ግርማ ሰንበቱ በበኩላቸው የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም በመጀመሪያ ግማሽ አመት ከ6 ሚሊየን ብር በላይ በቅጣት እና በጨረታ ገቢ ማድረጉን ገልፀው ባሳለፍነው አመት ተመሳሳይ ወቅት የተገኘው 3 ሚሊዮን ብር እንደነበር አስታውሰዋል።
ሀላፊው በተያዘው በጀት አመቱ 6ወራት የደንብ መተላለፎች በብቃት በመከላከል እና በመቆጣጠር የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ወረዳዎች እና የተከበሩ በአላትን/የኢሬቻ፣ መስቀል እና ጥምቀት/ ያለምንም የፀጥታ ችግር ተከብሮ እንዲያልቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለ ድርሻ አካላት እና የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እውቅና መስጠት የቀጣይ ስራችን ላይ ተነሳሽነት እንደሚፈጥር ገልጿል።
በእውቅና እና ሽልማቱን ፕሮግራሙ ወረዳ1፣ወረዳ10 እና ወረዳ 8 ከ1ኛ እስከ 3ኛ በመውጣት እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍3👏1