የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት በበጀት አመቱ የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡ ተገለፀ
15/10/2016ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት በ2016 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ ላደረጉ አካላት የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም አካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አይዳ አወል በበጀት ዓመቱ በክፍለ ከተማው ከደንብ ማስከበር ተቋም ጋር በርካታ የፀጥታ እና የደንብ ማስከበር ተግባራት መከናወናቸውን በመግለፅ በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት መዘጋጀት ይገባል ብለዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አክለውም ክ/ከተማው የንግድ እና የሰዎች እንቅስቃሴ የሚበዛበት በመሆኑ በቀጣይ ብዙ የሚቀሩ ስራዎች ስላሉ ለማስተካከልና በቀጣይ አብሮ ለመስራት እንዲሁም ለፅ/ቤቱ በሚያስፈልገው ሁሉ ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸው ገልፀዋል።
በመድረኩ የእንኳን መጣቹ ንግግር ያደረጉት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ደረጄ ነገሮ በበጀት አመቱ በደንብ መተላለፎች በግንዛቤ እና በቁጥጥር ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡ ገልፀዋል።
በተጨማሪም ፕሮግራሙ የተዘጋጀው በ2016 በጀት አመት ለተሰሩ ውጤታማ ስራዎች አመራሮች እና ኦፊሰሮች ለማመስገን የተዘጋጀ የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም መሆኑና በቀጣይ በጀት ዓመት በጥንካሬ ያገኘናቸውን ለማስቀጠል ክፍተቶቹ ለመሙላት መነቃቃትን ለመፍጠር የተዘጋጀ መድረክ መሆኑ ገልፀዋል።
የመድረኩ የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በንግግራቸው በከተማችን ደንብ መተላለፎች ከመከታተል እና ከመቆጣጠር ባሻገር እንደስሟ አዲስና ውብ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እየተሰራ መሆኑ ጠቁመዋል።
በመጨረሻም በበጀት አመቱ በፅ/ቤቱ የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ ጉልህ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
15/10/2016ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት በ2016 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ ላደረጉ አካላት የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም አካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አይዳ አወል በበጀት ዓመቱ በክፍለ ከተማው ከደንብ ማስከበር ተቋም ጋር በርካታ የፀጥታ እና የደንብ ማስከበር ተግባራት መከናወናቸውን በመግለፅ በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት መዘጋጀት ይገባል ብለዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አክለውም ክ/ከተማው የንግድ እና የሰዎች እንቅስቃሴ የሚበዛበት በመሆኑ በቀጣይ ብዙ የሚቀሩ ስራዎች ስላሉ ለማስተካከልና በቀጣይ አብሮ ለመስራት እንዲሁም ለፅ/ቤቱ በሚያስፈልገው ሁሉ ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸው ገልፀዋል።
በመድረኩ የእንኳን መጣቹ ንግግር ያደረጉት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ደረጄ ነገሮ በበጀት አመቱ በደንብ መተላለፎች በግንዛቤ እና በቁጥጥር ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡ ገልፀዋል።
በተጨማሪም ፕሮግራሙ የተዘጋጀው በ2016 በጀት አመት ለተሰሩ ውጤታማ ስራዎች አመራሮች እና ኦፊሰሮች ለማመስገን የተዘጋጀ የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም መሆኑና በቀጣይ በጀት ዓመት በጥንካሬ ያገኘናቸውን ለማስቀጠል ክፍተቶቹ ለመሙላት መነቃቃትን ለመፍጠር የተዘጋጀ መድረክ መሆኑ ገልፀዋል።
የመድረኩ የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በንግግራቸው በከተማችን ደንብ መተላለፎች ከመከታተል እና ከመቆጣጠር ባሻገር እንደስሟ አዲስና ውብ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እየተሰራ መሆኑ ጠቁመዋል።
በመጨረሻም በበጀት አመቱ በፅ/ቤቱ የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ ጉልህ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
👍5
"ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም!” ሀገር አቀፍ የጎዳና ሩጫ ውድድር እየተካሄደ ነው
ሰኔ 30/2016 ዓ.ም
ሰላምን አስመልክቶ የተዘጋጀ ሀገር አቀፍ የ6 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በኢትዮጵያ በተለያዩ ከተሞች እየተካሄደ ነው።
ውድድሩ “ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም!” በሚል መሪ ሀሳብ ከማለዳ 12 ሠዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋና በሌሎች ዋና ዋና የክልል ከተሞች እየተካሄደ ነዉ ።
በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው መርሐ ግብር ታዋቂ አትሌቶችና ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች እየተሳተፉ ነው።
ሰኔ 30/2016 ዓ.ም
ሰላምን አስመልክቶ የተዘጋጀ ሀገር አቀፍ የ6 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በኢትዮጵያ በተለያዩ ከተሞች እየተካሄደ ነው።
ውድድሩ “ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም!” በሚል መሪ ሀሳብ ከማለዳ 12 ሠዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋና በሌሎች ዋና ዋና የክልል ከተሞች እየተካሄደ ነዉ ።
በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው መርሐ ግብር ታዋቂ አትሌቶችና ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች እየተሳተፉ ነው።
👍9👏2
ባለስልጣኑ በ2016 በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡ ተገለፀ
04-11-2016
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት ከማዕከሉ ሰራተኞች ጋር የባለስልጣኑ ኃላፊዎች በተገኙበት ውይይት መድረክ አካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት በ2016 በጀት ዓመት በእቅዳችን መሰረት በከተማችን የሚታዩ የደንብ ጥሰቶች በመከላከል፣በመቆጣጠር እና እርምጃ በመውሰድ የተቋም ግንባታን ለማጠናከርና አመራሩንና ሰራተኞችን ለማብቃት በርካታ ተግባራትን በማከናወን በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገብ መቻሉ ገልፀዋል ።
አክለውም ኃላፊው የ2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ለቀጣይ የ2017 በጀት ዓመት ለምናከናውነው ሰራዎቸ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው ሲሆን የነበሩንን ጠንካራ ጎኖች በማስቀጠል በስራዎች ውስጥ የታዩ ክፍተቶችን እና መሰናክሎችን ለማሻሻል የውይይት መድረኩ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ።
በእለቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ በባለስልጣኑ የእቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል ።
በሪፖርቱ በበጀት ዓመቱ ታቅደው የተፈጸሙ ተግባራት ፣ ታቅደው ያልተከናወኑ ተግባራቶች ፣ በአፈጻጸም ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና የተወሰዱ መፍትሔዎች ቀርበዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች በባለስልጣኑ የበላይ ሀላፊዎች ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶ የቀጣይ የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
04-11-2016
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት ከማዕከሉ ሰራተኞች ጋር የባለስልጣኑ ኃላፊዎች በተገኙበት ውይይት መድረክ አካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት በ2016 በጀት ዓመት በእቅዳችን መሰረት በከተማችን የሚታዩ የደንብ ጥሰቶች በመከላከል፣በመቆጣጠር እና እርምጃ በመውሰድ የተቋም ግንባታን ለማጠናከርና አመራሩንና ሰራተኞችን ለማብቃት በርካታ ተግባራትን በማከናወን በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገብ መቻሉ ገልፀዋል ።
አክለውም ኃላፊው የ2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ለቀጣይ የ2017 በጀት ዓመት ለምናከናውነው ሰራዎቸ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው ሲሆን የነበሩንን ጠንካራ ጎኖች በማስቀጠል በስራዎች ውስጥ የታዩ ክፍተቶችን እና መሰናክሎችን ለማሻሻል የውይይት መድረኩ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ።
በእለቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ በባለስልጣኑ የእቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል ።
በሪፖርቱ በበጀት ዓመቱ ታቅደው የተፈጸሙ ተግባራት ፣ ታቅደው ያልተከናወኑ ተግባራቶች ፣ በአፈጻጸም ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና የተወሰዱ መፍትሔዎች ቀርበዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች በባለስልጣኑ የበላይ ሀላፊዎች ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶ የቀጣይ የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።