ባለስልጣኑ ለደንብ ማስከበር ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት ስምምነት ተፈራረመ
ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ጋር ለፖራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የውል ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነቱ የደንብ ማስከበር አባላት የከተማዋን ፀጥታ እና ደንብ የማስከበር ስራ በሚያከናውኑበት ወቅት የሚገጥማቸውን የትራንስፖርት እንግልት በእጅጉ እንደሚቀርፍ ታምኖበት የውል ስምምነት መደረጉ የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን እንደተናገሩት ኦፊሰሮቹ ይህንን የትራንስፖርት እድል ማግኘታቸው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን በማቃለል ከፍተኛ የሥራ ተነሳሽነት እንዲኖራቸው የሚያደርግና ለከተማዋ ሰላምና ደንብ መከበር የሚሰጡትን አገልግሎት የበለጠ ውጤታማ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።
ይህ ውሳኔ ለአባላቱ የተደረገ ትልቅ እውቅና እና ድጋፍ ሲሆን በቀጣይም የከተማዋን ደንብና ስርዓት ለማስከበር ለሚደረገው ጥረት የሚደግፍ አሰራሮች እንደሚዘረጉ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አካሉ አሰፋ በውል ስምምነቱ ለከተማችን ደንብ የሚያስከብሩ እና የመንገድ ደንነት በማስከበር መንገድ እንዳይዘጋጋ ጤናማ የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲኖር ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የደንብ ማስከበር አባላት አገልግሎት ስንሰጥ ክብር ይሰማናል ብለዋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ጋር ለፖራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የውል ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነቱ የደንብ ማስከበር አባላት የከተማዋን ፀጥታ እና ደንብ የማስከበር ስራ በሚያከናውኑበት ወቅት የሚገጥማቸውን የትራንስፖርት እንግልት በእጅጉ እንደሚቀርፍ ታምኖበት የውል ስምምነት መደረጉ የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን እንደተናገሩት ኦፊሰሮቹ ይህንን የትራንስፖርት እድል ማግኘታቸው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን በማቃለል ከፍተኛ የሥራ ተነሳሽነት እንዲኖራቸው የሚያደርግና ለከተማዋ ሰላምና ደንብ መከበር የሚሰጡትን አገልግሎት የበለጠ ውጤታማ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።
ይህ ውሳኔ ለአባላቱ የተደረገ ትልቅ እውቅና እና ድጋፍ ሲሆን በቀጣይም የከተማዋን ደንብና ስርዓት ለማስከበር ለሚደረገው ጥረት የሚደግፍ አሰራሮች እንደሚዘረጉ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አካሉ አሰፋ በውል ስምምነቱ ለከተማችን ደንብ የሚያስከብሩ እና የመንገድ ደንነት በማስከበር መንገድ እንዳይዘጋጋ ጤናማ የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲኖር ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የደንብ ማስከበር አባላት አገልግሎት ስንሰጥ ክብር ይሰማናል ብለዋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
❤8👍8👏3😁1
ባለስልጣኑ በላስቲክና ፌስታል ደንብ ቁጥር 13/83/2017 ዙሪያ የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጠ
ሐምሌ/28/2018
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በደንብ ቁጥር 13/83/2017 በፕላስቲክና ፌስታል ብክለት ላይ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጠ።
ስልጠናውን ያስጀመሩት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ
ኃላፊ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው እንዳሉት ተቋሙ በከተማ አስተዳደሩ የሚወጡትን ደንቦች አስቀድሞ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር የደንብ መተላለፉን የሚጸየፍ ማህበረሰብን ለመገንባት በተለያዩ መንገዶች ስልጠናዎችን የሚሰጥ መሆኑን ገልፀው፤ ሰልጥኖ ለማሰልጠን ዝግጁ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከፍተኛ ከአከባቢ ጥበቃ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሙላቱ ወሰኑ ስለ ፌስታል ብክለት መከላከልና የሚያስከትሉት ጉዳቶች ገልፀው ደንቡ በሚተገበርበት ወቅት ስለሚወሰደው እርጃ በስፋት አብራርተዋል።
በስልጠናው ላይ የተገኙት የሰልጥኖ አሰልጣኞችም የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሳት ትምህርታዊ እውቀትን የቀሰሙበትና ወደ ታች በመውረድ ለማሰልጠን ተገቢውን እውቀት እንዳገኙ ገልጸዋል።
መረጃው፡- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሐምሌ/28/2018
**የአዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በደንብ ቁጥር 13/83/2017 በፕላስቲክና ፌስታል ብክለት ላይ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጠ።
ስልጠናውን ያስጀመሩት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ
ኃላፊ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው እንዳሉት ተቋሙ በከተማ አስተዳደሩ የሚወጡትን ደንቦች አስቀድሞ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር የደንብ መተላለፉን የሚጸየፍ ማህበረሰብን ለመገንባት በተለያዩ መንገዶች ስልጠናዎችን የሚሰጥ መሆኑን ገልፀው፤ ሰልጥኖ ለማሰልጠን ዝግጁ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከፍተኛ ከአከባቢ ጥበቃ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሙላቱ ወሰኑ ስለ ፌስታል ብክለት መከላከልና የሚያስከትሉት ጉዳቶች ገልፀው ደንቡ በሚተገበርበት ወቅት ስለሚወሰደው እርጃ በስፋት አብራርተዋል።
በስልጠናው ላይ የተገኙት የሰልጥኖ አሰልጣኞችም የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሳት ትምህርታዊ እውቀትን የቀሰሙበትና ወደ ታች በመውረድ ለማሰልጠን ተገቢውን እውቀት እንዳገኙ ገልጸዋል።
መረጃው፡- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤6👍2
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የቢሮ ውስጥ እድሳቱን አጠናቆ አስመረቀ
ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ የቢሮ ውስጥ እድሳት በማጠናቀቅ ለሰራተኞች እና ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር አስመረቀ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምርቃት ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የተቋም ግንባታና አደረጃጀትን ማሻሻል ከህብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ፣ ለዜጎች ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልፀዋል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ ደንብ ማስከበር የደንብ መተላለፎችን በመቆጣጠር የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤት ከመፈጸምና በኃላፊነት ከመወጣት ባሻገር ያከናወነው ይህ የተቋም ግንባታ ስራ የሚበረታታና ሌሎች ጽህፈት ቤቶችንም የሚያነሳሳ ነው ብለዋል።
ዘገባው ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ የቢሮ ውስጥ እድሳት በማጠናቀቅ ለሰራተኞች እና ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር አስመረቀ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምርቃት ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የተቋም ግንባታና አደረጃጀትን ማሻሻል ከህብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ፣ ለዜጎች ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልፀዋል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ ደንብ ማስከበር የደንብ መተላለፎችን በመቆጣጠር የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤት ከመፈጸምና በኃላፊነት ከመወጣት ባሻገር ያከናወነው ይህ የተቋም ግንባታ ስራ የሚበረታታና ሌሎች ጽህፈት ቤቶችንም የሚያነሳሳ ነው ብለዋል።
ዘገባው ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍11❤3
ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኑኬሽን ስራ ለተቋም ግንባታ መሠረት መሆኑ ተገለፀ
29/11/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራር ከሰራተኞችና ከሚያገለግሉት ማህበረሰብ ያለውን ተግባቦት ለማጠናከር ጂኦ-ስፓሻል ቴክኖሎጂ እና በሚዲያ አጠቃቀምና ተግባቦት ላይ ስልጠና ሰጠ።
የሚዲያና ኮሙኑኬሽን ስራ ለተቋም ግንባታ እና የአመራርነት ውጤታማነት ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ሀላፊ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ገልጸዋል።
ዘመኑ የመረጃ በመሆኑ ከዘመኑ ጋር ቴክኖሎጂ ስርዓት መሠረት መረጃዎች ጂኦ-ስፓሻል ቴክኖሎጂ ስርት በመተግበር የደንብ መሠስከበር ስርዓት ማጠናከር እንደሚገባ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ የውጭና የህዝብ ግነኙነት ኃላፊ ዋና ኢኒስፔክተር ፍፁም ብርሀኑ በስልጠው አስረድተዋል።
በሚዲያ አጠቃቀምና ተግባቦት ላይ ስልጠና የሰጡት የተቋሙ የኮሙኑኬሽን ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ ጠንካራ የህዝብ ግንኙነት ለመፍጠር እና የህብረተሰብ ድጋፍ ለማግኘት ወቅቱን የጠበቀ የተግባቦት ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑ ጠቁመዋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ የደንብ ማስከበር ባለስልጣኑ የኮሙኑኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
29/11/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራር ከሰራተኞችና ከሚያገለግሉት ማህበረሰብ ያለውን ተግባቦት ለማጠናከር ጂኦ-ስፓሻል ቴክኖሎጂ እና በሚዲያ አጠቃቀምና ተግባቦት ላይ ስልጠና ሰጠ።
የሚዲያና ኮሙኑኬሽን ስራ ለተቋም ግንባታ እና የአመራርነት ውጤታማነት ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ሀላፊ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ገልጸዋል።
ዘመኑ የመረጃ በመሆኑ ከዘመኑ ጋር ቴክኖሎጂ ስርዓት መሠረት መረጃዎች ጂኦ-ስፓሻል ቴክኖሎጂ ስርት በመተግበር የደንብ መሠስከበር ስርዓት ማጠናከር እንደሚገባ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ የውጭና የህዝብ ግነኙነት ኃላፊ ዋና ኢኒስፔክተር ፍፁም ብርሀኑ በስልጠው አስረድተዋል።
በሚዲያ አጠቃቀምና ተግባቦት ላይ ስልጠና የሰጡት የተቋሙ የኮሙኑኬሽን ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ ጠንካራ የህዝብ ግንኙነት ለመፍጠር እና የህብረተሰብ ድጋፍ ለማግኘት ወቅቱን የጠበቀ የተግባቦት ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑ ጠቁመዋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ የደንብ ማስከበር ባለስልጣኑ የኮሙኑኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤3👏1