የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.5K subscribers
3.96K photos
13 videos
1 file
93 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ባለስልጣኑ ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከለው ዲሊኦፖል ኢንተራሽናል ሆቴል 600,000(ስድስት መቶ ሺህ) ብር መቅጣቱ አስታወቀ

03/09/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በካይ የፍሳሽ ቆሻሻን ወደ ወንዝና የወንዝ ዳርቻ የለቀቀው ዲሊኦፖል ኢንተራሽናል ሆቴል ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር 600,000/ስድስት መቶ ሺህ/ ብር የቅጣት እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል።

ድርጊቱ በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው ባንቢስ አከባቢ ወደ ወንዝ የሽንትቤት ፍሳሽ በመልቀቅ ብክለቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምርመራ በመረጋገጡ ከዚህ ቀደም እርምጃ የተወሰደ ሲሆን አሁንም በድጋሚ በመልቀቁ የቅጣቱን እጥፍ ተቀቷል።

ከቅጣቱ በተጨማሪ ብክለቱ ለማስቆም ችግሩ እስኪስተካከል የሆቴሉ የችግሩ መንስኤ የሆኑ መጸዳጃ ቤቶቹ እንዲታሸግ መደረጉ ተገልጿል።

ባለስልጣኑ በከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ወጪ በማውጣት ወንዝና የወንዝ ዳርቻዎች እየለሙ መሆኑ በመግለፅ ወንዞቹን በመበከል ለታለመለት አላማ እንዳይውል በሚያደርጉ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የሚወስደው አስተዳደራዊ እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል አሳውቋል።

ባለስልጣኑ ከተማው ነዋሪዎችና ተቋማት በደንቡ ዙሪያ ሰፊ ግንዛቤ መፍጠሩ አስታውሶ ነዋሪዎችና ተቋማት ከመሰል ተግባራቸው እንዲታቆጠቡ አሳስቧል።

ህብረተሰቡ ለማንኛውም አይነት የደንብ መተላለፍ በነፃ ስልክ 9995 መረጃና ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍9👏4
ባለስልጣኑ በኮሪደር መሠረተ ልማት ላይ የደንብ መተላለፍ ለሚፈጽሙ ግለሰቦችና ድርጅቶች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰበ

05/09/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በኮሪደር መሰረተ ልማት ላይ ህገወጥ ማስታወቂያ በመስቀል ሳይክል በማቆም ሳር ላይ ለተኙ እና የኮሪደር ልማት ያበላሹ ድርጅቶች 75,000/ሰባ አምስት ሺህ/ ብር የቅጣት እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል።

ድርጊቱ በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ማይ ኢንተርቴይመንት የተባለ ደርጅት በኮሪደር መንገድ ስታንዳርዱን ያልጠበቀ ማስታወቂያ በሳይክል በማቆምና ሳር ላይ በመተኛት ብር 25000 የተቀጣ ሲሆን እንዲሁም ሳምቤክ ሪል ስቴት የኮሪደር መንገድ በማበላሸት ብር 50000 በመቅጣት በድምሩ 75,000/ሰባ አምስት ሺህ ብር/ አስተዳደራዊ እርምጃ በመውሰድ ከጥፈታቸው እንዲታረሙ ተደርጓል።

ባለስልጣኑ በኮሪደር መሠረተ ልማት ላይ የደንብ መተላለፍ ለሚፈጽሙ ግለሰቦችና ድርጅቶች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እያሳሰበ በከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ወጪ የተሰራውን የኮሪደር ልማት በሚያበላሹ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የሚወስደው አስተዳደራዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

ህብረተሰቡ ለማንኛውም አይነት የደንብ መተላለፍ በነፃ ስልክ 9995 መረጃና ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍42
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በህ-ወጥ መንገድ ለገበያ ሊቀርብ የተዘጋጀ ስጋ መያዙ ተገለፀ

06/09/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**


በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ​በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በወረዳ 11 ደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት በተካሄደው ድንገተኛ ኦፕሬሽን በድብቅ የታረደና ለገበያ ሊቀርብ የነበረ ከፍተኛ መጠን ያለው የእንስሳት ስጋ በቁጥጥር ስር መዋሉን ተገለፀ።

​ኦፕሬሽኑ የተካሄደው በወረዳ 11 ልዩ ቦታው ቀጠና 01 "ሰው ለሰው እድር ቤት" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲሆን፣ ከጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በተደረገ ጥብቅ ፍተሻ ጤንነታቸው ያልተረጋገጡ 13 የታረዱ በጎች፣ 14 ፍየሎች እንዲሁም ፅዳቱ ያልተጠበ 312 ኪሎ ግራም ስጋ ተይዟል።

​የወረዳው የደንብ ማስከበር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተክሉ ምንዳ እንደገለጹት የተያዘው ስጋ እንዲወገድ ለአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የተረከበ ሲሆን ድርጊቱን የፈጸሙ ግለሰቦችም በህግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።

ኃላፊው አክለውም ህብረተሰቡ መሰል ህገ-ወጥ እርዶችንም ሆነ ማንኛውንም የደንብ መተላለፍ ሲመለከት በነፃ ስልክ መስመር 9995 ጥቆማ በመስጠት ከተቋሙ ጎን እንዲቆም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
👍6
ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በከተማችን በሰላም እንዲጠናቀቅ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑ ተገለፀ

12/09/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቅድመ ምርጫ በምርጫ እለት እና በድህረ ምርጫ ወቅት የተቀናጀና የተጠናከረ የጥበቃና የሰላም ግንባታ ተግባራትን በማከናወን ሰላማዊ ምርጫ እንዲከናወን የውይይት መድረክ አካሄደ ።

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ እጅግ ሰላማዊ ፣ ነጻ ፣ ፍትሀዊና ተዓማኒ በማድረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታውን ወደ ላቀ ደረጃ ማሻገር እንደሚገባ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል ።

አክለውም የደንብ ማስከበር አመራርና ኦፊሰር ምርጫው በከተማችን በሰላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ የሚገኙ ሲሆን ይሄንንም በቀጣይ በምርጫ እለት እና በድህረ ምርጫ ወቅት አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።

ለሀገራችን ሰላም እና ደህንነት በጋራ መቆም እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል ።

ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
👍1512👏2😢1