ባለስልጣኑ የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ ያለአግባብ በኮሪደር ልማት ላይ የለቀቁ አልፎዝ ፕላዛ እና ሳሚ ህንፃ /800,000/ስምንት መቶ ሺህ ብር መቅጣቱን ገለፀ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13፣ ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ የሚገኘውአልፎዝ ፕላዛ እና "ሳሚ ህንፃ" ከፍተኛ የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ተገነባው የኮሪደር መስመር በመልቀቅ አካባቢውን በመበከላቸው አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል።
ቅጣቱ የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ) መሰረት፣ ህግ በመተላለፋቸው እያንዳንዳቸው 400,000 (አራት መቶ ሺህ) ብር በድምሩ 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ።
የተወሰደው እርምጃ የከተማዋን ውበት ለመጠበቅ እና የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል የወጡ ደንቦችን ለማስከበር የተጀመረው ጥብቅ ቁጥጥር አካል መሆኑ ተገልጿል።
ባለስልጣኑ ማንኛውም ተቋም እና ግለሰብ መሰል የብክለት ተግባራትን ከመፈጸም እንዲቆጠብ እና የወጡ ህጎችን እንዲያከብሩ ጥሪው አስተላልፏል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፍ ድርጊት በሚፈፅሙ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የሚወሰደው እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ባለስልጣኑ መረጃውን ለሚሰጡት የህብረተሰብ ክፍል እያመሠገነ ሁሉም ነዋሪዎች ደንቡን ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲመለከት በነፃ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን አስተላልፏል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13፣ ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ የሚገኘውአልፎዝ ፕላዛ እና "ሳሚ ህንፃ" ከፍተኛ የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ተገነባው የኮሪደር መስመር በመልቀቅ አካባቢውን በመበከላቸው አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል።
ቅጣቱ የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ) መሰረት፣ ህግ በመተላለፋቸው እያንዳንዳቸው 400,000 (አራት መቶ ሺህ) ብር በድምሩ 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ።
የተወሰደው እርምጃ የከተማዋን ውበት ለመጠበቅ እና የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል የወጡ ደንቦችን ለማስከበር የተጀመረው ጥብቅ ቁጥጥር አካል መሆኑ ተገልጿል።
ባለስልጣኑ ማንኛውም ተቋም እና ግለሰብ መሰል የብክለት ተግባራትን ከመፈጸም እንዲቆጠብ እና የወጡ ህጎችን እንዲያከብሩ ጥሪው አስተላልፏል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፍ ድርጊት በሚፈፅሙ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የሚወሰደው እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ባለስልጣኑ መረጃውን ለሚሰጡት የህብረተሰብ ክፍል እያመሠገነ ሁሉም ነዋሪዎች ደንቡን ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲመለከት በነፃ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን አስተላልፏል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
👏7👍3
ባለስልጣኑ ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር የሚዲያ ስራዎች የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ
16/10/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የሚያከናውናቸውን ተግባራት ወደ ህብረተሰቡ ተደራሽነቱን ለማስፋት ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር በ2019 በጀት ዓመት በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተፈራርመዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋማቸው ራዕይ ለማሳካትና የተቋሙ መረጃዎች ወደ ሰፊው ማህበረሰብ ለማስፋት ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋር የስራ ስምምነት መፈራረም ማስፈለጉን አብራርተዋል፡፡
ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር እየተሰሩ የሚገኙት ፕሮግራሞች ከተቋም ገጽታ ግንባታ፣ ደንብ መተላለፎችን ከመከላከል እና ግንዛቤ ከመፍጠር አንጻር መልካም ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል
የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ዲባባ ተቋሙ ከከተማዋ ልማትና እድገት ጋር አብሮ በማደግ ላይ ያለ ተወዳዳሪና የሌሎች ሚዲያ ተምሳሌት ለመሆኑን እየሰራ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል።
ተቋሙ በኤኤምኤን ቴሌቭዥን፣ በኤኤምኤን ፕላስ፤በሬዲዮ፣ በሕትመት እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን በፍጥነት እና በጥራት ተደራሽ በማድረግ የብዙኃን አንደበት ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ ተናግረዋል
ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ቋንቋዎች መረጃዎችን ለአድማጭ ተመልካች እያቀረበ መሆኑን ገልጸው ሚዲያው ከተቋሙ ጋር በጋራ በመሆን ባከናወናቸው ስራዎች የባለስልጣኑን የግንዛቤ አድማስ ማስፋት የተቻለ መሆን ጠቅሰው፤ በቀጣይ የአቀራረብ ይዘቱን በማሻሻል ይበልጥ ሳቢ በማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
16/10/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የሚያከናውናቸውን ተግባራት ወደ ህብረተሰቡ ተደራሽነቱን ለማስፋት ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር በ2019 በጀት ዓመት በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተፈራርመዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋማቸው ራዕይ ለማሳካትና የተቋሙ መረጃዎች ወደ ሰፊው ማህበረሰብ ለማስፋት ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋር የስራ ስምምነት መፈራረም ማስፈለጉን አብራርተዋል፡፡
ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር እየተሰሩ የሚገኙት ፕሮግራሞች ከተቋም ገጽታ ግንባታ፣ ደንብ መተላለፎችን ከመከላከል እና ግንዛቤ ከመፍጠር አንጻር መልካም ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል
የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ዲባባ ተቋሙ ከከተማዋ ልማትና እድገት ጋር አብሮ በማደግ ላይ ያለ ተወዳዳሪና የሌሎች ሚዲያ ተምሳሌት ለመሆኑን እየሰራ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል።
ተቋሙ በኤኤምኤን ቴሌቭዥን፣ በኤኤምኤን ፕላስ፤በሬዲዮ፣ በሕትመት እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን በፍጥነት እና በጥራት ተደራሽ በማድረግ የብዙኃን አንደበት ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ ተናግረዋል
ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ቋንቋዎች መረጃዎችን ለአድማጭ ተመልካች እያቀረበ መሆኑን ገልጸው ሚዲያው ከተቋሙ ጋር በጋራ በመሆን ባከናወናቸው ስራዎች የባለስልጣኑን የግንዛቤ አድማስ ማስፋት የተቻለ መሆን ጠቅሰው፤ በቀጣይ የአቀራረብ ይዘቱን በማሻሻል ይበልጥ ሳቢ በማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍11❤6👏1