በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የአቅመ ደካማ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቱ ቁልፍ አስረከበ
09/12/ 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በክረምት በጎ ፍቃድ ስራ በወረዳ 02 ያስገነባውን የአቅመ ደካማ ቤት በማጠናቀቅ ለባለቤቱ አስረክቧል።
በፕሮግራሙ የተገኙት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ደንብ ማስከበር በከተማችን የሚስተዋሉ ደንብ መተላለፎችንና ህገ-ወጥ ተግባራትን ከመከላከል ጎን ለጎን ወደ ማህበረሰቡ በመውረድ ችግር ፈቺ የሆኑ ሰው ተኮር የበጎፍቃድ ስራዎችን በመስራት የችግኝ ተከላ፣ የደም ልገሳ፣የማዕድ ማጋራትና የቤት ዕድሳት ተግባራትን በማከናወን ለህብረተሰቡ ያለውን አለኝታነቱ በተግባር እያረጋገጠ መሆኑ ገልጸዋል ።
አክለውም የተጀመረው ሰው ተኮር በጎ ተግባር በቀጣይም በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል ።
በመርሐ ግብሩ ንግግር ያደረጉት የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አቶ አበራ ኢቲቻ በክረምት የዘጠና ቀናት ዕቅድ 2 ቤቶችን ለመገንባትና ለማደስ ታቅዶ በዛሬው ዕለት አንዱን ቤት በራስ አቅም ኦፊሰሮችን ባለሀብቶችን በማስተባበር ከፈረሳ ጀምሮ እስከሚጠናቀቅ በየጊዜው ክትትል በማድረግና ሁሉም አካል የበኩሉን ሚና በመወጣት 1.3 ሚሊዩን ብር በላይ ወጪ ተደረጎበት ለምረቃ መብቃቱን ገልጸዋል ።
የቤት እድሳት የተደረገላቸው ወ/ሮ ውዴ ያኢ በተደረገላቸው በጎ ተግባር መደሰታቸውን በመግለፅ በተግባሩ ለተሳተፉ በሙሉ ላቅ ያለ ምሳጋቸውን አቅርበዋል።
በምረቃ ፕሮግራሙ የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ፣የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አቶ አበራ ኢቲቻ ፣ የክ/ከተማው የህብረተሰብ ተሳትፎና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ኤርሚሾ ፣ የወረዳ 02 ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አዱኛ ዘነበ ፣የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ ኦፊሰሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
የቤት ግንባታው ሲከናወን ድጋፍ ላደረጉ እና ለአስተባበሩ አካላት የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቷል ።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
09/12/ 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በክረምት በጎ ፍቃድ ስራ በወረዳ 02 ያስገነባውን የአቅመ ደካማ ቤት በማጠናቀቅ ለባለቤቱ አስረክቧል።
በፕሮግራሙ የተገኙት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ደንብ ማስከበር በከተማችን የሚስተዋሉ ደንብ መተላለፎችንና ህገ-ወጥ ተግባራትን ከመከላከል ጎን ለጎን ወደ ማህበረሰቡ በመውረድ ችግር ፈቺ የሆኑ ሰው ተኮር የበጎፍቃድ ስራዎችን በመስራት የችግኝ ተከላ፣ የደም ልገሳ፣የማዕድ ማጋራትና የቤት ዕድሳት ተግባራትን በማከናወን ለህብረተሰቡ ያለውን አለኝታነቱ በተግባር እያረጋገጠ መሆኑ ገልጸዋል ።
አክለውም የተጀመረው ሰው ተኮር በጎ ተግባር በቀጣይም በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል ።
በመርሐ ግብሩ ንግግር ያደረጉት የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አቶ አበራ ኢቲቻ በክረምት የዘጠና ቀናት ዕቅድ 2 ቤቶችን ለመገንባትና ለማደስ ታቅዶ በዛሬው ዕለት አንዱን ቤት በራስ አቅም ኦፊሰሮችን ባለሀብቶችን በማስተባበር ከፈረሳ ጀምሮ እስከሚጠናቀቅ በየጊዜው ክትትል በማድረግና ሁሉም አካል የበኩሉን ሚና በመወጣት 1.3 ሚሊዩን ብር በላይ ወጪ ተደረጎበት ለምረቃ መብቃቱን ገልጸዋል ።
የቤት እድሳት የተደረገላቸው ወ/ሮ ውዴ ያኢ በተደረገላቸው በጎ ተግባር መደሰታቸውን በመግለፅ በተግባሩ ለተሳተፉ በሙሉ ላቅ ያለ ምሳጋቸውን አቅርበዋል።
በምረቃ ፕሮግራሙ የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ፣የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት አቶ አበራ ኢቲቻ ፣ የክ/ከተማው የህብረተሰብ ተሳትፎና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ኤርሚሾ ፣ የወረዳ 02 ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አዱኛ ዘነበ ፣የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ ኦፊሰሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
የቤት ግንባታው ሲከናወን ድጋፍ ላደረጉ እና ለአስተባበሩ አካላት የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቷል ።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍6👏1
ባለስልጣኑ የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር አከናወነ
12- 12- 2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ መግቢያ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ፕሮግራም ከማዕከሉ ሰራተኞች ጋር አካሂዳል፡፡
በዕለቱ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ የስነምግባርና የጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬእተር እንደገለፁት በሳምንቱ ያሉትን የስራ ጊዜያቶች በንቃት ለማሳለፍና በሰራተኞች መካከል ያለውን ግንኙነት በማጠናከር ተቀራርቦ ለመስራት ፕሮግራሙ የሚያግዝ ነው በማለት የመልካም ሳምንት ምኞታቸውን ገልጸዋል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ የህግ ቡድን መሪ አቶ ብርሃኑ ኮርሳ የራሳቸውን የህይወት ተሞክሮ ለሰራተኞች ልምድና እውቀት ይሆን ዘንድ አካፍለዋል ።
በተጨማሪም የቤተሰብ ሕግን በተመለከተ ያዘጋጁትን ሰነድ ለሰራተኛው በሚመጥን መልኩ በዝርዝር አቅርበዋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
12- 12- 2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ መግቢያ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ፕሮግራም ከማዕከሉ ሰራተኞች ጋር አካሂዳል፡፡
በዕለቱ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ የስነምግባርና የጸረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬእተር እንደገለፁት በሳምንቱ ያሉትን የስራ ጊዜያቶች በንቃት ለማሳለፍና በሰራተኞች መካከል ያለውን ግንኙነት በማጠናከር ተቀራርቦ ለመስራት ፕሮግራሙ የሚያግዝ ነው በማለት የመልካም ሳምንት ምኞታቸውን ገልጸዋል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ የህግ ቡድን መሪ አቶ ብርሃኑ ኮርሳ የራሳቸውን የህይወት ተሞክሮ ለሰራተኞች ልምድና እውቀት ይሆን ዘንድ አካፍለዋል ።
በተጨማሪም የቤተሰብ ሕግን በተመለከተ ያዘጋጁትን ሰነድ ለሰራተኛው በሚመጥን መልኩ በዝርዝር አቅርበዋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍4
ዛሬ የ90 ቀን የሁለት ወር ሥራ አፈፃፀም ገምግመናል::
የአገልግሎት አሰጣጥ ማዘመን እና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የሚቀርቡ ግብአቶች አቅርቦትን ፣ የገበያ ማረጋጋት ፣የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፣ የፕሮጀክቶች ግንባታ፣ የገቢ አፍፃፀም እና ለኮንፍረንስ የቱሪዝምን ምቹ ሁኔታ መፍጠር በትኩረት ገምግመናል።
በዚህም የሁለቱ ወር ስራ አፍፃፀም ውጤታማ እንደነበረም በርካታ ማሳያዎች ቀርበዋል ።በተለይ ከኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ ምርቶች በስፋት ወደ ከተማው መግባታቸው ፣ የገቢ አፈፃፀም፣ የክረምት በጐ ፍቃድ አገልግሎት፣ የስራ እድል ፈጠራ እና የፕሮጀክቶች አፈፃፀም የተሻሉ እንደነበራቸው አይተናል።
በሌላ በኩል ደግሞ መሻሻል የሚገባቸው እና በክፍታት የታዩትን በፍጥነት እንዲታረም አቅጣጫ አስቀምጠናል።ከቀጣዩ ሳምንት ጀምሮ የሚከናወኑት 2ተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ እንዲሁም የካሪቢያን መሪዎች ታላላቅ ስብስባ እና ጉባኤን በፍጹም ፀጥታ፣ በትሁት ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ ተቀብለን ለማስተናገድ ከወትሮው የተለያ ርብርብ እንድናደርግ ፤ ሁሉም የከተማው አመራር በትኩረት እንዲሰራ ተግባብተናል::
ማህበረሰባችንም ለእንግዶቻችን ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን በተግባር እንድናስይ ስል በአክብሮት እጠይቃለሁ::
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ !
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የአገልግሎት አሰጣጥ ማዘመን እና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የሚቀርቡ ግብአቶች አቅርቦትን ፣ የገበያ ማረጋጋት ፣የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፣ የፕሮጀክቶች ግንባታ፣ የገቢ አፍፃፀም እና ለኮንፍረንስ የቱሪዝምን ምቹ ሁኔታ መፍጠር በትኩረት ገምግመናል።
በዚህም የሁለቱ ወር ስራ አፍፃፀም ውጤታማ እንደነበረም በርካታ ማሳያዎች ቀርበዋል ።በተለይ ከኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ ምርቶች በስፋት ወደ ከተማው መግባታቸው ፣ የገቢ አፈፃፀም፣ የክረምት በጐ ፍቃድ አገልግሎት፣ የስራ እድል ፈጠራ እና የፕሮጀክቶች አፈፃፀም የተሻሉ እንደነበራቸው አይተናል።
በሌላ በኩል ደግሞ መሻሻል የሚገባቸው እና በክፍታት የታዩትን በፍጥነት እንዲታረም አቅጣጫ አስቀምጠናል።ከቀጣዩ ሳምንት ጀምሮ የሚከናወኑት 2ተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ እንዲሁም የካሪቢያን መሪዎች ታላላቅ ስብስባ እና ጉባኤን በፍጹም ፀጥታ፣ በትሁት ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ ተቀብለን ለማስተናገድ ከወትሮው የተለያ ርብርብ እንድናደርግ ፤ ሁሉም የከተማው አመራር በትኩረት እንዲሰራ ተግባብተናል::
ማህበረሰባችንም ለእንግዶቻችን ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን በተግባር እንድናስይ ስል በአክብሮት እጠይቃለሁ::
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ !
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍2