"ምቹ የስራ ቦታ መፍጠር የላቀ አፈጻጸምን ለማረጋገጥ አስተዋጽኦው ከፍተኛ ነው" ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ
ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በማዕከል የተጀመረው ምቹ የስራ አካባቢን የመፍጠር እና የአገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የመልካም አስተዳደር ተምሳሌትነቱን ለማረጋገጥ በየደረጃው በሚገኙ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ ጽህፈት ቤቶች የጀመራቸውን የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች አጠናክሮ በማስቀጠል በዛሬው እለት በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ መተግበሩን አስታወቀ።
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ቢሮውን በማዘመን ምቹ የስራ አካባቢን ለመፍጠር በአዲስ መልኩ ያደራጀውን ቢሮ የማስመረቅ እንዲሁም አዲሱ የፓራ ሚሊተሪ የደንብ ልብስ ለተገልጋዮቹ የማስተዋወቅ መርሀ ግብር በዛሬው እለት በታላቅ ድምቀት አካሂዷል።
በመርሀ ግብሩ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የክፍለ ከተማው የጽህፈት ቤት ኃላፊ ሻምበል ኦባድ ጁናን፣ የወረዳ የደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት "ምቹ የስራ ቦታ መፍጠር የላቀ አፈጻጸምን ለማረጋገጥ አስተዋጽኦው ከፍተኛ ነው" ካሉ በኋላ፣ በቀጣይም ይህ የሪፎርም ስራ ይበልጥ ተጠናክሮ በሌሎች ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በበጀት አመቱ ተቋሙን ከተማዋ ከያዘችው የዘመናዊ ከተማነትና የልማት ጉዞ ጋር በማስተሳሰር ወደ ላቀ ከፍታ ማሸጋገር እንደሚገባም አሳስበዋል።
የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሻምበል ኦባድ ጁና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ በአዲስ መልኩ የተደራጀውን ቢሮ እና የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን አዲስ የደንብ ልብስ አስተዋውቀዋል።
ኃላፊው አክለውም ይህ ማሻሻያ በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥና መልካም አስተዳደርን በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ ያለውን ፋይዳ ገልጸው፣ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በዕለቱ መርሃ ግብር ላይ በሰንዳፋ እና በአዳይቱ በተሰጡ ስልጠናዎች ላይ ለተሳተፉ አካላት የዕውቅና ምስክር ወረቀት የተሰጠ ሲሆን ክፍለ ከተማው ለሚያሳድጋቸው ህጻናትም የድጋፍና የስጦታ ማበርከት ስነ-ስርዓት ተከናውኗል።
ዘገባው:- የባለስልጣኑ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በማዕከል የተጀመረው ምቹ የስራ አካባቢን የመፍጠር እና የአገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የመልካም አስተዳደር ተምሳሌትነቱን ለማረጋገጥ በየደረጃው በሚገኙ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ ጽህፈት ቤቶች የጀመራቸውን የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች አጠናክሮ በማስቀጠል በዛሬው እለት በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ መተግበሩን አስታወቀ።
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ቢሮውን በማዘመን ምቹ የስራ አካባቢን ለመፍጠር በአዲስ መልኩ ያደራጀውን ቢሮ የማስመረቅ እንዲሁም አዲሱ የፓራ ሚሊተሪ የደንብ ልብስ ለተገልጋዮቹ የማስተዋወቅ መርሀ ግብር በዛሬው እለት በታላቅ ድምቀት አካሂዷል።
በመርሀ ግብሩ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የክፍለ ከተማው የጽህፈት ቤት ኃላፊ ሻምበል ኦባድ ጁናን፣ የወረዳ የደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት "ምቹ የስራ ቦታ መፍጠር የላቀ አፈጻጸምን ለማረጋገጥ አስተዋጽኦው ከፍተኛ ነው" ካሉ በኋላ፣ በቀጣይም ይህ የሪፎርም ስራ ይበልጥ ተጠናክሮ በሌሎች ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በበጀት አመቱ ተቋሙን ከተማዋ ከያዘችው የዘመናዊ ከተማነትና የልማት ጉዞ ጋር በማስተሳሰር ወደ ላቀ ከፍታ ማሸጋገር እንደሚገባም አሳስበዋል።
የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሻምበል ኦባድ ጁና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ በአዲስ መልኩ የተደራጀውን ቢሮ እና የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን አዲስ የደንብ ልብስ አስተዋውቀዋል።
ኃላፊው አክለውም ይህ ማሻሻያ በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥና መልካም አስተዳደርን በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ ያለውን ፋይዳ ገልጸው፣ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በዕለቱ መርሃ ግብር ላይ በሰንዳፋ እና በአዳይቱ በተሰጡ ስልጠናዎች ላይ ለተሳተፉ አካላት የዕውቅና ምስክር ወረቀት የተሰጠ ሲሆን ክፍለ ከተማው ለሚያሳድጋቸው ህጻናትም የድጋፍና የስጦታ ማበርከት ስነ-ስርዓት ተከናውኗል።
ዘገባው:- የባለስልጣኑ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
👍4
ባለስልጣኑ በ9995 ነጻ ስልክ መስመር በቀረቡ ጥቆማዎችና ቅሬታዎች ላይ ውይይት አካሄደ።
06/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የደንብ መተላለፍ ክትትል ፣ቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ በ2018 በጀት ዓመት ከጥር 25 እስከ ሰኔ 30 2018 በነጻ ስልክ መስመር 9995 ከህብረተሰቡ የመጡ ጥቆማዎች ፣ ቅሬታዎች እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት የውይይት መድረክ አካሂዷል ።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ የህዝብ ጥቆማዎችንና ቅሬታዎችን በሰፊው ለማስተናገድ የ 9995 ነጻ የጥሪ ማዕከል ዘመናዊ በማድረግ ሙሉ በሙሉ በኮምፒውተር እንዲደራጅ ተደርጎ በ3 ፈረቃ የ24 ሰዓት አገልግሎት መስጠት መጀመሩንና ማዕከሉ የከተማዋን ነዋሪዎች ስብጥር ባገናዘበ መልኩ ጥቆማዎችን በተለያዩ ቋንቋዎች ተቀብሎ ማስተናገድ የሚችሉ ባለሙያዎችን መድቦ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።
በመድረኩ በጥቆማ የሚመጡ ቅሬታዎች በምን አግባብ ተፈቱ ያልተፈቱ ካሉ በቀጣይ ችግሮቹን በመለየት መፍትሔ መስጠት እንደሚገባና ከሚመለከተው ተቋም በመተባበር የሚፈጠሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ እንደሚገባ ም/ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።
በ2018 በጀት ዓመት ከ 25/05/2018 እስከ 30/10/2018 በነጻ ስልክ መስመር 9995 ከህብረተሰቡ የመጡ ጥቆማዎች ፣ ቅሬታዎች እና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ሪፖርት ቀርቦ በመገምገም በቀጣይ ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል የትኩረት አቅጣጫ ተቀምጧል።
ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
።
06/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የደንብ መተላለፍ ክትትል ፣ቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዘርፍ በ2018 በጀት ዓመት ከጥር 25 እስከ ሰኔ 30 2018 በነጻ ስልክ መስመር 9995 ከህብረተሰቡ የመጡ ጥቆማዎች ፣ ቅሬታዎች እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት የውይይት መድረክ አካሂዷል ።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ የህዝብ ጥቆማዎችንና ቅሬታዎችን በሰፊው ለማስተናገድ የ 9995 ነጻ የጥሪ ማዕከል ዘመናዊ በማድረግ ሙሉ በሙሉ በኮምፒውተር እንዲደራጅ ተደርጎ በ3 ፈረቃ የ24 ሰዓት አገልግሎት መስጠት መጀመሩንና ማዕከሉ የከተማዋን ነዋሪዎች ስብጥር ባገናዘበ መልኩ ጥቆማዎችን በተለያዩ ቋንቋዎች ተቀብሎ ማስተናገድ የሚችሉ ባለሙያዎችን መድቦ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።
በመድረኩ በጥቆማ የሚመጡ ቅሬታዎች በምን አግባብ ተፈቱ ያልተፈቱ ካሉ በቀጣይ ችግሮቹን በመለየት መፍትሔ መስጠት እንደሚገባና ከሚመለከተው ተቋም በመተባበር የሚፈጠሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ እንደሚገባ ም/ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።
በ2018 በጀት ዓመት ከ 25/05/2018 እስከ 30/10/2018 በነጻ ስልክ መስመር 9995 ከህብረተሰቡ የመጡ ጥቆማዎች ፣ ቅሬታዎች እና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ሪፖርት ቀርቦ በመገምገም በቀጣይ ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል የትኩረት አቅጣጫ ተቀምጧል።
ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
።
👍13❤2👏2
"ለተገልጋይ እና አገልጋይ ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር የአገልግሎት እርካታን ማረጋገጥ" እንደሚገባ ተገለጸ።
ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በማዕከል የተጀመረው ምቹ የስራ አካባቢን የመፍጠር እና የአገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የመልካም አስተዳደር ተምሳሌትነቱን ለማረጋገጥ በየደረጃው በሚገኙ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ ጽህፈት ቤቶች የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች አጠናክሮ በማስቀጠል በዛሬው እለት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የሰራውን የቢሮ ማዘመን ስራ ተመርቆ ለዘመናዊ አገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ቢሮውን በማዘመን ምቹ የስራ አካባቢን ለመፍጠር በአዲስ መልኩ ያደራጀውን ቢሮ የማስመረቅ እንዲሁም አዲሱ የፓራ ሚሊተሪ የደንብ ልብስ ለተገልጋዮቹ የማስተዋወቅ መርሀ ግብር በዛሬው እለት አካሂዷል።
በመርሀ ግብሩ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ፣ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው እንዲሁም የ11ዱም ክ/ከተሞች ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት ለተገልጋይና አገልጋዩ ምቹ የስራ ቦታ በመፍጠር የአገልግሎት እርካታን ማረጋገጥ ያስፈልጋል በማለት በቀጣይም ይህ የሪፎርም ስራ ይበልጥ ተጠናክሮ በሌሎች ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ አክለውም ከማእከል ጀምሮ የዘመነ ተቋም መገንባቱን ገልጸው ወቅቱን የዋጀ በቴክኖሎጂ የታገዘ ብሎም ዘመናዊነት የተላበሰ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ በበኩላቸው የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ባደረጋቸው የሪፎርም ስራዎች እና በሚያከናውናቸው ተግባራቶች በከተማዋ የለውጥ አብነት መሆን ችሏል ለዚህም በህብረተሰቡ ዘንድ ስለ ተቋሙ ይሰነዘር የነበረውን አሉታዊ አመለካከት እንዲቀየር አድርጓል ብለዋል።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ይህ የተቋም ለውጥ ፍሬያማ እንዲሆን የአማራሩና ሰራተኛው ውህደት ትልቅ ሚና እንደነበረው ገልጸው አሁንም በአገልግሎት አሰጣጥ ብሎም በሪፎርም ስራዎች ሞዴል ሆነን ተልእኮዎቻችንን በስኬት እንወጣለን ብለዋል።
የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሻምበል ኦባድ ጁና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ በአዲስ መልኩ የተደራጀውን ቢሮ እና የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን አዲስ የደንብ ልብስ አስተዋውቀዋል።
ኃላፊው አክለውም ይህ ማሻሻያ በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥና መልካም አስተዳደርን በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ ያለውን ፋይዳ ገልጸው፣ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በመጨረሻም በምረቃ ስነ ስረአቱ የታደሙት የየክ/ከተማደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሀላፊዎች ከአመራር ቁርጠኝነት ጨምሮ ጥሩ ተሞክሮ እንዳገኙ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል
ዘገባው:- የባለስልጣኑ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በማዕከል የተጀመረው ምቹ የስራ አካባቢን የመፍጠር እና የአገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የመልካም አስተዳደር ተምሳሌትነቱን ለማረጋገጥ በየደረጃው በሚገኙ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ ጽህፈት ቤቶች የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች አጠናክሮ በማስቀጠል በዛሬው እለት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የሰራውን የቢሮ ማዘመን ስራ ተመርቆ ለዘመናዊ አገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ቢሮውን በማዘመን ምቹ የስራ አካባቢን ለመፍጠር በአዲስ መልኩ ያደራጀውን ቢሮ የማስመረቅ እንዲሁም አዲሱ የፓራ ሚሊተሪ የደንብ ልብስ ለተገልጋዮቹ የማስተዋወቅ መርሀ ግብር በዛሬው እለት አካሂዷል።
በመርሀ ግብሩ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ፣ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው እንዲሁም የ11ዱም ክ/ከተሞች ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት ለተገልጋይና አገልጋዩ ምቹ የስራ ቦታ በመፍጠር የአገልግሎት እርካታን ማረጋገጥ ያስፈልጋል በማለት በቀጣይም ይህ የሪፎርም ስራ ይበልጥ ተጠናክሮ በሌሎች ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ አክለውም ከማእከል ጀምሮ የዘመነ ተቋም መገንባቱን ገልጸው ወቅቱን የዋጀ በቴክኖሎጂ የታገዘ ብሎም ዘመናዊነት የተላበሰ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ በበኩላቸው የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ባደረጋቸው የሪፎርም ስራዎች እና በሚያከናውናቸው ተግባራቶች በከተማዋ የለውጥ አብነት መሆን ችሏል ለዚህም በህብረተሰቡ ዘንድ ስለ ተቋሙ ይሰነዘር የነበረውን አሉታዊ አመለካከት እንዲቀየር አድርጓል ብለዋል።
የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ይህ የተቋም ለውጥ ፍሬያማ እንዲሆን የአማራሩና ሰራተኛው ውህደት ትልቅ ሚና እንደነበረው ገልጸው አሁንም በአገልግሎት አሰጣጥ ብሎም በሪፎርም ስራዎች ሞዴል ሆነን ተልእኮዎቻችንን በስኬት እንወጣለን ብለዋል።
የክፍለ ከተማው የደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሻምበል ኦባድ ጁና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ በአዲስ መልኩ የተደራጀውን ቢሮ እና የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን አዲስ የደንብ ልብስ አስተዋውቀዋል።
ኃላፊው አክለውም ይህ ማሻሻያ በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥና መልካም አስተዳደርን በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ ያለውን ፋይዳ ገልጸው፣ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በመጨረሻም በምረቃ ስነ ስረአቱ የታደሙት የየክ/ከተማደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሀላፊዎች ከአመራር ቁርጠኝነት ጨምሮ ጥሩ ተሞክሮ እንዳገኙ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል
ዘገባው:- የባለስልጣኑ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
👍12❤2