የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.5K subscribers
3.96K photos
13 videos
1 file
93 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣኑ የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ ያለአግባብ በኮሪደር ልማት ላይ የለቀቁ አልፎዝ ፕላዛ እና ሳሚ ህንፃ /800,000/ስምንት መቶ ሺህ ብር መቅጣቱን ገለፀ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13፣ ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ የሚገኘውአልፎዝ ፕላዛ እና "ሳሚ ህንፃ" ከፍተኛ የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ተገነባው የኮሪደር መስመር በመልቀቅ አካባቢውን በመበከላቸው አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል።

ቅጣቱ የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ) መሰረት፣ ህግ በመተላለፋቸው እያንዳንዳቸው 400,000 (አራት መቶ ሺህ) ብር በድምሩ 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ።

የተወሰደው እርምጃ የከተማዋን ውበት ለመጠበቅ እና የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል የወጡ ደንቦችን ለማስከበር የተጀመረው ጥብቅ ቁጥጥር አካል መሆኑ ተገልጿል።

ባለስልጣኑ ማንኛውም ተቋም እና ግለሰብ መሰል የብክለት ተግባራትን ከመፈጸም እንዲቆጠብ እና የወጡ ህጎችን እንዲያከብሩ ጥሪው አስተላልፏል ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፍ ድርጊት በሚፈፅሙ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የሚወሰደው እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

ባለስልጣኑ መረጃውን ለሚሰጡት የህብረተሰብ ክፍል እያመሠገነ ሁሉም ነዋሪዎች ደንቡን ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲመለከት በነፃ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን አስተላልፏል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
👏7👍3
ባለስልጣኑ ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር የሚዲያ ስራዎች የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

16/10/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የሚያከናውናቸውን ተግባራት ወደ ህብረተሰቡ ተደራሽነቱን ለማስፋት ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር በ2019 በጀት ዓመት በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተፈራርመዋል።

የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋማቸው ራዕይ ለማሳካትና የተቋሙ መረጃዎች ወደ ሰፊው ማህበረሰብ ለማስፋት ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋር የስራ ስምምነት መፈራረም ማስፈለጉን አብራርተዋል፡፡

ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር እየተሰሩ የሚገኙት ፕሮግራሞች ከተቋም ገጽታ ግንባታ፣ ደንብ መተላለፎችን ከመከላከል እና ግንዛቤ ከመፍጠር አንጻር መልካም ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል

የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ዲባባ ተቋሙ ከከተማዋ ልማትና እድገት ጋር አብሮ በማደግ ላይ ያለ ተወዳዳሪና የሌሎች ሚዲያ ተምሳሌት ለመሆኑን እየሰራ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል።

ተቋሙ በኤኤምኤን ቴሌቭዥን፣ በኤኤምኤን ፕላስ፤በሬዲዮ፣ በሕትመት እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን በፍጥነት እና በጥራት ተደራሽ በማድረግ የብዙኃን አንደበት ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ ተናግረዋል

ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ቋንቋዎች መረጃዎችን ለአድማጭ ተመልካች እያቀረበ መሆኑን ገልጸው ሚዲያው ከተቋሙ ጋር በጋራ በመሆን ባከናወናቸው ስራዎች የባለስልጣኑን የግንዛቤ አድማስ ማስፋት የተቻለ መሆን ጠቅሰው፤ በቀጣይ የአቀራረብ ይዘቱን በማሻሻል ይበልጥ ሳቢ በማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍116👏1
የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በማዕከል የተጀመረው የሪፎርም ስራዎች አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል አስታወቀ

18/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰር እና አመራር ስልጠና ማጠቃለያ ፤ አዲሱን የፓራ ሚሊተሪ የደንብ ልብስ ምርቃት ፕሮግራም በከተማው በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት "ከስልጠና ወደ ስምሪት ፤ በዕውቀትና በቁርጠኝነት " በሚል መሪ ቃል የስራ ስምሪት መድረክ አካሄደ ።

በመድረኩ የተገኙት የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ አሕመድ ሀሰን ደንብ ማስከበር ባለፋት አመታት ራሱን በማዘመን በፊት ይነሳ የነበረውን ስም በማደስ ክፍተቶችን በማረም በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ቀን ከለሊት ጠንክሮ በመስራት ውጤታማ በመሆን ለሌሎች አርአያ እየሆነ ይገኛል ሱሉ ተናግረዋል ።

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ መቶ አለቃ ቦጋለ አለሙ በማዕከል የተጀመረው የሪፎርም ስራዎች አጠናክሮ እንደሚያስቀጥሉ በመግለፅ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ፣ በሰንዳፋና አዳይቱ ማሰልጠኛ ማዕከላት በ10 ተከታታይ ዙሮች የንድፈ ሃሳብና የተግባር ስልጠና የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት 681 የፓራ ሚሊተሪ አባላት እና አመራሮች ተሳትፈው ስልጠናቸውን በስኬት ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

ተቋሙ እየገነባው ካለው ዘመናዊ አደረጃጀትና ሙያዊ ክብር ጋር የሚመጥን አዲስ የደንብ ልብስ ያሳመረቀ ሲሆን በዛሬው ዕለት የንፋስ ስልክ ላፍቶ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የክፍለ ከተማው ዋና ሰራ አስፈጻሚ እና ሌሎች የክፍለ ከተማው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት አዲሱን የፖራ ሚሊተሪ የደንብ ልብስ አስተዋውቋል።

የማህበራዊ ችግር ለገጠማት በክፍለ ከተማው የምታገለግል የደንብ ማስከበር ኦፊሰር ድጋፍ የተደረገ ሲሆን የሚደረግላቸውን ድጋፍ በቀጣይም እንደሚቀጥል ተገልጿል።

ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
11👍5