የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.5K subscribers
3.96K photos
13 videos
1 file
93 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
በበጀት አመቱ የደንብ መተላለፎች በ81.3% መቀነስ መቻሉ ተገለፀ ።

20/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክፍለ ከተማና ወረዳ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎች አስቀምጧል ።

በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት ጠንካራ አፈፃፀሞችን ያስመዘገበ መሆኑን ገልጸው፣ የተገኙ ስኬቶችን ይበልጥ ለማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በ2019 በጀት ዓመት ለመሙላት መድረኩ መዘጋጀቱን አስገንዝበዋል።

​ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ በበጀት ዓመቱ ካከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል በተለይ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ በሕግ ማስከበር፣ በተቋም ግንባታ እና በሰው ኃይል አቅም ማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ርቀት መጓዙ ተገልጿል።

ቀደም ሲል አናሎግ የነበረውና በቀን ለ12 ሰዓታት ብቻ አገልግሎት ይሰጥ የነበረው የ9995 የጥሪ መስመር ወደ ዲጂታል በመቀየር፣ በአሁኑ ወቅት በአምስት ቋንቋዎች የ24 ሰዓት ሙሉ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገልፆ በቀን ከ200 እስከ 300 የሚደርሱ ጥቆማዎችን በመቀበል፣ ከሕዝብ በሚገኝ መረጃ ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ የመፈፀም አቅምን ለማሳደግ ለነባር ኦፊሰሮች እና አመራሮች በኢትዮጽያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በሰንዳፋ እና በአዳይቱ የመፈጸም አቅምን የሚያሳድጉ ጠንካራ ስልጠናዎች ተሰጥተዋል።

​በኮሪደር ልማት የተሰሩ መሰረተ ልማቶችን ከመጠበቅ አንፃር ተቋሙ ሌት ተቀን እየሰራ ይገኛል። ከዚህ ባለፈም ከመሬት አስተዳደር ጋር በተያያዘ ወደ መሬት ባንክ የገቡ መሬቶችን ሙሉ በሙሉ ማስከበር የተቻለ ሲሆን፣ ከ9ኙ የደንብ ጥሰቶች (የጎዳና ንግድ፣ የደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ፣ ሕገ-ወጥ ማስታወቂያ እና ሌሎችም) ጋር በተያያዘ በተደረገ ጠንካራ ስራ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ81.3% ብልጫ ያለው ውጤት ተመዝግቧል ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት በእቅድ አፈጻጸም የተከናወኑ አበይት ተግባራት ፣ የገጠሙ ተግዳሮቶች ፣ የተወሰዱ የመፍትሄ ሪፖርት በባለስልጣኑ እቅድና በጀት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ ቀርቧል ።

በመድረኩ የ2019 በጀት ዓመት መሪ እቅድ እና የቀጣይ 90 ቀናት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በመጨረሻም በመድረኩ የተሳተፉ አመራሮችና ዳይሬክተሬቶች በቀረበው ሪፖርት እና እቅድ ላይ ሀሳብናና ጥያቄዎች አቅርበው ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶበት ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ዋና ስራ አስኪያጁ አስቀምጠዋል ።

ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
👍81👎1
ባለስልጣኑ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ መርኃ ግብር አካሄደ

23/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን "ተስፋን እንትከል " በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፍቃድ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርዓ ግብር በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በብሔረ ጽጌ ፓርክ አካሂዷል ።

የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደገለጹት ይህ የችግኝ ተከላ መርኃ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትራችን እና በከተማችን ከንቲባ የተጀመረውን የ90 ቀን የክረምት እቅድ ለማስቀጠል ተቋሙ የጀመረው ስራ መሆኑን ጠቁመዋል።
አክለውም ባለስልጣኑ ባለፈው ዓመት 18 ሺህ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በዘንድሮው ዓመት ተጨማሪ 2 ሺህ በመጨመር በአጠቃላይ 20 ሺህ ችግኞችን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ እንደሚተክል አስታውቀዋል።

ተስፋን መትከል ማለት ዛሬ ላይ ሆኖ ነገን ብሩህ አድርጎ ማየት ማለት ነው፤ ነገ ብሩህ የሆነ ብልጽግናን ማየት ማለት ነው። ዛሬ የተከልነውን ነገ ፍሬውን እንለቅማለን ሲሉ ዋና ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል ።

ከችግኝ ተከላው በተጨማሪም ተቋሙ የደም ልገሳ፣ የማዕድ ማጋራት እና ሌሎች የበጎ አድራጎት ስራዎችን በቀጣይ እንደሚያከናውን አረጋግጠዋል።

​የመርኃ ግብሩ የክብር እንግዳ የሆኑት የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አህመድ ሀሰን የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ስያሜውን ቀይሮ በህዝብ ዘንድ የነበረውን የእምነት ጉድለት በማረምና የሪፎርም ስራዎችን በብቃት በመተግበር ዛሬ ለደረሰበት የላቀ ደረጃ ላይ መብቃቱን ገልጸዋል።

ይህ መርኃ ግብር ልምላሜን፣ የከተማችንን አረንጓዴነት፣ የነዋሪዎቿን ምግብ እና ተስፋን የምንተክልበት በመሆኑ ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን የበኩላችንን ኃላፊነት መወጣት ይጠበቅብናል ሲሉ አቶ አህመድ ገልጸዋል ።

ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
👍143
የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አአገልግሎት አሰጣጥ የሪፎርም ስራ በወረዳ ፅ/ቤቶቹ መተግበር መጀመሩ ተገለፀ

25/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ለሰራተኞች ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር ያከናወነውን የሪፎርም፣ የተቋም ግንባታ ስራዎች ከማዕከል አስከ ወረዳ የሚገኙ ኃላፊዎች በተገኙበት የቢሮ ጉብኝት ተካሂዷል ።

የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እየተከናወነ የሚገኘው ምቹ የስራ አከባቢን የመፍጠር እና የሪፎርም ስራዎች የተሰጠንን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት የሚያግዝ የሰራተኛውን የስራ ተነሳሽነት የሚጨምር እንዲሁም የምንሰጠው ቀልጣፋ አገልግሎት የተገልጋዩን ማህበረሰብ እርካታ የሚጨምር መሆኑን ገልጸዋል ።

አክለውም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር አአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ማዘመንና ቀልጣፋ ማድረግ እንደሚገባና እየተከናወኑ የሚገኘው የሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል ።

ወረዳው በከተማ ደረጃ የተጀመረውን የሪፎርም ስራ በማስቀጠል ለሰራተኞች እና ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር እንዲሁም ስራዎችን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግና የደንብ መተላለፎችን በዘመናዊ መንገድ ለመከታተል ከኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር የሁኔታዎች መከታተያ ክፍል አዘጋጅቷል
በተጨማሪም ለሰራተኞቹ ምቹ የማደሪያ ክፍል፣ ልብስ መቀየሪያ ፣ ምግብ ማብሰያ ክፍልና ሻወር ቤት አዘጋጅቷል ።

የጉብኝቱ ተሳታፊዎች አሁን በወረዳው የታየው አበረታች አፈጻጸም በሚሰሩበት አካባቢዎች ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባው በመሆኑ የተጀመረውን የሪፎርምና የተቋም ግንባታ ሥራ በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል በቁርጠኝነት የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል ።
👍107👏4