ባለስልጣጣኑ "ሰው ተኮር ተግባሮቻችን ለአብሮነታችን" በሚል መሪ ቃል የአቅመ ደካማ እናት ቤት እድሳት አጠናቆ ለባለቤቱ የቁልፍ ርክክብ አደረገ
13/06/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ "ሰው ተኮር ተግባሮቻችን ለአብሮነታችን" በሚል መሪ ቃል በወረዳ 02 ለሚገኙ አቅመ ደካማ የመኖሪያ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቶቹ አስረከበ፡፡
በቤቱ ምርቃት መርሀ-ግብር ላይ የአዲስ አበባ የደንብ ማስከበር ባለ ስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ ፣የወረዳ ደንብ ማስከበር አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በፕሮግራሙ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ተቋሙ ደንብ መተላለፎችንና ህገ-ወጥ ተግባራትን ከመከላከል ጎን ለጎን ወደ ማህበረሰቡ በመውረድ ሰው ተኮር የበጎፍቃድ ስራዎችን በመስራት ለህብረተሰቡ ያለውን አለኝታነት በተግባር እያሳየ ይገኛል ይህ ሰው ተኮር በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በምርቃት ፕሮግራሙ የኮልፌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ በኑሮአቸው ዝቅተኛ ገቢ ላላቸውና ረዳት ለሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች በሰው ተኮር ተግባራት ላይ በመሳተፍ በክ/ከተማው በቤት እድሳት፣ማእድ በማጋራትና በሌሎች የተለያዩ ሰው ተኮር ስራዎች እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡
አክለውም የብልፅግና እሳቤ ከሆነው የሰው ተኮር ስራ አንዱ በዛሬው እለት በክፍለ ከተማው ያሉ ወረዳዎችን በማስተባበር የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት በማጠናቀቅ ለባለቤቱ አስረክበዋል በቤት እድሳት ወቅት አስተዋጾ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
የቤት እድሳት የተደረገላት የወረዳ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ሙሪዳ አወል ከደንብ ማስከበር አመራርና አባላት ለተደረገላቸው ድጋፍ ከልብ አመስግነዋል፡፡
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
13/06/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ "ሰው ተኮር ተግባሮቻችን ለአብሮነታችን" በሚል መሪ ቃል በወረዳ 02 ለሚገኙ አቅመ ደካማ የመኖሪያ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቶቹ አስረከበ፡፡
በቤቱ ምርቃት መርሀ-ግብር ላይ የአዲስ አበባ የደንብ ማስከበር ባለ ስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ ፣የወረዳ ደንብ ማስከበር አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በፕሮግራሙ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ተቋሙ ደንብ መተላለፎችንና ህገ-ወጥ ተግባራትን ከመከላከል ጎን ለጎን ወደ ማህበረሰቡ በመውረድ ሰው ተኮር የበጎፍቃድ ስራዎችን በመስራት ለህብረተሰቡ ያለውን አለኝታነት በተግባር እያሳየ ይገኛል ይህ ሰው ተኮር በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በምርቃት ፕሮግራሙ የኮልፌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ጎንፋ በኑሮአቸው ዝቅተኛ ገቢ ላላቸውና ረዳት ለሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች በሰው ተኮር ተግባራት ላይ በመሳተፍ በክ/ከተማው በቤት እድሳት፣ማእድ በማጋራትና በሌሎች የተለያዩ ሰው ተኮር ስራዎች እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡
አክለውም የብልፅግና እሳቤ ከሆነው የሰው ተኮር ስራ አንዱ በዛሬው እለት በክፍለ ከተማው ያሉ ወረዳዎችን በማስተባበር የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት በማጠናቀቅ ለባለቤቱ አስረክበዋል በቤት እድሳት ወቅት አስተዋጾ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
የቤት እድሳት የተደረገላት የወረዳ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ሙሪዳ አወል ከደንብ ማስከበር አመራርና አባላት ለተደረገላቸው ድጋፍ ከልብ አመስግነዋል፡፡
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
👍2
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2017 የግማሽ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም የእውቅናና ሽልማት ፕሮግራም አካሂዷል ።
15 /06 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2017 የመጀመሪያ ስድሰት ወር የእቅድ አፈጻጸም የእውቅና እና ሽልማት ፕሮግራም አካሄደ ።
በመርሀ ግብሩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ውቢት ዮሐንስ፣ የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ፣ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ፣ ሌሎች አመራሮችና የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ ኦፊሰሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በመድረኩ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት ተቋሙ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ እየሠራና እንዲሁም ስራዎችን በቴክኖሎጂ በማዘመን ውጤታማ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝና የኦፊሰሮችን ጥቅማ ጥቅም ለማስጠበቅ ሰፊ ስራ አየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል።
በዋናነትም ማንኛውንም የተቋሙን ተልዕኮ ስንወጣ በፍጹም ስነ-ምግባርና ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ ኃላፊነታችን በታማኝነት አንወጣ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመድረኩ የተገኙት የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ውቢት ዮሐንስ በክ/ከተማው ሚሰተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በመከላከል በመቆጣጠርና እርምጃ በመውሰድ እና የአደባባይ በአላትና የአፍርካ ህብረት ጉባኤ ሰላማዊ ሆኖ ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ የደንብ ማስከበር ተቋም ከሌሎች አካላት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ስራዎችን መሰራቱንና ክ/ከተማውም እውቅና መስጠቱን አሰታውቀዋል፡፡
የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ በግማሽ ዓመቱ በክ/ከተማው እንደ ጽ/ቤት የነበረውን እቅድ አፈጻጸም ሲገልጹ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ በመወጣት ህገወጥነትንና ደንብ ጥሰቶችን በመከላከልና በመቆጣጠር ደንብ ተላላፊ ከሆኑ አካላት ከቅጣት 7 ሚሊዮን ብር ለመንግስት ገቢ መደረጉን ገልፀዋል።
በመጨረሻም በ2017በጀት ዓመት በስድስት ወራት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቶች የእውቅናና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን
1ኛ ወረዳ 01
2ኛ ወረዳ 03
3ኛ ወረዳ 05 በመሆናቸው የዋንጫና ሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆነዋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
15 /06 /2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2017 የመጀመሪያ ስድሰት ወር የእቅድ አፈጻጸም የእውቅና እና ሽልማት ፕሮግራም አካሄደ ።
በመርሀ ግብሩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ውቢት ዮሐንስ፣ የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ፣ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ፣ ሌሎች አመራሮችና የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ ኦፊሰሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በመድረኩ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደተናገሩት ተቋሙ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ እየሠራና እንዲሁም ስራዎችን በቴክኖሎጂ በማዘመን ውጤታማ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝና የኦፊሰሮችን ጥቅማ ጥቅም ለማስጠበቅ ሰፊ ስራ አየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል።
በዋናነትም ማንኛውንም የተቋሙን ተልዕኮ ስንወጣ በፍጹም ስነ-ምግባርና ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ ኃላፊነታችን በታማኝነት አንወጣ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመድረኩ የተገኙት የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ውቢት ዮሐንስ በክ/ከተማው ሚሰተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በመከላከል በመቆጣጠርና እርምጃ በመውሰድ እና የአደባባይ በአላትና የአፍርካ ህብረት ጉባኤ ሰላማዊ ሆኖ ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ የደንብ ማስከበር ተቋም ከሌሎች አካላት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ስራዎችን መሰራቱንና ክ/ከተማውም እውቅና መስጠቱን አሰታውቀዋል፡፡
የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ኢቲቻ በግማሽ ዓመቱ በክ/ከተማው እንደ ጽ/ቤት የነበረውን እቅድ አፈጻጸም ሲገልጹ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ በመወጣት ህገወጥነትንና ደንብ ጥሰቶችን በመከላከልና በመቆጣጠር ደንብ ተላላፊ ከሆኑ አካላት ከቅጣት 7 ሚሊዮን ብር ለመንግስት ገቢ መደረጉን ገልፀዋል።
በመጨረሻም በ2017በጀት ዓመት በስድስት ወራት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቶች የእውቅናና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን
1ኛ ወረዳ 01
2ኛ ወረዳ 03
3ኛ ወረዳ 05 በመሆናቸው የዋንጫና ሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆነዋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
አራዳ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2017 በጀት አመት የ6 ወር እቅድ አፈጻጸም የእውቅና የሽልማት መርሃ ግብር አካሄደ
የካቲት 16/2017 ዓ.ም
**አዲስ አባባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ በኮሪደር ልማት ስራዎች እና የ2017 በጀት አመት የ6 ወር እቅድ አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና ሽልማት መርሃ ግብር አካሂዷል።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው፣ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ምክትል ሀላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ ፣የአራዳ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጌታሁን አበራ፣ሌሎች የክ/ከተማው ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣የመከላከያ፣ የፌደራል እና የከተማው የፖሊስ አባላት፣ ባለድርሻ አካላት ፣ የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ ኦፊሰሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የሀይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ዓለምን ያስደመመው አፍሪካውያንን ያነጋገረ የአዲስ አበባ የልማት ስራ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አባሎቻችን እና ባለድርሻ አካሎች ከልብ አመስግነው የመጀመሪያ የኮሪደር ልማት ስረሠ የተጀመረው በአራዳ ክፍለ ከተማ ላይ ነው የአራዳ ክፍለ ከተማ ነው ለዚህም ትልቁ ኃይላችን የደንብ ማስከበር እንደነበር ገልጸዋል።
በዚህም ኦፊሰሩ ለልማት የተነሱ እናቶቻችን እና አባቶቻችን ያለምንም ወጪ እቃቸውን ወደ ተሽከርካሪ በመጫንና ወደ ተሰጣቸውም ቦታ በመውሰድ የአራዳ ክፍለ ከተማ ኦፊሰሮችና አመራሮች ከፍተኛ ሚና መጫወታቸው ጠቁመዋል።
የመድረኩ ንግግር ያደረጉት የአራዳ ክ/ከተማ ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታሁን አበራ ደንብ ማስከበር በየጊዜው እያደገና እየተሻሻለ የሚገኝ ተቋም መሆኑና እያከናወናቸው ያሉ ውጤታማ ተግባራት በግልጽ ማሳያ ናቸው በማለት በቀጣይ ተቋሙ ለሚያከናውኗቸው ስራዎች ከጎኑ ሆነው እንደሚደግፉ ተናግረዋል ።
የአራዳ ክ/ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብዲ የተሰራው የኮሪደር ልማት ስራው ተውቦና ደምቆ የምናየው ከፊትም ከኋላም ደንብ ማስከበር አባላት መሰዋዕትነት እየከፈሉ ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲቆይ ላደረጉት አስተዋፅኦ ተቋሙና አባላቱ ማመሰገን፣ ማክበር እና መሸለም እንደሚገባ ገልፀዋል።
በመድረኩ የእንኳን ደና መጣቹ ንግግር ያደረጉት የአራዳ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሀላፊ ሻምበል ኑርልኝ ገ/ኪዳን ቀን እና ሌሊት የሰሩ የደንብ ማስከበር ተልዕኮ ተቀብለው የሚታዩ የደም መተላለፍና ህገ-ወጥ ተግባራትን በመቆጣጠር በመከላከል በዚህ ስድስት ወር ውስጥ የደንብ የደንብ መተላለፍ 53.9% መቀነሱ ገልጸዋል።
አክለውም እውቅና እና ሸልማት መሠጠቱ የተሰሩ ስራዎችን ከባለድርሻ አካላትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት የተሻለ አፈጻጸም ለማምጣት ጉልህ ሚና አንዳለው ገልጸው ከ1ኛ - 3ኛ የወጡ ወረዳዎች እውቅና እና ሸልማት ተበርክቶላቸዋል።
እውቅና እና ሸልማት በአፈፃፀማቸው መሠረት 1ኛ ወረዳ 5 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት
2ኛ ወረዳ 6 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት
3ኛ ወረዳ 9 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በመውጣት እውቅና እና ሸልማት ተበርክቶላቸዋል።
ዘገበው ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
የካቲት 16/2017 ዓ.ም
**አዲስ አባባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ በኮሪደር ልማት ስራዎች እና የ2017 በጀት አመት የ6 ወር እቅድ አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና ሽልማት መርሃ ግብር አካሂዷል።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው፣ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ምክትል ሀላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ ፣የአራዳ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጌታሁን አበራ፣ሌሎች የክ/ከተማው ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣የመከላከያ፣ የፌደራል እና የከተማው የፖሊስ አባላት፣ ባለድርሻ አካላት ፣ የወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ ኦፊሰሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የሀይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ዓለምን ያስደመመው አፍሪካውያንን ያነጋገረ የአዲስ አበባ የልማት ስራ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አባሎቻችን እና ባለድርሻ አካሎች ከልብ አመስግነው የመጀመሪያ የኮሪደር ልማት ስረሠ የተጀመረው በአራዳ ክፍለ ከተማ ላይ ነው የአራዳ ክፍለ ከተማ ነው ለዚህም ትልቁ ኃይላችን የደንብ ማስከበር እንደነበር ገልጸዋል።
በዚህም ኦፊሰሩ ለልማት የተነሱ እናቶቻችን እና አባቶቻችን ያለምንም ወጪ እቃቸውን ወደ ተሽከርካሪ በመጫንና ወደ ተሰጣቸውም ቦታ በመውሰድ የአራዳ ክፍለ ከተማ ኦፊሰሮችና አመራሮች ከፍተኛ ሚና መጫወታቸው ጠቁመዋል።
የመድረኩ ንግግር ያደረጉት የአራዳ ክ/ከተማ ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታሁን አበራ ደንብ ማስከበር በየጊዜው እያደገና እየተሻሻለ የሚገኝ ተቋም መሆኑና እያከናወናቸው ያሉ ውጤታማ ተግባራት በግልጽ ማሳያ ናቸው በማለት በቀጣይ ተቋሙ ለሚያከናውኗቸው ስራዎች ከጎኑ ሆነው እንደሚደግፉ ተናግረዋል ።
የአራዳ ክ/ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብዲ የተሰራው የኮሪደር ልማት ስራው ተውቦና ደምቆ የምናየው ከፊትም ከኋላም ደንብ ማስከበር አባላት መሰዋዕትነት እየከፈሉ ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲቆይ ላደረጉት አስተዋፅኦ ተቋሙና አባላቱ ማመሰገን፣ ማክበር እና መሸለም እንደሚገባ ገልፀዋል።
በመድረኩ የእንኳን ደና መጣቹ ንግግር ያደረጉት የአራዳ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሀላፊ ሻምበል ኑርልኝ ገ/ኪዳን ቀን እና ሌሊት የሰሩ የደንብ ማስከበር ተልዕኮ ተቀብለው የሚታዩ የደም መተላለፍና ህገ-ወጥ ተግባራትን በመቆጣጠር በመከላከል በዚህ ስድስት ወር ውስጥ የደንብ የደንብ መተላለፍ 53.9% መቀነሱ ገልጸዋል።
አክለውም እውቅና እና ሸልማት መሠጠቱ የተሰሩ ስራዎችን ከባለድርሻ አካላትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት የተሻለ አፈጻጸም ለማምጣት ጉልህ ሚና አንዳለው ገልጸው ከ1ኛ - 3ኛ የወጡ ወረዳዎች እውቅና እና ሸልማት ተበርክቶላቸዋል።
እውቅና እና ሸልማት በአፈፃፀማቸው መሠረት 1ኛ ወረዳ 5 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት
2ኛ ወረዳ 6 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት
3ኛ ወረዳ 9 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በመውጣት እውቅና እና ሸልማት ተበርክቶላቸዋል።
ዘገበው ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።