ባለስልጣኑ በለውጥ አመራር እና በውሳኔ ሰጪነት ላይ ስልጠና ሰጠ
05/04/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከማዕከል እስከ ወረዳ ለሚገኙ አመራሮች በስልታዊ አስተቃቀድ፣ በአስተዳደር ፣ውሳኔ ሰጪነትና እና የለውጥ አመራር ላይ ስልጠና ሰጠ።
የስልጠናው መክፈቻ ንግግር ያደረኩት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋማችን የቅድመ መከላከል እና ስልጠና ዘርፍ በእቅድ ውስጥ በመያዝ የአመራሮችን አቅም ይገነባል ተብሎ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
አክለውም ሰልጣኝ አመራሮ በሚኖረው የ3 ቀናት ቆይታ በስልጠናው መሰረት የተቋሙን ፍላጎት እና አላማ አውቆ ወደ ስራ መግባት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል።
ስልጠናው ከኢትዮጲያ ስራ አመራር ኢንሰቲትዩት በመጡ አሰልጣኝ ዶ/ር ጀቤሳ ተሾመ እና በአቶ ሀገር መኩሪያ ለቀጣይ 2 ቀናት የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ ኮማንደር አህመድ መሀመድ ስልጠናው በእውቀት ላይ የተመሰረተ አመራር ለመፍጠር ወሳኝነት እንዳለው ተናግረው ስልጠናው ለቀጣይ ሁለት ቀናት በጥብቅ ዲሲፕሊን እንደሚመራ ገልፀዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
05/04/2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከማዕከል እስከ ወረዳ ለሚገኙ አመራሮች በስልታዊ አስተቃቀድ፣ በአስተዳደር ፣ውሳኔ ሰጪነትና እና የለውጥ አመራር ላይ ስልጠና ሰጠ።
የስልጠናው መክፈቻ ንግግር ያደረኩት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋማችን የቅድመ መከላከል እና ስልጠና ዘርፍ በእቅድ ውስጥ በመያዝ የአመራሮችን አቅም ይገነባል ተብሎ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
አክለውም ሰልጣኝ አመራሮ በሚኖረው የ3 ቀናት ቆይታ በስልጠናው መሰረት የተቋሙን ፍላጎት እና አላማ አውቆ ወደ ስራ መግባት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል።
ስልጠናው ከኢትዮጲያ ስራ አመራር ኢንሰቲትዩት በመጡ አሰልጣኝ ዶ/ር ጀቤሳ ተሾመ እና በአቶ ሀገር መኩሪያ ለቀጣይ 2 ቀናት የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ ኮማንደር አህመድ መሀመድ ስልጠናው በእውቀት ላይ የተመሰረተ አመራር ለመፍጠር ወሳኝነት እንዳለው ተናግረው ስልጠናው ለቀጣይ ሁለት ቀናት በጥብቅ ዲሲፕሊን እንደሚመራ ገልፀዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
የአንካራው ስምምነት የተገኘው ውጤት የሀገራችን ጠንካራ የዲፕሎማሲ ውጤት ማሳያ መሆኑን ተገለፀ
07/04/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የማዕከል፣የክፍለ ከተማና የወረዳ ኃላፊዎች እእንዲሁም የማዕከሉ ዳይሬክተሮች በተገኙበት በወቅታዊ በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል የተደረሰውን የአንካራ ስምምነት ተከትሎ የውይይት መድረክ ተካሄደ።
የውይይቱ መነሻ ሰነድ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ ቤት የአቅም ግንባታ እና የፖለቲካ ዘርፍ ምክትል ሀላፊ አቶ ዘውዱ ከበደ የአንካራው ስምምነት የተገኘው ውጤት የሀገራችን ጠንካራ የዲፕሎማሲ ውጤት ማሳያ መሆኑ ገልፀዋል።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፅኖ ፈጣሪነት ለማሳጣት በጎረቤት ሀገራት በጠላትነተ ለማስፈረጅ የየተዘጋጁ አካላት ሴራ ያከሸፈ መሆኑ ገልፀዋል።
አክለውም ስምምነቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ ጥበብና ብስለት በተሞላበት መንገድ ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ በህጋዊ መልኩ ምላሽ የተገኘበት መሆኑ ገልፀዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በአንካራው ስምምነት በርካታ የኢኮኖሚ ትሩፋቶች የሚያስገኝ በመሆኑ የተጀመሩ የልማት ስራዎች አጠናክሮ በማስቀጠል የሀገራችን ብልፅግና እውን ለማድረግ የሚያጠናክር መሆኑ ገልፀዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
07/04/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የማዕከል፣የክፍለ ከተማና የወረዳ ኃላፊዎች እእንዲሁም የማዕከሉ ዳይሬክተሮች በተገኙበት በወቅታዊ በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል የተደረሰውን የአንካራ ስምምነት ተከትሎ የውይይት መድረክ ተካሄደ።
የውይይቱ መነሻ ሰነድ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ ቤት የአቅም ግንባታ እና የፖለቲካ ዘርፍ ምክትል ሀላፊ አቶ ዘውዱ ከበደ የአንካራው ስምምነት የተገኘው ውጤት የሀገራችን ጠንካራ የዲፕሎማሲ ውጤት ማሳያ መሆኑ ገልፀዋል።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፅኖ ፈጣሪነት ለማሳጣት በጎረቤት ሀገራት በጠላትነተ ለማስፈረጅ የየተዘጋጁ አካላት ሴራ ያከሸፈ መሆኑ ገልፀዋል።
አክለውም ስምምነቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ ጥበብና ብስለት በተሞላበት መንገድ ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ በህጋዊ መልኩ ምላሽ የተገኘበት መሆኑ ገልፀዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በአንካራው ስምምነት በርካታ የኢኮኖሚ ትሩፋቶች የሚያስገኝ በመሆኑ የተጀመሩ የልማት ስራዎች አጠናክሮ በማስቀጠል የሀገራችን ብልፅግና እውን ለማድረግ የሚያጠናክር መሆኑ ገልፀዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ባለስልጣኑ ሰሞኑን በNBC Ethiopia በሳምንቱ ጫወታ ፕሮግራም ስለደንብ ማስከበር ባለስልጣን የቀረበው መረጃ የተሳሳተና ተቋሙን የማይገልፅ መሆኑ አስታወቀ
16/04/2017 ዓ.ም
**አዲስ አባባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ደንብና ህግና የማስከበር ተግባሩን ለማስተጓጎል ሆን ብለው የተቋሙን ስም ለማጠልሸት የተሳሳተ አመለካከት በህብረተሰቡ ላይ እንዲሰርፅ በሚያደርጉ ግለሰቦችና ተቋማት በህግ አግባብ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አስታወቀ።
የባለስልጣኑ የህግ አገልግሎት ቡድን መሪ አቶ ብርሃኑ ኮርሳ ሰሞኑን በNBC Ethiopia በሳምንቱ ጫወታ ፕሮግራም ስለደንብ ማስከበር ባለስልጣን የቀረበውና በሶሻል ሚዲያዎች የተጋራው መረጃ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የማይገልፅና ከሚሰጠው አገልግሎት ፈፅሞ የተሳሳተ መረጃ መሆኑ ገልፀዋል።
የፕሮግራሙ አቅራቢው ስለባለስልጣኑ የገለፀው መረጃ ከተቋሙ ተግባር ፍፁም አሉባልታና የሀሰት መሆናቸውና ድርጊቱ ህገ-ወጦችን የሚደግፍና የሚያበረታታ በመሆኑ ሊታረም እንደሚገባ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ ፕሮግራሙ ከሚዲያ እና ከጋዜጠኝነት ስነ-ምግባር ባፈነገጠ መልኩ የተቋሙን ሀሳብ፣ አሰራርና መመሪያ ለህብረተሰቡ አሉታዊ እንዳለውና በጥላቻና ሀላፊነት በጎደለው መልኩ የቀረበ በመሆኑ ተቀባይነት እንደሌለው አስታውቋል።
ፕሮግራሙ እንደ ሚዲያ አሰራር የተቋሙ ስራዎች በመግለፅ ክፍተቶቹን እንዲታረሙ ማሳየት ሲገባው ሆን ብሎ ከዚህ በተቃራኒ ፍፁም አሉታዊና የጥላቻ አመለካከትን የቀረበበት በመሆኑ ጉዳዩ ለህግ እንደሚያቀርበው ባለስልጣኑ አስታውቋል።
ተቋሙ የሄደበትን በህግ የመጠየቅ ሂደትና የደረሰበት ውጤት ለህብረተሰቡ ግልፅ እንደሚደረግና በተቋሙ ላይ የተሳሳተ መረጃ የሚያሰራጭ ማንኛውም አካላት ላይ በህግ አግባብ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አቶ ብርሃኑ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ አዲስ አበባ ከተማን ውብ ፣ፅዱ፣ ለነዋሪዎቿና ለእንግዶቿ ምቹ ለማድረግ የደንብ መተላለፎች ለመከላከልና የበኮሪደር ልማቱ መሰረተ ልማት ደህንነት ለማስጠበቅ የተሰጠውን ሀላፊነት ለመወጣት ቀን ከለሊት እየሰራ ያለውን ስራ በሀሰት መረጃዎች አንደማይደናቀፍ አስታውቋል፡፡
ባለስልጣኑ በሀሰት መረጃ እና በአሉባልታዎች የተቋሙን ስም ለማጠልሸትና ለህብረተሰቡ የተሳሳተ መረጃ የሚሰጡ ግለሰቦችና ተቋማት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
መረጃው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
16/04/2017 ዓ.ም
**አዲስ አባባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ደንብና ህግና የማስከበር ተግባሩን ለማስተጓጎል ሆን ብለው የተቋሙን ስም ለማጠልሸት የተሳሳተ አመለካከት በህብረተሰቡ ላይ እንዲሰርፅ በሚያደርጉ ግለሰቦችና ተቋማት በህግ አግባብ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አስታወቀ።
የባለስልጣኑ የህግ አገልግሎት ቡድን መሪ አቶ ብርሃኑ ኮርሳ ሰሞኑን በNBC Ethiopia በሳምንቱ ጫወታ ፕሮግራም ስለደንብ ማስከበር ባለስልጣን የቀረበውና በሶሻል ሚዲያዎች የተጋራው መረጃ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የማይገልፅና ከሚሰጠው አገልግሎት ፈፅሞ የተሳሳተ መረጃ መሆኑ ገልፀዋል።
የፕሮግራሙ አቅራቢው ስለባለስልጣኑ የገለፀው መረጃ ከተቋሙ ተግባር ፍፁም አሉባልታና የሀሰት መሆናቸውና ድርጊቱ ህገ-ወጦችን የሚደግፍና የሚያበረታታ በመሆኑ ሊታረም እንደሚገባ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ ፕሮግራሙ ከሚዲያ እና ከጋዜጠኝነት ስነ-ምግባር ባፈነገጠ መልኩ የተቋሙን ሀሳብ፣ አሰራርና መመሪያ ለህብረተሰቡ አሉታዊ እንዳለውና በጥላቻና ሀላፊነት በጎደለው መልኩ የቀረበ በመሆኑ ተቀባይነት እንደሌለው አስታውቋል።
ፕሮግራሙ እንደ ሚዲያ አሰራር የተቋሙ ስራዎች በመግለፅ ክፍተቶቹን እንዲታረሙ ማሳየት ሲገባው ሆን ብሎ ከዚህ በተቃራኒ ፍፁም አሉታዊና የጥላቻ አመለካከትን የቀረበበት በመሆኑ ጉዳዩ ለህግ እንደሚያቀርበው ባለስልጣኑ አስታውቋል።
ተቋሙ የሄደበትን በህግ የመጠየቅ ሂደትና የደረሰበት ውጤት ለህብረተሰቡ ግልፅ እንደሚደረግና በተቋሙ ላይ የተሳሳተ መረጃ የሚያሰራጭ ማንኛውም አካላት ላይ በህግ አግባብ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አቶ ብርሃኑ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ አዲስ አበባ ከተማን ውብ ፣ፅዱ፣ ለነዋሪዎቿና ለእንግዶቿ ምቹ ለማድረግ የደንብ መተላለፎች ለመከላከልና የበኮሪደር ልማቱ መሰረተ ልማት ደህንነት ለማስጠበቅ የተሰጠውን ሀላፊነት ለመወጣት ቀን ከለሊት እየሰራ ያለውን ስራ በሀሰት መረጃዎች አንደማይደናቀፍ አስታውቋል፡፡
ባለስልጣኑ በሀሰት መረጃ እና በአሉባልታዎች የተቋሙን ስም ለማጠልሸትና ለህብረተሰቡ የተሳሳተ መረጃ የሚሰጡ ግለሰቦችና ተቋማት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
መረጃው፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።