ባለስልጣኑ የፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች የሥልጠና ማጠቃለያ እና አዲስ የደንብ ልብስ ትውውቅ አደረገ
13/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች የሥልጠና ማጠቃለያ እና የደንብ ልብስ ትውውቅ ፕሮግራም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ እንዲሁም የከተማው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አካሂዷል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ የከተማ አስተዳደሩ ተቋሙን ለማደራጀት የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ ቆይቷል።በዚም አግባብ ባለስልጣኑ እራሱን በአስራር፣ በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ አዘምኖ ለሌሎች ተቋማት ጭምር ተምሳሌት በመሆን ላይ ይገኛል ይህን አርአያነቱን አጠናክሮ በመቀጠል እራሱን ብራንድ ተቋም በማድረግ የከተማዋን ራዕይ እውን ለማድረግ እየሰራ ይገኛል ብለዋል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደገለጹት ተቋሙ ራሱን በዕውቀት፣ በቴክኖሎጂና በሰለጠነ የሰው ኃይል ለመገንባት ሰፊ የሪፎርም ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል። በዚህም በ2017 በጀት ዓመት ከከተማ አስተዳደሩ የተሰጠው እውቅና ለበለጠ ስራ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑን አስታውሰዋል።
በ2018 በጀት ዓመት የተቋሙን አመራሮችና አባላት አቅም ለመገንባት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ፣ በሰንዳፋና አዳይቱ ማሰልጠኛ ማዕከላት በ10 ተከታታይ ዙሮች የንድፈ ሃሳብና የተግባር ስልጠና ተሰጥቷል።
በዚህ ስልጠና ላይ 7,893 የፓራ ሚሊተሪ አባላት እና 148 አመራሮች በድምሩ 8,039 ሰልጣኞች ተሳትፈው ስልጠናቸውን በስኬት ማጠናቀቃቸው ሻለቃ ዘሪሁን ገልጸዋል።
የአቅም ግንባታ ስልጠና አባላቱ ከህዝብ ጋር በክብርና በሰላማዊ መንገድ እንዲግባቡ፣ ህግና ስርዓትን ያለ ምንም አድልዎ እንዲያስከብሩ፣ እንዲሁም የተሟላ ስነ-ምግባርና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ክህሎት ኖሯቸው ህዝብን በታማኝነት እንዲያገለግሉ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተመላክቷል።
ተቋሙ እየገነባው ካለው ዘመናዊ አደረጃጀትና ሙያዊ ስነምግባር የሚመጥን አዲስ የደንብ ልብስ በዛሬው ዕለት በይፋ አስተዋውቋል።
ይህ አዲስ የደንብ ልብስ አለም አቀፍ ተሞክሮዎችንና ደረጃዎችን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ ሲሆን አባላቱም ይህንን አዲስ የደንብ ልብስ ሲለብሱ ትልቅ ህዝባዊ አደራ መሸከማቸውን ተገንዝበው በኃላፊነት ስሜት መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን፣ በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ በንቃት ለመሳተፍ የ90 ቀን እቅድ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱ ተገልጿል። በዚህም አቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የአረንጓዴ አሻራ፣ የወላጆችን ማዕድ ማጋራት፣ የደም ልገሳ እና የአደጋ ስጋት ቅነሳ ተግባራት በዋናነት እንደሚከናወኑ ተጠቁሟል።
በዕለቱ በስራ ላይ እያሉ የአካልና የጤና ጉዳት የደረሰባቸው አባላትና የሰማዕታት ቤተሰቦችም በልዩ ክብር እንደሚታሰቡና የሚደረግላቸውን ድጋፍ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
ጠንካራ የአገልግሎት ስርዓት ያላቸው ፣ ስነምግባር የተላበሱ ፣ አገልጋይ ባለሙያዎችን እና አመራሮችን የመፍጠር ተቋማዊ የሪፎርም ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ፦ https://linktr.ee/aacodeenforcement
13/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች የሥልጠና ማጠቃለያ እና የደንብ ልብስ ትውውቅ ፕሮግራም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ እንዲሁም የከተማው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አካሂዷል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ የከተማ አስተዳደሩ ተቋሙን ለማደራጀት የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ ቆይቷል።በዚም አግባብ ባለስልጣኑ እራሱን በአስራር፣ በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ አዘምኖ ለሌሎች ተቋማት ጭምር ተምሳሌት በመሆን ላይ ይገኛል ይህን አርአያነቱን አጠናክሮ በመቀጠል እራሱን ብራንድ ተቋም በማድረግ የከተማዋን ራዕይ እውን ለማድረግ እየሰራ ይገኛል ብለዋል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደገለጹት ተቋሙ ራሱን በዕውቀት፣ በቴክኖሎጂና በሰለጠነ የሰው ኃይል ለመገንባት ሰፊ የሪፎርም ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል። በዚህም በ2017 በጀት ዓመት ከከተማ አስተዳደሩ የተሰጠው እውቅና ለበለጠ ስራ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑን አስታውሰዋል።
በ2018 በጀት ዓመት የተቋሙን አመራሮችና አባላት አቅም ለመገንባት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ፣ በሰንዳፋና አዳይቱ ማሰልጠኛ ማዕከላት በ10 ተከታታይ ዙሮች የንድፈ ሃሳብና የተግባር ስልጠና ተሰጥቷል።
በዚህ ስልጠና ላይ 7,893 የፓራ ሚሊተሪ አባላት እና 148 አመራሮች በድምሩ 8,039 ሰልጣኞች ተሳትፈው ስልጠናቸውን በስኬት ማጠናቀቃቸው ሻለቃ ዘሪሁን ገልጸዋል።
የአቅም ግንባታ ስልጠና አባላቱ ከህዝብ ጋር በክብርና በሰላማዊ መንገድ እንዲግባቡ፣ ህግና ስርዓትን ያለ ምንም አድልዎ እንዲያስከብሩ፣ እንዲሁም የተሟላ ስነ-ምግባርና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ክህሎት ኖሯቸው ህዝብን በታማኝነት እንዲያገለግሉ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተመላክቷል።
ተቋሙ እየገነባው ካለው ዘመናዊ አደረጃጀትና ሙያዊ ስነምግባር የሚመጥን አዲስ የደንብ ልብስ በዛሬው ዕለት በይፋ አስተዋውቋል።
ይህ አዲስ የደንብ ልብስ አለም አቀፍ ተሞክሮዎችንና ደረጃዎችን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ ሲሆን አባላቱም ይህንን አዲስ የደንብ ልብስ ሲለብሱ ትልቅ ህዝባዊ አደራ መሸከማቸውን ተገንዝበው በኃላፊነት ስሜት መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን፣ በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ በንቃት ለመሳተፍ የ90 ቀን እቅድ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱ ተገልጿል። በዚህም አቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የአረንጓዴ አሻራ፣ የወላጆችን ማዕድ ማጋራት፣ የደም ልገሳ እና የአደጋ ስጋት ቅነሳ ተግባራት በዋናነት እንደሚከናወኑ ተጠቁሟል።
በዕለቱ በስራ ላይ እያሉ የአካልና የጤና ጉዳት የደረሰባቸው አባላትና የሰማዕታት ቤተሰቦችም በልዩ ክብር እንደሚታሰቡና የሚደረግላቸውን ድጋፍ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
ጠንካራ የአገልግሎት ስርዓት ያላቸው ፣ ስነምግባር የተላበሱ ፣ አገልጋይ ባለሙያዎችን እና አመራሮችን የመፍጠር ተቋማዊ የሪፎርም ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ፦ https://linktr.ee/aacodeenforcement
❤5👍1
ባለስልጣኑ የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ ያለአግባብ በኮሪደር ልማት ላይ የለቀቁ አልፎዝ ፕላዛ እና ሳሚ ህንፃ /800,000/ስምንት መቶ ሺህ ብር መቅጣቱን ገለፀ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13፣ ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ የሚገኘውአልፎዝ ፕላዛ እና "ሳሚ ህንፃ" ከፍተኛ የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ተገነባው የኮሪደር መስመር በመልቀቅ አካባቢውን በመበከላቸው አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል።
ቅጣቱ የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ) መሰረት፣ ህግ በመተላለፋቸው እያንዳንዳቸው 400,000 (አራት መቶ ሺህ) ብር በድምሩ 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ።
የተወሰደው እርምጃ የከተማዋን ውበት ለመጠበቅ እና የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል የወጡ ደንቦችን ለማስከበር የተጀመረው ጥብቅ ቁጥጥር አካል መሆኑ ተገልጿል።
ባለስልጣኑ ማንኛውም ተቋም እና ግለሰብ መሰል የብክለት ተግባራትን ከመፈጸም እንዲቆጠብ እና የወጡ ህጎችን እንዲያከብሩ ጥሪው አስተላልፏል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፍ ድርጊት በሚፈፅሙ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የሚወሰደው እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ባለስልጣኑ መረጃውን ለሚሰጡት የህብረተሰብ ክፍል እያመሠገነ ሁሉም ነዋሪዎች ደንቡን ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲመለከት በነፃ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን አስተላልፏል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13፣ ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ የሚገኘውአልፎዝ ፕላዛ እና "ሳሚ ህንፃ" ከፍተኛ የሽንት ቤት ፍሳሽ ወደ ተገነባው የኮሪደር መስመር በመልቀቅ አካባቢውን በመበከላቸው አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል።
ቅጣቱ የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ) መሰረት፣ ህግ በመተላለፋቸው እያንዳንዳቸው 400,000 (አራት መቶ ሺህ) ብር በድምሩ 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ።
የተወሰደው እርምጃ የከተማዋን ውበት ለመጠበቅ እና የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል የወጡ ደንቦችን ለማስከበር የተጀመረው ጥብቅ ቁጥጥር አካል መሆኑ ተገልጿል።
ባለስልጣኑ ማንኛውም ተቋም እና ግለሰብ መሰል የብክለት ተግባራትን ከመፈጸም እንዲቆጠብ እና የወጡ ህጎችን እንዲያከብሩ ጥሪው አስተላልፏል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የደንብ መተላለፍ ድርጊት በሚፈፅሙ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የሚወሰደው እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ባለስልጣኑ መረጃውን ለሚሰጡት የህብረተሰብ ክፍል እያመሠገነ ሁሉም ነዋሪዎች ደንቡን ተላልፎ የሚገኝ አካል ሲመለከት በነፃ የስልክ መስመር 9995 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን አስተላልፏል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
👏7👍3
ባለስልጣኑ ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር የሚዲያ ስራዎች የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ
16/10/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የሚያከናውናቸውን ተግባራት ወደ ህብረተሰቡ ተደራሽነቱን ለማስፋት ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር በ2019 በጀት ዓመት በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተፈራርመዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋማቸው ራዕይ ለማሳካትና የተቋሙ መረጃዎች ወደ ሰፊው ማህበረሰብ ለማስፋት ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋር የስራ ስምምነት መፈራረም ማስፈለጉን አብራርተዋል፡፡
ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር እየተሰሩ የሚገኙት ፕሮግራሞች ከተቋም ገጽታ ግንባታ፣ ደንብ መተላለፎችን ከመከላከል እና ግንዛቤ ከመፍጠር አንጻር መልካም ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል
የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ዲባባ ተቋሙ ከከተማዋ ልማትና እድገት ጋር አብሮ በማደግ ላይ ያለ ተወዳዳሪና የሌሎች ሚዲያ ተምሳሌት ለመሆኑን እየሰራ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል።
ተቋሙ በኤኤምኤን ቴሌቭዥን፣ በኤኤምኤን ፕላስ፤በሬዲዮ፣ በሕትመት እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን በፍጥነት እና በጥራት ተደራሽ በማድረግ የብዙኃን አንደበት ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ ተናግረዋል
ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ቋንቋዎች መረጃዎችን ለአድማጭ ተመልካች እያቀረበ መሆኑን ገልጸው ሚዲያው ከተቋሙ ጋር በጋራ በመሆን ባከናወናቸው ስራዎች የባለስልጣኑን የግንዛቤ አድማስ ማስፋት የተቻለ መሆን ጠቅሰው፤ በቀጣይ የአቀራረብ ይዘቱን በማሻሻል ይበልጥ ሳቢ በማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
16/10/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የሚያከናውናቸውን ተግባራት ወደ ህብረተሰቡ ተደራሽነቱን ለማስፋት ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር በ2019 በጀት ዓመት በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተፈራርመዋል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የተቋማቸው ራዕይ ለማሳካትና የተቋሙ መረጃዎች ወደ ሰፊው ማህበረሰብ ለማስፋት ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋር የስራ ስምምነት መፈራረም ማስፈለጉን አብራርተዋል፡፡
ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር እየተሰሩ የሚገኙት ፕሮግራሞች ከተቋም ገጽታ ግንባታ፣ ደንብ መተላለፎችን ከመከላከል እና ግንዛቤ ከመፍጠር አንጻር መልካም ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል
የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ዲባባ ተቋሙ ከከተማዋ ልማትና እድገት ጋር አብሮ በማደግ ላይ ያለ ተወዳዳሪና የሌሎች ሚዲያ ተምሳሌት ለመሆኑን እየሰራ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል።
ተቋሙ በኤኤምኤን ቴሌቭዥን፣ በኤኤምኤን ፕላስ፤በሬዲዮ፣ በሕትመት እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን በፍጥነት እና በጥራት ተደራሽ በማድረግ የብዙኃን አንደበት ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝ ተናግረዋል
ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ቋንቋዎች መረጃዎችን ለአድማጭ ተመልካች እያቀረበ መሆኑን ገልጸው ሚዲያው ከተቋሙ ጋር በጋራ በመሆን ባከናወናቸው ስራዎች የባለስልጣኑን የግንዛቤ አድማስ ማስፋት የተቻለ መሆን ጠቅሰው፤ በቀጣይ የአቀራረብ ይዘቱን በማሻሻል ይበልጥ ሳቢ በማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍11❤6👏1