የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.5K subscribers
3.94K photos
13 videos
1 file
93 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
የባለስልጣኑ አመራር እና ሰራተኞች በአንድ ጀምበር 8 መቶ ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል አሻራቸውን አኖሩ

ዛሬ የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ ለምግብ ዋስትና፣ ለውሃ ሀብት ጥበቃ፣ ለምግብ አቅርቦትና ለቀጣይ ትውልድ ንጹህ አየር ዋስትና ናት።

የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን!
👍5👏21
ባለስልጣኑ የእጩ አመራሮች የመሪነት እና የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና መካሄድ ጀመረ

ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ለተወጣጡ እጩ አመራሮች የመሪነት እና የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና መካሄድ ጀምሯል።

​ስልጠናው እንደ መሪ የማሰብ፣ የማቀድ እና የመፈጸም ክህሎትን ለማዳበር ያለመ ሲሆን በዋናነት የመሪነት ክህሎትን፣ የተከታይነት ባህሪያትን፣ የስሜት ብልህነትን፣ የመሪነት ንድፈ-ሀሳቦችን እና ስልቶችን፣ የማበረታቻ ስልቶችን እና ሌሎች ጠቃሚ የመሪነት ፅንሰ-ሀሳቦችን ያካተተ ነው።

​በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በ2018 በጀት ዓመት በአፈጻጸሙ አንደኛ በመሆን የተሸለመ መሆኑን አስታውሰው ይህ ስልጠና ከተማችን እያሳየች ያለችውን ፈጣን እድገት በሚመጥን መልኩ ተቋሙን በዘመናዊ አሰራር እና በእውቀት የሚመራ በተግባር የሚታይ የአመራር ብቃትን የተላበሰ፣ በመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ጥብቅ እርምጃ የሚወስድ እና የአገልግሎት እርካታን የሚያረጋግጥ ብቁ እና ንቁ እጩ አመራሮችን ለማፍራት ያለመ መሆኑን ገልፀዋል።

​ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ስልጠናው ለአራት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ በመግለጽ ሰልጣኞች ስልጠናውን በከፍተኛ ንቃት፣ ተነሳሽነት እና ጥብቅ ዲስፕሊን እንዲከታተሉ አሳስበዋል።

ይህ ስልጠና ተቋሙ የወደፊት ተተኪ መሪዎችን በማፍራት የተቋሙን ዘላቂ እድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም ገልፀዋል።

​ባለስልጣኑ ይህንን ስልጠና በማካሄድ ብቁ እና ንቁ አመራሮችን በማፍራት የከተማዋን እድገት ለማፋጠን እና የህዝብ አገልግሎትን ለማሻሻል ያለውን ቁርጠኝነት ያሳኘ መሆኑ ተገልጿል ።

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
👍65
ባለስልጣኑ ለደንብ ማስከበር ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት ስምምነት ተፈራረመ

ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ጋር ለፖራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የውል ስምምነት ተፈራረመ።

ስምምነቱ የደንብ ማስከበር አባላት የከተማዋን ፀጥታ እና ደንብ የማስከበር ስራ በሚያከናውኑበት ወቅት የሚገጥማቸውን የትራንስፖርት እንግልት በእጅጉ እንደሚቀርፍ ታምኖበት የውል ስምምነት መደረጉ የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል።

ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን እንደተናገሩት ኦፊሰሮቹ ይህንን የትራንስፖርት እድል ማግኘታቸው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን በማቃለል ከፍተኛ የሥራ ተነሳሽነት እንዲኖራቸው የሚያደርግና ለከተማዋ ሰላምና ደንብ መከበር የሚሰጡትን አገልግሎት የበለጠ ውጤታማ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።

​ይህ ውሳኔ ለአባላቱ የተደረገ ትልቅ እውቅና እና ድጋፍ ሲሆን በቀጣይም የከተማዋን ደንብና ስርዓት ለማስከበር ለሚደረገው ጥረት የሚደግፍ አሰራሮች እንደሚዘረጉ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አካሉ አሰፋ በውል ስምምነቱ ለከተማችን ደንብ የሚያስከብሩ እና የመንገድ ደንነት በማስከበር መንገድ እንዳይዘጋጋ ጤናማ የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲኖር ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የደንብ ማስከበር አባላት አገልግሎት ስንሰጥ ክብር ይሰማናል ብለዋል።

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
8👍8👏3😁1
ባለስልጣኑ በላስቲክና ፌስታል ደንብ ቁጥር 13/83/2017 ዙሪያ የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጠ

ሐምሌ/28/2018
**የአዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በደንብ ቁጥር 13/83/2017 በፕላስቲክና ፌስታል ብክለት ላይ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጠ።

ስልጠናውን ያስጀመሩት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ
ኃላፊ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው እንዳሉት ተቋሙ በከተማ አስተዳደሩ የሚወጡትን ደንቦች አስቀድሞ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር የደንብ መተላለፉን የሚጸየፍ ማህበረሰብን ለመገንባት በተለያዩ መንገዶች ስልጠናዎችን የሚሰጥ መሆኑን ገልፀው፤ ሰልጥኖ ለማሰልጠን ዝግጁ እንዲሆኑ አሳስበዋል።

ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከፍተኛ ከአከባቢ ጥበቃ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሙላቱ ወሰኑ ስለ ፌስታል ብክለት መከላከልና የሚያስከትሉት ጉዳቶች ገልፀው ደንቡ በሚተገበርበት ወቅት ስለሚወሰደው እርጃ በስፋት አብራርተዋል።

በስልጠናው ላይ የተገኙት የሰልጥኖ አሰልጣኞችም የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሳት ትምህርታዊ እውቀትን የቀሰሙበትና ወደ ታች በመውረድ ለማሰልጠን ተገቢውን እውቀት እንዳገኙ ገልጸዋል።

መረጃው፡- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
6👍2
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የቢሮ ውስጥ እድሳቱን አጠናቆ አስመረቀ

ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ​ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ የቢሮ ውስጥ እድሳት በማጠናቀቅ ለሰራተኞች እና ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር አስመረቀ።

​የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በምርቃት ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የተቋም ግንባታና አደረጃጀትን ማሻሻል ከህብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ፣ ለዜጎች ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልፀዋል።

​በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ ደንብ ማስከበር የደንብ መተላለፎችን በመቆጣጠር የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤት ከመፈጸምና በኃላፊነት ከመወጣት ባሻገር ያከናወነው ይህ የተቋም ግንባታ ስራ የሚበረታታና ሌሎች ጽህፈት ቤቶችንም የሚያነሳሳ ነው ብለዋል።

​ዘገባው ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
👍113