ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በከተማችን በሰላም እንዲጠናቀቅ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑ ተገለፀ
12/09/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቅድመ ምርጫ በምርጫ እለት እና በድህረ ምርጫ ወቅት የተቀናጀና የተጠናከረ የጥበቃና የሰላም ግንባታ ተግባራትን በማከናወን ሰላማዊ ምርጫ እንዲከናወን የውይይት መድረክ አካሄደ ።
ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ እጅግ ሰላማዊ ፣ ነጻ ፣ ፍትሀዊና ተዓማኒ በማድረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታውን ወደ ላቀ ደረጃ ማሻገር እንደሚገባ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል ።
አክለውም የደንብ ማስከበር አመራርና ኦፊሰር ምርጫው በከተማችን በሰላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ የሚገኙ ሲሆን ይሄንንም በቀጣይ በምርጫ እለት እና በድህረ ምርጫ ወቅት አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።
ለሀገራችን ሰላም እና ደህንነት በጋራ መቆም እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል ።
ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
12/09/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቅድመ ምርጫ በምርጫ እለት እና በድህረ ምርጫ ወቅት የተቀናጀና የተጠናከረ የጥበቃና የሰላም ግንባታ ተግባራትን በማከናወን ሰላማዊ ምርጫ እንዲከናወን የውይይት መድረክ አካሄደ ።
ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ እጅግ ሰላማዊ ፣ ነጻ ፣ ፍትሀዊና ተዓማኒ በማድረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታውን ወደ ላቀ ደረጃ ማሻገር እንደሚገባ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል ።
አክለውም የደንብ ማስከበር አመራርና ኦፊሰር ምርጫው በከተማችን በሰላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ የሚገኙ ሲሆን ይሄንንም በቀጣይ በምርጫ እለት እና በድህረ ምርጫ ወቅት አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።
ለሀገራችን ሰላም እና ደህንነት በጋራ መቆም እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል ።
ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
👍15❤12👏2😢1
ባለስልጣኑ በቀጣይ አምስት ዓመት የደንብ መተላለፎች የቁጥጥር ስራው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመተግበር እንደሚሰራ ገለፀ
ግንቦት 28 2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2022 ዓ ም ራዕዩንና ለማሳካትና ስማርት ሲቲ ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ እውን ሊያደርግ የሚያስችል የአምስት አመት ስትራቴጂክ እቅድ ላይ ውይይት ተደረገ።
በውይይቱ ተቋሙን በቴክኖሎጂ በማላቅ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ በ2022 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማን ለአፍሪካ ከተሞች ተምሳሌት እንድትሆን ባለስልጣኑ ያስቀመጠውን ራእይ እውን የሚያደርግ ነው ሲሉ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ አምስት አመት የደንብ መተላለፎች የቁጥጥርና ሂደቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመተግበር በከተማ የሚስተዋሉ ደንብ መተላለፎችን በመቀነስ ለነዋሪዎቿ እንዲሁ ለእንግዶቿ ምቹና ሰላማዊ የሆነች አዲስ አበባን ለመረጋገጥ መሆኑ በእቅዱ ተመላክቷል።
ባለስልጣኑ በማዕከል የተጀመረው የቴክኖሎጂ አገልግሎቶች በማላቅ እስከ ታችኛው መዋቅር ተደራሽ በማድረግ የተቋሙን ራዕይና ተልእኮ ባለ ድርሻ አካላትና ህብተሰቡ የሚሳተፉበት ስልት መነደፉን በውይይቱ ተመላክቷል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ እውጤት ተኮር ስራዎችን በማከናወን የተገልጋይ ፍላጎትን መሠረት ያደረገ አገልግሎት አሰጣጥ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገልጿል።
መረጃው:- የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ግንቦት 28 2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2022 ዓ ም ራዕዩንና ለማሳካትና ስማርት ሲቲ ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ እውን ሊያደርግ የሚያስችል የአምስት አመት ስትራቴጂክ እቅድ ላይ ውይይት ተደረገ።
በውይይቱ ተቋሙን በቴክኖሎጂ በማላቅ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ በ2022 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማን ለአፍሪካ ከተሞች ተምሳሌት እንድትሆን ባለስልጣኑ ያስቀመጠውን ራእይ እውን የሚያደርግ ነው ሲሉ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ አምስት አመት የደንብ መተላለፎች የቁጥጥርና ሂደቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመተግበር በከተማ የሚስተዋሉ ደንብ መተላለፎችን በመቀነስ ለነዋሪዎቿ እንዲሁ ለእንግዶቿ ምቹና ሰላማዊ የሆነች አዲስ አበባን ለመረጋገጥ መሆኑ በእቅዱ ተመላክቷል።
ባለስልጣኑ በማዕከል የተጀመረው የቴክኖሎጂ አገልግሎቶች በማላቅ እስከ ታችኛው መዋቅር ተደራሽ በማድረግ የተቋሙን ራዕይና ተልእኮ ባለ ድርሻ አካላትና ህብተሰቡ የሚሳተፉበት ስልት መነደፉን በውይይቱ ተመላክቷል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ እውጤት ተኮር ስራዎችን በማከናወን የተገልጋይ ፍላጎትን መሠረት ያደረገ አገልግሎት አሰጣጥ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገልጿል።
መረጃው:- የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
❤9👍7
የከተማችን ስነ-ምህዳር ጤንነት በማስጠበቅ የደንብ መተላለፎች ለመከላከል ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
06/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በደንብ 180/2017 ወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ብክለት መከላከልና በአዋጅ ቁጥር 1383/2017 ስራዎች ዙሪያ በተመለከተ የውይይት መድረክ ተካሄደ ።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር እሸቱ ለማ ከተማችንን ንጹህ ውብ ለነዋሪዎቿ ምቹ ለቱሪስት መስብ የአፍሪካ ተምሳሌት እንድትሆን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ህብረተሰቡን በማሳተፍ በመስራትና የግንዛቤ ስራዎች በስፈት በመከናወኑ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።
የፕላስቲክ ምርቶች /ፌስታሎች / በተፈጥሮ ለረጅም ጊዜ ሳይበሰብሱ የሚቆዩ በመሆናቸው የአከባቢ ስነምህዳር ብሎም የሰዎች እና የእንስሳት የጤና ጠንቅ በመሆናቸው ህብረተሰቡ እነዚህን የጤና ጠንቅ የሆኑ ምርቶችን ባለመጠቀም አጠቃላይ የስነምህዳር ጤንነትን በማስጠበቅ ሂደት የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ ዶ/ር እሸቱ ገልጸዋል ።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ወንዞችን እና የወንዙ ዳርቻዎችን ከብክለት ጽዱ ለማድረግ ሁለቱም ተቋማት በጋራ በመቀናጀት ለመከላከልና የተሰጠውን ተልዕኮ ለመወጣት በርካታ ተግባራትን በጋራ በማከናወን አመርቂ ስራ መሰራቱንና በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ገልጸዋል ።
አክለውም ከቅጣትና ከደንብ ማስከበር ባለፈ፣ ህብረተሰቡ ስለ አካባቢ ጥበቃና ስለ ቆሻሻ ጉዳት በቂ ግንዛቤ አግኝቶ ቆሻሻን የሚፀየፍ ትውልድ እንዲፈጠር በትኩረት መስራት እንደሚገባና ህግንና ደንብን ተላልፈው አካባቢን በሚበክሉ አካላት ላይ ጥብቅ የደንብ ማስከበር ስራ እንደሚሰራና ተጠያቂነት እንደሚሰፍን አስገንዝበዋል።
በመድረኩ በደንብ 180/2017 የወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል በአዋጅ ቁጥር 1383/2017 በጋራ የተሰሩ ጥቅል ስራዎች ሪፖርት እና የፕላስቲክ ከረጢት አምራቾችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የህግ ተከባሪነት የመስክ ሪፖርት ቀርቧ ውይይት ተካሂዷል ።
በአዋጅ 1383/2017 የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ላይ የፕላስቲክ ብክለትን ለመቀነስ አዋጁን ለመተግበር በተደረጉ የቅጣት እርምጃዎች ህግን ባለመክበር 60 አካላት በድምሩ 1.3 ሚሊዮን ብር መቀጣታቸው በሰዱ ተገልጿል ።
ከተማችን ከአካባቢ ብክለትና ከደንብ መተላለፍ የጸዳች ለማድረግ ከላይ አስከ ታች ያለው መዋቅር በቅንጅትና በቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል
ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
06/10/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በደንብ 180/2017 ወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ብክለት መከላከልና በአዋጅ ቁጥር 1383/2017 ስራዎች ዙሪያ በተመለከተ የውይይት መድረክ ተካሄደ ።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር እሸቱ ለማ ከተማችንን ንጹህ ውብ ለነዋሪዎቿ ምቹ ለቱሪስት መስብ የአፍሪካ ተምሳሌት እንድትሆን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ህብረተሰቡን በማሳተፍ በመስራትና የግንዛቤ ስራዎች በስፈት በመከናወኑ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።
የፕላስቲክ ምርቶች /ፌስታሎች / በተፈጥሮ ለረጅም ጊዜ ሳይበሰብሱ የሚቆዩ በመሆናቸው የአከባቢ ስነምህዳር ብሎም የሰዎች እና የእንስሳት የጤና ጠንቅ በመሆናቸው ህብረተሰቡ እነዚህን የጤና ጠንቅ የሆኑ ምርቶችን ባለመጠቀም አጠቃላይ የስነምህዳር ጤንነትን በማስጠበቅ ሂደት የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ ዶ/ር እሸቱ ገልጸዋል ።
የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ ወንዞችን እና የወንዙ ዳርቻዎችን ከብክለት ጽዱ ለማድረግ ሁለቱም ተቋማት በጋራ በመቀናጀት ለመከላከልና የተሰጠውን ተልዕኮ ለመወጣት በርካታ ተግባራትን በጋራ በማከናወን አመርቂ ስራ መሰራቱንና በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ገልጸዋል ።
አክለውም ከቅጣትና ከደንብ ማስከበር ባለፈ፣ ህብረተሰቡ ስለ አካባቢ ጥበቃና ስለ ቆሻሻ ጉዳት በቂ ግንዛቤ አግኝቶ ቆሻሻን የሚፀየፍ ትውልድ እንዲፈጠር በትኩረት መስራት እንደሚገባና ህግንና ደንብን ተላልፈው አካባቢን በሚበክሉ አካላት ላይ ጥብቅ የደንብ ማስከበር ስራ እንደሚሰራና ተጠያቂነት እንደሚሰፍን አስገንዝበዋል።
በመድረኩ በደንብ 180/2017 የወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል በአዋጅ ቁጥር 1383/2017 በጋራ የተሰሩ ጥቅል ስራዎች ሪፖርት እና የፕላስቲክ ከረጢት አምራቾችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የህግ ተከባሪነት የመስክ ሪፖርት ቀርቧ ውይይት ተካሂዷል ።
በአዋጅ 1383/2017 የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ላይ የፕላስቲክ ብክለትን ለመቀነስ አዋጁን ለመተግበር በተደረጉ የቅጣት እርምጃዎች ህግን ባለመክበር 60 አካላት በድምሩ 1.3 ሚሊዮን ብር መቀጣታቸው በሰዱ ተገልጿል ።
ከተማችን ከአካባቢ ብክለትና ከደንብ መተላለፍ የጸዳች ለማድረግ ከላይ አስከ ታች ያለው መዋቅር በቅንጅትና በቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል
ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
❤12👍9👏1