የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.5K subscribers
3.96K photos
13 videos
1 file
93 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አአገልግሎት አሰጣጥ የሪፎርም ስራ በወረዳ ፅ/ቤቶቹ መተግበር መጀመሩ ተገለፀ

25/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ለሰራተኞች ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር ያከናወነውን የሪፎርም፣ የተቋም ግንባታ ስራዎች ከማዕከል አስከ ወረዳ የሚገኙ ኃላፊዎች በተገኙበት የቢሮ ጉብኝት ተካሂዷል ።

የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እየተከናወነ የሚገኘው ምቹ የስራ አከባቢን የመፍጠር እና የሪፎርም ስራዎች የተሰጠንን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት የሚያግዝ የሰራተኛውን የስራ ተነሳሽነት የሚጨምር እንዲሁም የምንሰጠው ቀልጣፋ አገልግሎት የተገልጋዩን ማህበረሰብ እርካታ የሚጨምር መሆኑን ገልጸዋል ።

አክለውም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር አአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ማዘመንና ቀልጣፋ ማድረግ እንደሚገባና እየተከናወኑ የሚገኘው የሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል ።

ወረዳው በከተማ ደረጃ የተጀመረውን የሪፎርም ስራ በማስቀጠል ለሰራተኞች እና ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር እንዲሁም ስራዎችን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግና የደንብ መተላለፎችን በዘመናዊ መንገድ ለመከታተል ከኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር የሁኔታዎች መከታተያ ክፍል አዘጋጅቷል
በተጨማሪም ለሰራተኞቹ ምቹ የማደሪያ ክፍል፣ ልብስ መቀየሪያ ፣ ምግብ ማብሰያ ክፍልና ሻወር ቤት አዘጋጅቷል ።

የጉብኝቱ ተሳታፊዎች አሁን በወረዳው የታየው አበረታች አፈጻጸም በሚሰሩበት አካባቢዎች ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባው በመሆኑ የተጀመረውን የሪፎርምና የተቋም ግንባታ ሥራ በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል በቁርጠኝነት የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል ።
👍107👏4
ባለስልጣኑ "ደም መለገስ ህይወት መስጠት ነው" መሪ ቃል የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

02/11/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

​የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ጋር በመተባበር "ደም መለገስ ህይወት መስጠት ነው" በሚል መሪ ቃል ያዘጋጁት ታላቅ የደም ልገሳ መርሐ-ግብር በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ተከናውኗል።

​በደም ልገሳ መርሐ-ግብር ላይ የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ባደረጉት ንግግር የደንብ ማስከበር ተቋም የከተማዋን ሰላምና ሥርዓት ከመጠበቅና ሕግን ከማስከበር ጎን ለጎን የሕዝብን ሕይወት ለመታደግና ወገንተኝነትን ለማሳየት በሚደረጉ መሰል የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ ሁልጊዜም ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆኑን ገልጸዋል።

አክለውም ደም መለገስ ለወገን ሕይወት መታደግ ብቻ ሳይሆን በራሱ ታላቅ ሰብአዊነትና የውስጥ እርካታ የሚገኝበት የበጎነት ማሳያ ነው በማለት በልገሳው ላይ በንቃት ለተሳተፉ የተቋሙ አመራሮች፣ የቢሮ ባለሙያዎችና ለደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ታላቅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

​የአዲስ አበባ ከተማ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ወ/ሮ አስራት ንጉሴ በከተማችን የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ባህልን ለማሳደግና የማኅበረሰቡን ትብብር ለማጠናከር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ጠቁመዋል።

የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አባላት የከተማዋን ደንብና ሥርዓት በቁርጠኝነት ከመጠበቅ ባለፈ በዛሬ ለሕይወት ሕይወት የሚሆነውን ደማቸውን በመለገስ ያሳዩት ወገንተኝነት እጅግ የሚያስመሰግንና ለሌሎች ተቋማትም ትልቅ አርአያ የሚሆን ነው ሲሉ ወ/ሮ አስራት ገልጸዋል።

​በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው በዚህ መርሐ-ግብር ላይ የሁለቱ ተቋማት አመራሮች፣ ሠራተኞች ፣ የክ/ከተማና የወረዳ ደንብ ማስከበር ኃላፊዎች እና ኦፊሰሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን፣ የተሰበሰበው ደም በሕክምና ማዕከላት ለሚገኙና ደም ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ሕይወትን እንደሚታደግ ተገልጿል።

ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
👍133👏3