የባለስልጣኑ አመራር እና ሰራተኞች በአንድ ጀምበር 8 መቶ ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል አሻራቸውን እያኖሩ ይገኛሉ
ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራሮች እና ሰራተኞች በአንድ ጀምበር 8 መቶ ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል አሻራቸውን እያኖሩ ይገኛሉ።
በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአንድ ጀምበር ብቻ 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ግብ ለማሳካት በአንድ ላይ በመሰለፍ የታሪክ አካል እየሆኑ ይገኛሉ።
ዛሬ የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ ለምግብ ዋስትና፣ ለውሃ ሀብት ጥበቃ፣ ለምግብ አቅርቦትና ለቀጣይ ትውልድ ንጹህ አየር ዋስትና ናት።
ዛሬ የምንተክለው ችግኝ፣ ነገ የምንሰበስበው አረንጓዴ ተስፋ ነው።
የትም ይሁኑ የት፣ በሚኖሩበትና በሚሠሩበት አካባቢ ቢያንስ አንድ ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ዕለት አካል ይሁኑ።
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን!
ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አመራሮች እና ሰራተኞች በአንድ ጀምበር 8 መቶ ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል አሻራቸውን እያኖሩ ይገኛሉ።
በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአንድ ጀምበር ብቻ 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ግብ ለማሳካት በአንድ ላይ በመሰለፍ የታሪክ አካል እየሆኑ ይገኛሉ።
ዛሬ የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ ለምግብ ዋስትና፣ ለውሃ ሀብት ጥበቃ፣ ለምግብ አቅርቦትና ለቀጣይ ትውልድ ንጹህ አየር ዋስትና ናት።
ዛሬ የምንተክለው ችግኝ፣ ነገ የምንሰበስበው አረንጓዴ ተስፋ ነው።
የትም ይሁኑ የት፣ በሚኖሩበትና በሚሠሩበት አካባቢ ቢያንስ አንድ ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ዕለት አካል ይሁኑ።
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን!
👍3❤1
የባለስልጣኑ አመራር እና ሰራተኞች በአንድ ጀምበር 8 መቶ ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል አሻራቸውን አኖሩ
ዛሬ የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ ለምግብ ዋስትና፣ ለውሃ ሀብት ጥበቃ፣ ለምግብ አቅርቦትና ለቀጣይ ትውልድ ንጹህ አየር ዋስትና ናት።
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን!
ዛሬ የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ ለምግብ ዋስትና፣ ለውሃ ሀብት ጥበቃ፣ ለምግብ አቅርቦትና ለቀጣይ ትውልድ ንጹህ አየር ዋስትና ናት።
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን!
👍5👏2❤1
ባለስልጣኑ የእጩ አመራሮች የመሪነት እና የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና መካሄድ ጀመረ
ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ለተወጣጡ እጩ አመራሮች የመሪነት እና የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና መካሄድ ጀምሯል።
ስልጠናው እንደ መሪ የማሰብ፣ የማቀድ እና የመፈጸም ክህሎትን ለማዳበር ያለመ ሲሆን በዋናነት የመሪነት ክህሎትን፣ የተከታይነት ባህሪያትን፣ የስሜት ብልህነትን፣ የመሪነት ንድፈ-ሀሳቦችን እና ስልቶችን፣ የማበረታቻ ስልቶችን እና ሌሎች ጠቃሚ የመሪነት ፅንሰ-ሀሳቦችን ያካተተ ነው።
በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በ2018 በጀት ዓመት በአፈጻጸሙ አንደኛ በመሆን የተሸለመ መሆኑን አስታውሰው ይህ ስልጠና ከተማችን እያሳየች ያለችውን ፈጣን እድገት በሚመጥን መልኩ ተቋሙን በዘመናዊ አሰራር እና በእውቀት የሚመራ በተግባር የሚታይ የአመራር ብቃትን የተላበሰ፣ በመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ጥብቅ እርምጃ የሚወስድ እና የአገልግሎት እርካታን የሚያረጋግጥ ብቁ እና ንቁ እጩ አመራሮችን ለማፍራት ያለመ መሆኑን ገልፀዋል።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ስልጠናው ለአራት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ በመግለጽ ሰልጣኞች ስልጠናውን በከፍተኛ ንቃት፣ ተነሳሽነት እና ጥብቅ ዲስፕሊን እንዲከታተሉ አሳስበዋል።
ይህ ስልጠና ተቋሙ የወደፊት ተተኪ መሪዎችን በማፍራት የተቋሙን ዘላቂ እድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ ይህንን ስልጠና በማካሄድ ብቁ እና ንቁ አመራሮችን በማፍራት የከተማዋን እድገት ለማፋጠን እና የህዝብ አገልግሎትን ለማሻሻል ያለውን ቁርጠኝነት ያሳኘ መሆኑ ተገልጿል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ለተወጣጡ እጩ አመራሮች የመሪነት እና የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና መካሄድ ጀምሯል።
ስልጠናው እንደ መሪ የማሰብ፣ የማቀድ እና የመፈጸም ክህሎትን ለማዳበር ያለመ ሲሆን በዋናነት የመሪነት ክህሎትን፣ የተከታይነት ባህሪያትን፣ የስሜት ብልህነትን፣ የመሪነት ንድፈ-ሀሳቦችን እና ስልቶችን፣ የማበረታቻ ስልቶችን እና ሌሎች ጠቃሚ የመሪነት ፅንሰ-ሀሳቦችን ያካተተ ነው።
በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣኑ በ2018 በጀት ዓመት በአፈጻጸሙ አንደኛ በመሆን የተሸለመ መሆኑን አስታውሰው ይህ ስልጠና ከተማችን እያሳየች ያለችውን ፈጣን እድገት በሚመጥን መልኩ ተቋሙን በዘመናዊ አሰራር እና በእውቀት የሚመራ በተግባር የሚታይ የአመራር ብቃትን የተላበሰ፣ በመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ጥብቅ እርምጃ የሚወስድ እና የአገልግሎት እርካታን የሚያረጋግጥ ብቁ እና ንቁ እጩ አመራሮችን ለማፍራት ያለመ መሆኑን ገልፀዋል።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ስልጠናው ለአራት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ በመግለጽ ሰልጣኞች ስልጠናውን በከፍተኛ ንቃት፣ ተነሳሽነት እና ጥብቅ ዲስፕሊን እንዲከታተሉ አሳስበዋል።
ይህ ስልጠና ተቋሙ የወደፊት ተተኪ መሪዎችን በማፍራት የተቋሙን ዘላቂ እድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ ይህንን ስልጠና በማካሄድ ብቁ እና ንቁ አመራሮችን በማፍራት የከተማዋን እድገት ለማፋጠን እና የህዝብ አገልግሎትን ለማሻሻል ያለውን ቁርጠኝነት ያሳኘ መሆኑ ተገልጿል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
👍6❤5
ባለስልጣኑ ለደንብ ማስከበር ፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት ስምምነት ተፈራረመ
ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ጋር ለፖራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የውል ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነቱ የደንብ ማስከበር አባላት የከተማዋን ፀጥታ እና ደንብ የማስከበር ስራ በሚያከናውኑበት ወቅት የሚገጥማቸውን የትራንስፖርት እንግልት በእጅጉ እንደሚቀርፍ ታምኖበት የውል ስምምነት መደረጉ የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን እንደተናገሩት ኦፊሰሮቹ ይህንን የትራንስፖርት እድል ማግኘታቸው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን በማቃለል ከፍተኛ የሥራ ተነሳሽነት እንዲኖራቸው የሚያደርግና ለከተማዋ ሰላምና ደንብ መከበር የሚሰጡትን አገልግሎት የበለጠ ውጤታማ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።
ይህ ውሳኔ ለአባላቱ የተደረገ ትልቅ እውቅና እና ድጋፍ ሲሆን በቀጣይም የከተማዋን ደንብና ስርዓት ለማስከበር ለሚደረገው ጥረት የሚደግፍ አሰራሮች እንደሚዘረጉ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አካሉ አሰፋ በውል ስምምነቱ ለከተማችን ደንብ የሚያስከብሩ እና የመንገድ ደንነት በማስከበር መንገድ እንዳይዘጋጋ ጤናማ የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲኖር ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የደንብ ማስከበር አባላት አገልግሎት ስንሰጥ ክብር ይሰማናል ብለዋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
ሐምሌ 28/2018ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ጋር ለፖራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የውል ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነቱ የደንብ ማስከበር አባላት የከተማዋን ፀጥታ እና ደንብ የማስከበር ስራ በሚያከናውኑበት ወቅት የሚገጥማቸውን የትራንስፖርት እንግልት በእጅጉ እንደሚቀርፍ ታምኖበት የውል ስምምነት መደረጉ የባለሥልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን እንደተናገሩት ኦፊሰሮቹ ይህንን የትራንስፖርት እድል ማግኘታቸው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን በማቃለል ከፍተኛ የሥራ ተነሳሽነት እንዲኖራቸው የሚያደርግና ለከተማዋ ሰላምና ደንብ መከበር የሚሰጡትን አገልግሎት የበለጠ ውጤታማ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።
ይህ ውሳኔ ለአባላቱ የተደረገ ትልቅ እውቅና እና ድጋፍ ሲሆን በቀጣይም የከተማዋን ደንብና ስርዓት ለማስከበር ለሚደረገው ጥረት የሚደግፍ አሰራሮች እንደሚዘረጉ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አካሉ አሰፋ በውል ስምምነቱ ለከተማችን ደንብ የሚያስከብሩ እና የመንገድ ደንነት በማስከበር መንገድ እንዳይዘጋጋ ጤናማ የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲኖር ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የደንብ ማስከበር አባላት አገልግሎት ስንሰጥ ክብር ይሰማናል ብለዋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡
❤8👍8👏3😁1