ባለስልጣኑ በተግባቦት ፣ በመረጃ አያያዝ እና የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም በተመለከተ ስልጠና ሰጠ ።
መጋቢት 12/ 2016 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በክፍለ ከተማ እና በወረዳ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤቶች በኮሙኒኬሽን እና ሶሻል ሚዲያ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች በተግባቦት ፣በመረጃ አያያዝ እና በሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ እንደተናገሩት ባለስልጣኑ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ የሚዲያ አግባቦችን በመጠቀም ላይ ይገኛል ይህንንም ስራ በጋራ ለማሳለጥ ከክ/ከተማ እስከ ወረዳ ድረስ የመረጃ ቅብብሎሹን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
ሀላፊው አያይዘው የተቋሙን ገጽታ በመገንባት ለደንብ ማስከበር ስራ ህብረተሰቡ አዎንታዊ አመለካከት እንዲኖረው እና ህገ-ወጥነትን የሚኮንን ዜጋን ለማፍራት ተግባቦት እና ሚዲያ ሚናው ከፍተኛ ስለሆነ ስልጠናው እንደሚያግዝ ገልፀው በቀጣይ የተሰጠውን ስልጠና ተግባራዊ በማድረግ ከሰልጣኞች እና ሁሉም የተቋሙ ባለሙያዎች በተቋሙ ገጽታ ግንባታ ስራው የበኩሉን እንዲወጣ አሳስበዋል ።
በተግባቦት፣በመረጃ አያያዝ እና የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ የተዘጋጀው ስልጠና በባለስልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ የምስራች ግርማ የተቋሙን ተግባራት ማዕከል ባደረገ መልኩ ሰጥተዋል።
የስልጠናው ዓላማ በተቋሙ የሚሰሩ ስራዎችን ለማህበረሰቡ ለማስተዋወቅ ፣ሶሻል ሚድያ በመጠቀም የተቋሙ የመረጃ ልውውጥ ተደራሽ ለማድረግና ተቋሙ በየጊዜው የሚከፈትበትን የሶሻል ሚድያ ስም ማጥፋት ዘመቻ ሰራተኛው ትግል በማድረግ ትክክለኛውና የተደራጀ መረጃ ለህብረተሰቡ እንዲሰጥ ለማስቻል መሆኑ ተገልጿል ።
የሚዲያ አካላትን በአግባቡ ከተጠቀምንባቸው የተቋምና የሀገር ገጽታ ከመገንባት ባለፈ ለሀገራችን ሰላም ከፍተኛ ሚና ያለው ሲሆን ያለአግባብ ከተጠቀምንበት ከፍተኛ ጉዳት የሚያመጣ መሆኑን በመገንዘብ ማህበራዊ ሚዲያን ለመልካም ተግባርና ለሀገር ግንባታ ልንጠቀምበት እንደሚገባ በስልጠናው ተገልጿል።
በመጨረሻም ከሰልጣኞች ጋር በቀጣይ በጋራ በተቀናጀና በተናበበ ሁኔታ ለመስራት ውይይት በማድረግ ከሰልጣኞች ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች በባለስልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ የምሰራች ግርማ እና የሬ/ቴ/ህ/ዝግጅት ቡድን መሪ በአቶ ሄኖክ ታደሰ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ስልጠናው ተጠናቋል ።
ዘገበው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የትዊተር/X/ ሚዲያ ገፃችን
https://x.com/Addis_Denb?t=u8wW3qnxWk48GYzJ4RD96Q&s=09
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ!
መጋቢት 12/ 2016 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በክፍለ ከተማ እና በወረዳ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤቶች በኮሙኒኬሽን እና ሶሻል ሚዲያ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች በተግባቦት ፣በመረጃ አያያዝ እና በሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ እንደተናገሩት ባለስልጣኑ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ የሚዲያ አግባቦችን በመጠቀም ላይ ይገኛል ይህንንም ስራ በጋራ ለማሳለጥ ከክ/ከተማ እስከ ወረዳ ድረስ የመረጃ ቅብብሎሹን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
ሀላፊው አያይዘው የተቋሙን ገጽታ በመገንባት ለደንብ ማስከበር ስራ ህብረተሰቡ አዎንታዊ አመለካከት እንዲኖረው እና ህገ-ወጥነትን የሚኮንን ዜጋን ለማፍራት ተግባቦት እና ሚዲያ ሚናው ከፍተኛ ስለሆነ ስልጠናው እንደሚያግዝ ገልፀው በቀጣይ የተሰጠውን ስልጠና ተግባራዊ በማድረግ ከሰልጣኞች እና ሁሉም የተቋሙ ባለሙያዎች በተቋሙ ገጽታ ግንባታ ስራው የበኩሉን እንዲወጣ አሳስበዋል ።
በተግባቦት፣በመረጃ አያያዝ እና የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ የተዘጋጀው ስልጠና በባለስልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ የምስራች ግርማ የተቋሙን ተግባራት ማዕከል ባደረገ መልኩ ሰጥተዋል።
የስልጠናው ዓላማ በተቋሙ የሚሰሩ ስራዎችን ለማህበረሰቡ ለማስተዋወቅ ፣ሶሻል ሚድያ በመጠቀም የተቋሙ የመረጃ ልውውጥ ተደራሽ ለማድረግና ተቋሙ በየጊዜው የሚከፈትበትን የሶሻል ሚድያ ስም ማጥፋት ዘመቻ ሰራተኛው ትግል በማድረግ ትክክለኛውና የተደራጀ መረጃ ለህብረተሰቡ እንዲሰጥ ለማስቻል መሆኑ ተገልጿል ።
የሚዲያ አካላትን በአግባቡ ከተጠቀምንባቸው የተቋምና የሀገር ገጽታ ከመገንባት ባለፈ ለሀገራችን ሰላም ከፍተኛ ሚና ያለው ሲሆን ያለአግባብ ከተጠቀምንበት ከፍተኛ ጉዳት የሚያመጣ መሆኑን በመገንዘብ ማህበራዊ ሚዲያን ለመልካም ተግባርና ለሀገር ግንባታ ልንጠቀምበት እንደሚገባ በስልጠናው ተገልጿል።
በመጨረሻም ከሰልጣኞች ጋር በቀጣይ በጋራ በተቀናጀና በተናበበ ሁኔታ ለመስራት ውይይት በማድረግ ከሰልጣኞች ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች በባለስልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ የምሰራች ግርማ እና የሬ/ቴ/ህ/ዝግጅት ቡድን መሪ በአቶ ሄኖክ ታደሰ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ስልጠናው ተጠናቋል ።
ዘገበው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
የትዊተር/X/ ሚዲያ ገፃችን
https://x.com/Addis_Denb?t=u8wW3qnxWk48GYzJ4RD96Q&s=09
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ!
👍2
ኘረስ ሪሊዝ
ባለስልጣኑ በ2016 ዓ.ም በመጀመሪያው ስድስት ወራት የላቀ የእቅድ አፈፃፀም ላስመዘገቡ አካላት ዕውቅና ሊሰጥ ነው።
መጋቢት 20/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2016 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የላቀ እቅድ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ለማዕከል ዳይሬክቶሬቶችና ቡድኖች እንዲሁም ለክፍለ ከተማና ለወረዳ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤቶች እውቅና በመስጠት የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ሊያበረክት መሆኑ ተገልጿል።
እውቅናው በነገው እለት ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በጌት ፋም ሆቴል የከተማውና የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላው እንግዶች በተገኙበት በእቅዳቸው መሠረት ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት እውቅናው እንደሚሰጥ የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ ጠቁመዋል።
መረጃው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ባለስልጣኑ በ2016 ዓ.ም በመጀመሪያው ስድስት ወራት የላቀ የእቅድ አፈፃፀም ላስመዘገቡ አካላት ዕውቅና ሊሰጥ ነው።
መጋቢት 20/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2016 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የላቀ እቅድ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ለማዕከል ዳይሬክቶሬቶችና ቡድኖች እንዲሁም ለክፍለ ከተማና ለወረዳ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤቶች እውቅና በመስጠት የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ሊያበረክት መሆኑ ተገልጿል።
እውቅናው በነገው እለት ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በጌት ፋም ሆቴል የከተማውና የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላው እንግዶች በተገኙበት በእቅዳቸው መሠረት ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት እውቅናው እንደሚሰጥ የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ ጠቁመዋል።
መረጃው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍6
ባለስልጣኑ የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም የእውቅና እና ሽልማት ፕሮግራም አካሄደ ።
መጋቢት 21/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2016 ግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት የእውቅና ሽልማት ፕሮግራም በጌትፋም ሆቴል አካሄደ ።
በፕሮግራሙ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የፍትህና የመልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ፣ የከተማው ሰላምና ፀጥታና የባለስልጣኑ ከፍተኛ ኃላፊዎች ፣ የክ/ከተማና የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ የሀይማኖት አባቶች ፣ አርቲስቶች ፣ የማዕከሉ ዳይሬክተሮች ፣ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት ባለስልጣኑ በአዋጅ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃትና በጥራት እየተወጣ የሚገኝ ሲሆን ለስራዎቻችን መሳካት ከፍተኛ ሚና የተጫወቱት አካላት እነማን ናቸው ሚለውን ምዘና በማካሄድ በመለየት በዛሬው ዕለት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ እውቅናና ሽልማት በመስጠት ማበረታት ለቀጣይ ስራችንን መሳካት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል ።
ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የመንግስትና የህዝብ ሀብት የሆነውንን መሬት በልዩ ትኩረት በመጠበቅ በተያዘው በጀት ዓመት ምንም አይነት ወረራ እንዳየፈጸም ማድረግ ችሏል ።
የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎች በማጠናከር ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት በመስራት በከተማችን የሚታዪ የደንብ ጥሰቶችን በመከላከል በመቆጣጠርና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ እርምጃ በመውሰድ ከተማችን የደንብ ጥሰት የቀነሰባት እንደ ስሟ አዲስና ውብ እንድትሆን በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ዋና ሰራ አስኪያጁ ተናግረዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ 2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም የምዘና ዉጤት ትንተና ማጠቃለያ ሰነድ በባለስልጣኑ የለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ ቀርቧል።
በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የፍትህና የመልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ አንደተናገሩት ደንብ ማስከበር ደንብ ጥሰትን ከመከላከል ጎን ለጎን ከጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ ከማስጠበቅ አንጻር እየሰራ ያለው ስራ ሊበረታታ እእንደሚገባ በመግለፅ ህብረተሰቡ በቀጣይ የደንብ ማስከበር ስራን በመገንዘብ በሚያከናውናቸው ተግባራት ላይ ከጎኑ ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የፍትህና የመልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ ፣የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ፣ ም/ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አበባ እሸቴ ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶበታል
በ2016 ግማሽ ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ክ/ከተማና ወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ፣ የማዕከል ዳይሬክቶሬትና ቡድን መሪዎች የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ።
በዚህም መሰረት ከ 11 ክ/ከተማ ከ1ኛ አስከ 3ኛ የወጡት
1ኛ ጉለሌ ክፍለ ከተማ
2ኛ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ
3ኛ ልደታ ክፍለ ከተማ የእውቅና ሽልማትና ላፕቶፕ ተበርክቶላቸዋል
ከ119 ወረዳዎች ከ1ኛ አስከ 3ኛ የወጡት
1ኛ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወረዳ 11
2ኛ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 7
3ኛ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 5 እና ጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 5 የኮምፒውተር ሽልማትና ተበርክቶላቸዋል።
ከማዕከል ዳይሬክቶሬት ከ1ኛ አስከ 3ኛ የወጡት
1ኛ የደንብ መተላለፍ ክትትልና ቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት
2ኛ የስልጠናና ጥናት ዳይሬክቶሬት
3ኛ ደንብ መተላለፍ መከላከል ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት
ከማዕከል ቡድን ከ1ኛ አስከ 3ኛ የወጡት
1ኛየንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ቡድን
2ኛ የስልጠና ቡድን
3ኛ የሲቪል የሰው ሀይል ቡድን
ዘገባው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን
መጋቢት 21/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2016 ግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት የእውቅና ሽልማት ፕሮግራም በጌትፋም ሆቴል አካሄደ ።
በፕሮግራሙ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የፍትህና የመልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ፣ የከተማው ሰላምና ፀጥታና የባለስልጣኑ ከፍተኛ ኃላፊዎች ፣ የክ/ከተማና የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ የሀይማኖት አባቶች ፣ አርቲስቶች ፣ የማዕከሉ ዳይሬክተሮች ፣ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት ባለስልጣኑ በአዋጅ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃትና በጥራት እየተወጣ የሚገኝ ሲሆን ለስራዎቻችን መሳካት ከፍተኛ ሚና የተጫወቱት አካላት እነማን ናቸው ሚለውን ምዘና በማካሄድ በመለየት በዛሬው ዕለት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ እውቅናና ሽልማት በመስጠት ማበረታት ለቀጣይ ስራችንን መሳካት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል ።
ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የመንግስትና የህዝብ ሀብት የሆነውንን መሬት በልዩ ትኩረት በመጠበቅ በተያዘው በጀት ዓመት ምንም አይነት ወረራ እንዳየፈጸም ማድረግ ችሏል ።
የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎች በማጠናከር ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት በመስራት በከተማችን የሚታዪ የደንብ ጥሰቶችን በመከላከል በመቆጣጠርና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ እርምጃ በመውሰድ ከተማችን የደንብ ጥሰት የቀነሰባት እንደ ስሟ አዲስና ውብ እንድትሆን በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ዋና ሰራ አስኪያጁ ተናግረዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ 2016 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም የምዘና ዉጤት ትንተና ማጠቃለያ ሰነድ በባለስልጣኑ የለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ቀጸላ ቀርቧል።
በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የፍትህና የመልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ አንደተናገሩት ደንብ ማስከበር ደንብ ጥሰትን ከመከላከል ጎን ለጎን ከጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ ከማስጠበቅ አንጻር እየሰራ ያለው ስራ ሊበረታታ እእንደሚገባ በመግለፅ ህብረተሰቡ በቀጣይ የደንብ ማስከበር ስራን በመገንዘብ በሚያከናውናቸው ተግባራት ላይ ከጎኑ ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳብና ጥያቄዎች የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የፍትህና የመልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ ፣የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ፣ ም/ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አበባ እሸቴ ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶበታል
በ2016 ግማሽ ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ክ/ከተማና ወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ፣ የማዕከል ዳይሬክቶሬትና ቡድን መሪዎች የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ።
በዚህም መሰረት ከ 11 ክ/ከተማ ከ1ኛ አስከ 3ኛ የወጡት
1ኛ ጉለሌ ክፍለ ከተማ
2ኛ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ
3ኛ ልደታ ክፍለ ከተማ የእውቅና ሽልማትና ላፕቶፕ ተበርክቶላቸዋል
ከ119 ወረዳዎች ከ1ኛ አስከ 3ኛ የወጡት
1ኛ ኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወረዳ 11
2ኛ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 7
3ኛ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 5 እና ጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 5 የኮምፒውተር ሽልማትና ተበርክቶላቸዋል።
ከማዕከል ዳይሬክቶሬት ከ1ኛ አስከ 3ኛ የወጡት
1ኛ የደንብ መተላለፍ ክትትልና ቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት
2ኛ የስልጠናና ጥናት ዳይሬክቶሬት
3ኛ ደንብ መተላለፍ መከላከል ግንዛቤ ማስጨበጥ ዳይሬክቶሬት
ከማዕከል ቡድን ከ1ኛ አስከ 3ኛ የወጡት
1ኛየንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ቡድን
2ኛ የስልጠና ቡድን
3ኛ የሲቪል የሰው ሀይል ቡድን
ዘገባው ፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን
👍6