የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
994 subscribers
1.5K photos
4 videos
1 file
51 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
ኦፊሰሮች 17ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን እየተከበረ ይገኛል

       ጥቅምት 4/2017 ዓ.ም

ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ለሉዓላዊነታችን ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ሐሳብ ነው የሚከበረው የዘንድሮው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በክፍለ ከተሞች ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኦፊሰሮች ወታደራዊ ሰልፍ ታጅቦ እየተከበረ ይገኛል ።
ባለስልጣኑ ሲሰጥ የቆየው የመጀመሪያ ዙር የኦፊሰር የአቅም ግንቦት ስልጠና በተቀመጠው ፕሮግራም መሰረት በስኬት አጠናቀቀ

04/02/2017ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በሁሉም ክፍለ ከተማ እና ወረዳ ለሚገኙ የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ለሶስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየውን የመጀመሪያ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና አጠናቋል።

በሶስት ቀን በቆየው ስልጠና ለኦፊሰሩ በስነምግባርና ጸረ ሙስና፣በስነ ምግባር መመሪያ ቁጥር 3/2015ዓ.ም ላይ ፣ በተሻሽው በደንብ ቁጥር 167/2016ዓ.ም ፣ ፣ በመረጃ አያያዝና ትንተና ፣ በደንብ ቁጥር 167/2016 አና የሀገር ፍቅር ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል ።

በአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉሉ በስልጠናው ማጠቃለያው ተገኝተው ስልጠው ከኦፊሰሩ የዕለት ከዕለት ተግባር ጋር የሚያያዝ በመሆኑ ግንዛቤ የሚጨመር መሆኑ በመግለፅ ቀጣይነት ያለው መሆኑ ጠቁመዋ።

ስልጠናው የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሩ በስነምግባር የታነጹ እንዲሆንና በተቋሙ ሁለንተናዊ ለውጥ አንዲያመጡና በተሰማሩበት ቦታ ሁሉ ህብረተሰቡን በቀናነት እንዲያገለግሉ የተዘጋጀ የአቅም ማጎልበቻ መሆኑን የስልጠናው አስተባባሪ ወሮ ላቀች ሀይሌ ተናግረዋል ።

በስልጠናው ተሳትፊ የነበሩት ኦፊሰሮች ስልጠናው ራሳቸውን ከብልሹ አሰራር በማራቅ የተቋሙን ግብ ለማሳካት ያለቸውን አቅም በመጠቀም በትጋት እንደሚሰሩ ግንዛቤ መፍጠሩ ገልፀዋል ።

ስልጠናው በተለይ ከስራችን ጋር የተያያዙ ህግና መመርያን እንድናውቅና የምናውቃቸውን በስራችን አጠናክረን እንድንቀጥልና አሰራሩን ተረድተን በስራ ላይ ለሚገጥሙን የአሰራር ክፍተቶችን ለመሙላት አቅም ፈጥሮልናል ብለዋል ፡፡

ባለስልጣኑ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች እየሰጠ ያለው ስልጠና ይበል የሚሰኝና ለኦፊሰሩ መብትና ግዴታውን በማወቅ ስራውን እንዲሰራ፣የመረጃ አያያዝ ስርዓት ለማጠንከር ግንዛቤ የተጨበጠበት መሆኑና ገልፀዋል።

በስልጠናው ማጠቃለያ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ከስልጠናው ተሳታፊዎች በርካታ ሀሳብና አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን በከተማውና በክፍለ ከተማው ሀላፊዎችና ተወካዮች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።

ዘገባው ፦ የአዲስ አባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሙስናና ብልሹ አሰራር ለመግታት ባለሙያን በእውቀትና በስነ-ምግባር ማነፅ እንደሚያስፈልግ ተገለፀ

09/02/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2ኛ ዙር ሙያዊ ተላብሰው አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል ከ2100 በላይ ለፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በአስራ አንዱም ክፍለ ከተሞች የስነ-ምግባር መመሪያ ቁጥር 3/2015 እና በፀረ ሙስና ላይ የአቅም የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ።

ባለስልጣኑ ለመሚያስተዳድራቸው ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በስነ-ምግባር መመሪያ እና ብልሹ አሰራር በሀገር ላይ የሚያደርሱ ጉዳቶች በተመለከተ ስልጠና በመስጠትና ግንዛቤ በመፍጠር በቀጣይ በብልሹ አሰራር ተግባር ውስጥ ገብተው የተገኙ ኦፊሰሮች ላይ ጠንከር ያለ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።

የባለስልጣኑ የስነ ምግባር እና የፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ሙስናና ብልሹ አሰራር ለመግታት ባለሙያን በእውቀትና በስነ-ምግባር ማነፅ እንደሚያስፈልግ ገልፀው ሰልጣኞች በሰለጠኑት መሰረት ህብረተሰቡን በመመሪያው መሰረት በሙያዊ ስነምግባር ማገልገል እንደሚጠበቅባቸው ገልፀዋል።

ስልጠናው በሦስት ዙር የሚሰጥ ሲሆን መጀመሪያው በተሰጠው የስነ-ምግባር መመሪያ ስልጠና 2000በላይ ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠናው የወሰዱ ሲሆን በቀጣይ 3ኛ ዙር ለ2100 ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና እንደሚሰጥ ተጠቁሟል።

ዘገባው ፦ የአዲስ አባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።