የሀዘን መግለጫ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋሙ አማካሪ የነበሩት እና በምክትል ስራ አስኪያጅነት ተቋሙን የመሩት ወ/ሮ አበባ እሸቴ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።
ወ/ሮ አበባ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው እለት ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም ህይወታቸው በማለፉ ተቋሙ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለመላው ቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናቱን ይመኛል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋሙ አማካሪ የነበሩት እና በምክትል ስራ አስኪያጅነት ተቋሙን የመሩት ወ/ሮ አበባ እሸቴ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።
ወ/ሮ አበባ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው እለት ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም ህይወታቸው በማለፉ ተቋሙ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለመላው ቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናቱን ይመኛል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን
😭69🙈3❤1
ባለስልጣኑ ወደ ወንዝ በካይ ፍሳሽ የለቀቁ 2 ተቋማት 700,000 ብር መቅጣቱ አስታወቀ
09-12 -2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ስሙ አዋሬ አደባባይ አካባቢ ጃንቦ ሪል እስቴት የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ወንዝ በመልቀቁ ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በቅንጅት በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት 300,000/ሦስት መቶ ሺህ/ ብር ተቀጥቷል።
በተያያዘ ዜና በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ሪፌንቲ አካባቢ ሼንግዴይ ኪለይ እና ሲመንት ማኑፋክቸሪንግ የግል ማህበር ያልተጣራ የሲሚንቶ ፍሳሽ ወደ ወንዝ በመልቀቁ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመሆን በደንብና ቁጥር 180/2017 መሰረት 400,000/አራት መቶ ሺህ/ ብር በመቅጣት ፍሳሹ እንዲቆም ተደርጓል።
የግልና የመንግስት ተቋማት እና ግለሰቦች መሰረተ ልማት ደህንነት በመጠበቅ ከአካባቢነ ከብክለት በመጠበቅ ስራቸው እንዲሰሩ እያሳሰበ ደንብ በሚተላለፉት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።
ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው፡- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ፦ https://linktr.ee/aacodeenforcement
09-12 -2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ስሙ አዋሬ አደባባይ አካባቢ ጃንቦ ሪል እስቴት የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ወንዝ በመልቀቁ ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በቅንጅት በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት 300,000/ሦስት መቶ ሺህ/ ብር ተቀጥቷል።
በተያያዘ ዜና በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ሪፌንቲ አካባቢ ሼንግዴይ ኪለይ እና ሲመንት ማኑፋክቸሪንግ የግል ማህበር ያልተጣራ የሲሚንቶ ፍሳሽ ወደ ወንዝ በመልቀቁ ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመሆን በደንብና ቁጥር 180/2017 መሰረት 400,000/አራት መቶ ሺህ/ ብር በመቅጣት ፍሳሹ እንዲቆም ተደርጓል።
የግልና የመንግስት ተቋማት እና ግለሰቦች መሰረተ ልማት ደህንነት በመጠበቅ ከአካባቢነ ከብክለት በመጠበቅ ስራቸው እንዲሰሩ እያሳሰበ ደንብ በሚተላለፉት ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።
ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው፡- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ፦ https://linktr.ee/aacodeenforcement
👍3❤1
ባለስልጣኑ በአራዳ ክፍለ ከተማ ያስገነባው የአቅመ ደካማ ቤት አጠናቆ ለባለቤቶቹ አስረከበ
12/12/2018 ዓ.ም
** አዲስአበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የአራዳ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በስሩ የሚገኙ ወረዳዎችን በማስተባበር በክፍለ ከተማው ወረዳ 04 ለሚገኙ አቅመ ደካማ ነዋሪ መኖሪያ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቱ አስረክቧል።
በምርቃቱ መርሐ ግቡሩ የተገኙት የአራዳ ክፍለ ከተማ ም/ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዲ ሙሉነህ ደንብ ማስከበር ለከተማው ህዝብ ደራሽ በመሆን የሀገሩን ልማት ለማስቀጠል ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል በትጋት እንደሚሰራ በመግለፅ ዛሬም በበጎ ተግባራ በክፍለ ከተማው ላስቀመጠው አሻራ ምስጋና አቅርበዋል ።
በፕሮግራሙ የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ኃላፊ ሻምበል ኑርልኝ ገ/ኪዳን የክረምት በጓ ፈቃድ ስራዎች ከሆነው ሰው ተኮር ተግባር የአቅመ ደካማ ቤት በመገንባት በ27 ቀናት ሰርቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቷ ማስረከቡን ገልፀዋል ።
አክለውም የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ባሉ 8 ወረዳዎች ከሚሰራቸው የደንብ መተላለፍ መከላከልና መቆጣጠር በተጨማሪ ሰው ተኮር ስራዎች አንዱ የስራው አካል አድርጎ እንደሚሰራ በመጠቆም ለዚህም 1,454,200 ብር በማውጣት የወ/ሮ ከበቡሽ ሸዋ ቤት አፈርሶ መገንባቱን ተናግረዋል ።
ቤቱ የተገነባላቸው ወ/ሮ ከበቡሽ ሸዋ ከ5 በላይ ቤተሰብ ይዘው የሚኖሩበት ቤት ቀደም ሲል ዝናብና ፀሀይ የሚፈራርቅበት የነበረና ለመኖር ፈታኝ እንደነበር በመግለፅ ለተደረገላቸው ነገር ሁሉ ለደንብ ማስከበር ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አበርክተዋል።
በመድረኩ የተሳተፉት የአራዳ ክፍለ ከተማ የበጓ ፈቃድና ህብረተሰብ ተሳትፎ ኃላፊ ወ/ሮ ፀጋነሽ ታምራት ደንብ ማስከበር በክፍለ ከተማው ከተለዮ የአቅመ ደካማ ቤት አንዱ የሆነውን ቤት በአጭር ጊዜ አፍርሶ ከማደስ ባሻገር የተለያዩ ቁሳቁሶችን በማሟላት ለወገን ደረሽነቱን በማስመስከሩ እጅግ የሚበረታታ ነው ሲሉ ገልፀዋል ።
በመጨረሻም ለበጓ አድራጎት ስራው ተሳታፊ ለነበሩ አካለት የምስክር ወረቀት በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡፡፡
12/12/2018 ዓ.ም
** አዲስአበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የአራዳ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በስሩ የሚገኙ ወረዳዎችን በማስተባበር በክፍለ ከተማው ወረዳ 04 ለሚገኙ አቅመ ደካማ ነዋሪ መኖሪያ ቤት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቱ አስረክቧል።
በምርቃቱ መርሐ ግቡሩ የተገኙት የአራዳ ክፍለ ከተማ ም/ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዲ ሙሉነህ ደንብ ማስከበር ለከተማው ህዝብ ደራሽ በመሆን የሀገሩን ልማት ለማስቀጠል ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል በትጋት እንደሚሰራ በመግለፅ ዛሬም በበጎ ተግባራ በክፍለ ከተማው ላስቀመጠው አሻራ ምስጋና አቅርበዋል ።
በፕሮግራሙ የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ኃላፊ ሻምበል ኑርልኝ ገ/ኪዳን የክረምት በጓ ፈቃድ ስራዎች ከሆነው ሰው ተኮር ተግባር የአቅመ ደካማ ቤት በመገንባት በ27 ቀናት ሰርቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቷ ማስረከቡን ገልፀዋል ።
አክለውም የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ባሉ 8 ወረዳዎች ከሚሰራቸው የደንብ መተላለፍ መከላከልና መቆጣጠር በተጨማሪ ሰው ተኮር ስራዎች አንዱ የስራው አካል አድርጎ እንደሚሰራ በመጠቆም ለዚህም 1,454,200 ብር በማውጣት የወ/ሮ ከበቡሽ ሸዋ ቤት አፈርሶ መገንባቱን ተናግረዋል ።
ቤቱ የተገነባላቸው ወ/ሮ ከበቡሽ ሸዋ ከ5 በላይ ቤተሰብ ይዘው የሚኖሩበት ቤት ቀደም ሲል ዝናብና ፀሀይ የሚፈራርቅበት የነበረና ለመኖር ፈታኝ እንደነበር በመግለፅ ለተደረገላቸው ነገር ሁሉ ለደንብ ማስከበር ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አበርክተዋል።
በመድረኩ የተሳተፉት የአራዳ ክፍለ ከተማ የበጓ ፈቃድና ህብረተሰብ ተሳትፎ ኃላፊ ወ/ሮ ፀጋነሽ ታምራት ደንብ ማስከበር በክፍለ ከተማው ከተለዮ የአቅመ ደካማ ቤት አንዱ የሆነውን ቤት በአጭር ጊዜ አፍርሶ ከማደስ ባሻገር የተለያዩ ቁሳቁሶችን በማሟላት ለወገን ደረሽነቱን በማስመስከሩ እጅግ የሚበረታታ ነው ሲሉ ገልፀዋል ።
በመጨረሻም ለበጓ አድራጎት ስራው ተሳታፊ ለነበሩ አካለት የምስክር ወረቀት በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡፡፡
❤4👍2
ባለስልጣኑ በ2019 በጀት አመት የደንብ መተላለፎችን በ54.3 ፐርሰንት ለመቀነስ ማቀዱ ተገለፀ
14/12/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2019 በጀት አመት እቅድ ላይ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከማዕከል ሰራተኞች ጋር የተቋሙ ስኬት በማስቀጠል የደንብ መተላለፎች ለመቀነስ በተነደፉ ስልቶች እና እቅዶች ላይ ውይይት ተደረገ።
በውይይቱን የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በ2019 በጀት አመት የቀደውን እቅድ በትጋትና በቁረጠኝነት በመስራት በከተማችን የደንብ መተላለፍ እንዲቀንስና በተነደፉ ስልቶች እና እቅዶች መሠረት በትጋት በመፈፀም በከተማ አስተዳደሩ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት ሁሌም ዝግጁ መሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።
የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ በበጀት ዓመቱ የደንብ መተላለፍ የሚፀየፍ ማህበረሰብ ለመፍጠር በርካታ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች እንደሚሰጡና በቴክኖሎጂ በታገዘ የደንብ መተላለፍ በመከላከል በመቆጣጠር በ9 የደንብ መተላለፎች ላይ በ54.3 ፐርሰንት ለመቀነስ መታቀዱ ተናግረዋል።
በቀጣይ ከሁለት ሺህ በላይ አዲስ የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን መልምሎ ስልጠና በመስጠት ወደ ተቋሙ በመቀላቀል እና በስራ ላይ ያሉትን ከ7000 በላይ ነባር የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰር በማስልጠን የሰው ሃይሉ ለማብቃት እንደሚሰራ በተነደፈው ስልት ተመላክቷል።
በመድረኩ በ2018 በጀት አመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ዳይሬክተሮች ቡድን መሪዎችና ፈፃሚዎች ምስጋናና እውቅና በመስጠት ለመላው የተቋሙ አመራሮች እና ሰራተኞች ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በከተማ ደረጃ 1ኛ እንዲወጣና ተሸላሚ እንዲሆን ላበረከቱት አስተዋፅኦ ምስጋናና እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
14/12/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2019 በጀት አመት እቅድ ላይ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከማዕከል ሰራተኞች ጋር የተቋሙ ስኬት በማስቀጠል የደንብ መተላለፎች ለመቀነስ በተነደፉ ስልቶች እና እቅዶች ላይ ውይይት ተደረገ።
በውይይቱን የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በ2019 በጀት አመት የቀደውን እቅድ በትጋትና በቁረጠኝነት በመስራት በከተማችን የደንብ መተላለፍ እንዲቀንስና በተነደፉ ስልቶች እና እቅዶች መሠረት በትጋት በመፈፀም በከተማ አስተዳደሩ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት ሁሌም ዝግጁ መሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።
የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ በበጀት ዓመቱ የደንብ መተላለፍ የሚፀየፍ ማህበረሰብ ለመፍጠር በርካታ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች እንደሚሰጡና በቴክኖሎጂ በታገዘ የደንብ መተላለፍ በመከላከል በመቆጣጠር በ9 የደንብ መተላለፎች ላይ በ54.3 ፐርሰንት ለመቀነስ መታቀዱ ተናግረዋል።
በቀጣይ ከሁለት ሺህ በላይ አዲስ የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን መልምሎ ስልጠና በመስጠት ወደ ተቋሙ በመቀላቀል እና በስራ ላይ ያሉትን ከ7000 በላይ ነባር የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰር በማስልጠን የሰው ሃይሉ ለማብቃት እንደሚሰራ በተነደፈው ስልት ተመላክቷል።
በመድረኩ በ2018 በጀት አመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ዳይሬክተሮች ቡድን መሪዎችና ፈፃሚዎች ምስጋናና እውቅና በመስጠት ለመላው የተቋሙ አመራሮች እና ሰራተኞች ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በከተማ ደረጃ 1ኛ እንዲወጣና ተሸላሚ እንዲሆን ላበረከቱት አስተዋፅኦ ምስጋናና እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
👍12❤1