ባለስልጣኑ ጉድጓድ ውስጥ የወደቀን መንገደኛ በማንሳት መልካም ተግባር ላከናወኑ ኦፊሰሮች የእውቅና ሽልማት ሰጠ
07/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን " በጎነታችን የማንነታችን መገለጫ የተቋማችን ድንቅ ተግባር ማሳያ ነው" በሚል መሪ ቃል በጎ ተግባር ላከናወኑ የአቃቂ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ለሶስት ኦፊሰሮች የእውቅና ሽልማት መርሐ ግብር አካሂዷል ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ተቋሙ ከሚሰራው የደንብ ማስከበር ስራዎች በተጨማሪ መልካም ስነምግባርና ቅን ልብ ያላቸውን ኦፊሰሮች የተቋሙን ገጽታ በመገንባት ለሌሎች አርአያ መሆን በመቻላቸው እንደ ተቋም እውቅና መሰጠቱን ገልጸዋል ።
አክለውም በቀጣይ በስነምግባር በመታነጽ የደንብ መተላለፍ ተግባሮችን በመከላከል ትኩረት እያደረግን ውጤታማ እንድንሆን አደራ በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ።
በመድረኩ የተገኙት የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አለማየሁ ሜጀና ደንብ ማስከበር በ7/24 የስራ ባህል በመስራት በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች እንዲቀንስ ከማስቻሉም በላይ ቅን ልቦና ባላቸው ኦፊሰሮች አማካኝነት የተቋሙን መገንባት ተችሏል ሲሉ ገልጸዋል ።
በዚህ በጎ ተግባር ላይ ተሳትፋችሁ ለሌሎች በርካታ ዜጎች ምሳሌ ስለሆናችሁ በራሴ እና በክ/ከተማው ስም ከፍተኛ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ሲሉ ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል ።
የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አባል የሆኑት ኦፊሰር ተስፋሁን እነ ኦፊሰር ሌንሳ ባከናወኑት በጎ ተግባር አማካኝነት እንዲሁም በሶሻል ሚዲያ መልካም ተግባር በማሰራጨት ኦፊሰር ይርጋለም የተቋም ግንባታ ስራ በመስራታቸው በጋራ ተሰብስበን የባለስልጣኑ ዋና ሰራ አስኪያጅና የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ በተገኙበት እውቅና ለመስጠት በዛሬው ዕለት ተገኝተናል ሲሉ የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኜ ሂርፓሳ ተናግረዋል ።
በመድረኩ ቅን ልቦና ላላቸው ኦፊሰሮች ላደረጉት መልካም ተግባር የስማርት ስልክ በስጦታ መልክ ተበርክቶላቸዋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
07/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን " በጎነታችን የማንነታችን መገለጫ የተቋማችን ድንቅ ተግባር ማሳያ ነው" በሚል መሪ ቃል በጎ ተግባር ላከናወኑ የአቃቂ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ለሶስት ኦፊሰሮች የእውቅና ሽልማት መርሐ ግብር አካሂዷል ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ተቋሙ ከሚሰራው የደንብ ማስከበር ስራዎች በተጨማሪ መልካም ስነምግባርና ቅን ልብ ያላቸውን ኦፊሰሮች የተቋሙን ገጽታ በመገንባት ለሌሎች አርአያ መሆን በመቻላቸው እንደ ተቋም እውቅና መሰጠቱን ገልጸዋል ።
አክለውም በቀጣይ በስነምግባር በመታነጽ የደንብ መተላለፍ ተግባሮችን በመከላከል ትኩረት እያደረግን ውጤታማ እንድንሆን አደራ በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ።
በመድረኩ የተገኙት የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አለማየሁ ሜጀና ደንብ ማስከበር በ7/24 የስራ ባህል በመስራት በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች እንዲቀንስ ከማስቻሉም በላይ ቅን ልቦና ባላቸው ኦፊሰሮች አማካኝነት የተቋሙን መገንባት ተችሏል ሲሉ ገልጸዋል ።
በዚህ በጎ ተግባር ላይ ተሳትፋችሁ ለሌሎች በርካታ ዜጎች ምሳሌ ስለሆናችሁ በራሴ እና በክ/ከተማው ስም ከፍተኛ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ሲሉ ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል ።
የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አባል የሆኑት ኦፊሰር ተስፋሁን እነ ኦፊሰር ሌንሳ ባከናወኑት በጎ ተግባር አማካኝነት እንዲሁም በሶሻል ሚዲያ መልካም ተግባር በማሰራጨት ኦፊሰር ይርጋለም የተቋም ግንባታ ስራ በመስራታቸው በጋራ ተሰብስበን የባለስልጣኑ ዋና ሰራ አስኪያጅና የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ በተገኙበት እውቅና ለመስጠት በዛሬው ዕለት ተገኝተናል ሲሉ የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኜ ሂርፓሳ ተናግረዋል ።
በመድረኩ ቅን ልቦና ላላቸው ኦፊሰሮች ላደረጉት መልካም ተግባር የስማርት ስልክ በስጦታ መልክ ተበርክቶላቸዋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡