የሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ይካሄዳል
መስከረም 27/2017 ዓ.ም
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ይካሔዳል፡፡
በኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 58 ንዑስ አንቀፅ (2) እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 24 ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአንድ ዓመት የሥራ ጊዜ ከመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መሆኑ ተደንግጓል፡፡
በድንጋጌው መሰረት የ6ኛው ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የተጠናቀቀ ሲሆን 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓትም የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት በተገኙበት ዛሬ ከቀኑ 8 ሠዓት ጀምሮ ይካሄዳል ተብሏል፡፡
በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይም የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት ለሁለቱ የፌዴራል መንግሥት ምክር ቤቶች ዓመታዊ ሥራቸውን መጀመራቸውን በማብሰር የፌዴራል መንግሥቱን ዓመታዊ ዕቅድ ያቀርባሉ።
የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደሚገኙም ተጠቁሟል፡፡
መስከረም 27/2017 ዓ.ም
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ይካሔዳል፡፡
በኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 58 ንዑስ አንቀፅ (2) እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 24 ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአንድ ዓመት የሥራ ጊዜ ከመስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ሰኞ ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መሆኑ ተደንግጓል፡፡
በድንጋጌው መሰረት የ6ኛው ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የተጠናቀቀ ሲሆን 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓትም የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት በተገኙበት ዛሬ ከቀኑ 8 ሠዓት ጀምሮ ይካሄዳል ተብሏል፡፡
በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይም የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት ለሁለቱ የፌዴራል መንግሥት ምክር ቤቶች ዓመታዊ ሥራቸውን መጀመራቸውን በማብሰር የፌዴራል መንግሥቱን ዓመታዊ ዕቅድ ያቀርባሉ።
የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደሚገኙም ተጠቁሟል፡፡
ባለስልጣኑ በ2017 በጀት ዓመት በመጀመሪያ ሩብ አመት የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ገመገመ
27/01/2017ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 የመጀመሪያ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የባለስልጣኑ የበላይ ኃላፊዎች በተገኙበት ከማዕከሉ ፕሮሰስ ካውንስል አባላት ጋር በዛሬው እለት ተገምግሟል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ ክትትል ፣ ቁጥጥርና እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ እና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍና የድጋፍ ሰጪ ዳይሬክተሮች የ2017 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በሩብ ዓመቱ የታዪ ክፍተቶች ያጋጠሙ ችግሮችን እና ጠንካራ ጎኖች ቀርበው ውይይት ተደርጓል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ ስራዎች በጥንካሬ የሚገለፁ መሆናቸው ገልፀው በቀጣይ ሁሉም ሰራተኞች እና በየደረጃው ያሉ አመራሮች በቁርጠኝነት በመስራት አሁን ላይ የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል ከተማችን ደንብ መተላለፎች የቀነሰባት ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው ።
27/01/2017ዓ.ም
**አዲስ አበባ*
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 የመጀመሪያ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የባለስልጣኑ የበላይ ኃላፊዎች በተገኙበት ከማዕከሉ ፕሮሰስ ካውንስል አባላት ጋር በዛሬው እለት ተገምግሟል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ ክትትል ፣ ቁጥጥርና እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ እና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍና የድጋፍ ሰጪ ዳይሬክተሮች የ2017 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በሩብ ዓመቱ የታዪ ክፍተቶች ያጋጠሙ ችግሮችን እና ጠንካራ ጎኖች ቀርበው ውይይት ተደርጓል ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ ስራዎች በጥንካሬ የሚገለፁ መሆናቸው ገልፀው በቀጣይ ሁሉም ሰራተኞች እና በየደረጃው ያሉ አመራሮች በቁርጠኝነት በመስራት አሁን ላይ የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል ከተማችን ደንብ መተላለፎች የቀነሰባት ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ዘገባው:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው ።