በበጀት አመቱ ባለፉት 9 ወራት የደንብ መተላለፎች በ82% እና የወንጀል ምጣኔ በ47% መቀነስ መቻሉ ተገለፀ
22/08/2018ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እና የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የ9 ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።
የመድረኩን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ከተማችን የአፍሪካ ትልቋ የቱሪዝም የስህበት ከተማ ሆናለች፤ የከተማዋ ሰላምና ደህንነት አስተማማኝና በመሆኑ በርካታ ሀገር አቀፍ ብቻ ሳይሆን አለም አቀፍ ሁነቶች እየተካሄዱባት ይገኛል፤ ይህንንም ማድረግ የቻልነው ህዝቡን በቀጥታ የሰላም ባለቤት ማድረግ በመቻሉ መሆኑ ገልፀዋል።
በከተማው ከ200ሺ በላይ ለሚሆኑ የሰላም ሰራዊት አባላት በ9 ወራት ውስጥ በድግግሞሽ የአቅም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸውን በከተማችን የደንብ መተላለፎች እንዲቀንሱ እና ለከተማዋ የሚመጥን ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ለማፍራት ወታደራዊ እና የንድፈ ሀሳብ ስልጠናዎችን በመስጠት የሰው ኃይሉ ላይ ከፍተኛ ለውጥ መታየቱን ተናግረዋል።
በዕለቱ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንዳሉት በባለፍት 9ወራት የአደባባይ በዓላት በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ እና የተለያዮ የደንብ መተላለፎች እንዳይከሰቱ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው።
ይህንንም ለማሳካት ቀደም ብለን ስራዎችን በእቅድ አዘጋጅተን በየሩብ ዓመቱ መገምገም መቻሉን ተናግረው። በዛሬው ዕለትም ምን ሰራን የሚለውን ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ለቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችን ተቀብለን የምንወጣበት መሆኑን ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2018 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት በከተማዋ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ እና የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ ረገድ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወኑ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች 82% መቀነሱን ሪፖርቱን ያቀረቡት የባስልጣኑ የእቅድ እና በጀት ዳይሬክተር ኮነሬል አድማሱ ተክሌ ተናግረዋል።
በተመሳሳይ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ የእቅድና በጀት ዳይሬክተር አቶ ማስረሻ ሀብቴ ሪፖርቱን ሲያቀርቡ እንዳሉት በ9ወራት የወንጀል ምጣኔ ከቀደሙት ጊዜያት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ 47.15 በመቶ መቀነሱን ገልፀዋል።
በመጨረሻም ለመድረክ የቀረቡትን ሀሳብ እና አስተያየቶች ላይ ምላሽ በሁለቱ ተቋማት አመራሮች ምላሽ ተሰቶበት እና የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀምጦ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው:-የደንብ ማስከበር ኮሙኑኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
22/08/2018ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እና የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የ9 ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።
የመድረኩን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ከተማችን የአፍሪካ ትልቋ የቱሪዝም የስህበት ከተማ ሆናለች፤ የከተማዋ ሰላምና ደህንነት አስተማማኝና በመሆኑ በርካታ ሀገር አቀፍ ብቻ ሳይሆን አለም አቀፍ ሁነቶች እየተካሄዱባት ይገኛል፤ ይህንንም ማድረግ የቻልነው ህዝቡን በቀጥታ የሰላም ባለቤት ማድረግ በመቻሉ መሆኑ ገልፀዋል።
በከተማው ከ200ሺ በላይ ለሚሆኑ የሰላም ሰራዊት አባላት በ9 ወራት ውስጥ በድግግሞሽ የአቅም ግንባታ ስራዎች መሰራታቸውን በከተማችን የደንብ መተላለፎች እንዲቀንሱ እና ለከተማዋ የሚመጥን ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ለማፍራት ወታደራዊ እና የንድፈ ሀሳብ ስልጠናዎችን በመስጠት የሰው ኃይሉ ላይ ከፍተኛ ለውጥ መታየቱን ተናግረዋል።
በዕለቱ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንዳሉት በባለፍት 9ወራት የአደባባይ በዓላት በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ እና የተለያዮ የደንብ መተላለፎች እንዳይከሰቱ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው።
ይህንንም ለማሳካት ቀደም ብለን ስራዎችን በእቅድ አዘጋጅተን በየሩብ ዓመቱ መገምገም መቻሉን ተናግረው። በዛሬው ዕለትም ምን ሰራን የሚለውን ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ለቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችን ተቀብለን የምንወጣበት መሆኑን ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የ2018 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት በከተማዋ የደንብ መተላለፎችን በመቀነስ እና የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ ረገድ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወኑ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች 82% መቀነሱን ሪፖርቱን ያቀረቡት የባስልጣኑ የእቅድ እና በጀት ዳይሬክተር ኮነሬል አድማሱ ተክሌ ተናግረዋል።
በተመሳሳይ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ የእቅድና በጀት ዳይሬክተር አቶ ማስረሻ ሀብቴ ሪፖርቱን ሲያቀርቡ እንዳሉት በ9ወራት የወንጀል ምጣኔ ከቀደሙት ጊዜያት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ 47.15 በመቶ መቀነሱን ገልፀዋል።
በመጨረሻም ለመድረክ የቀረቡትን ሀሳብ እና አስተያየቶች ላይ ምላሽ በሁለቱ ተቋማት አመራሮች ምላሽ ተሰቶበት እና የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀምጦ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘገባው:-የደንብ ማስከበር ኮሙኑኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍5👏3❤1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ያከናወናቸውን የሪፎርም ስራዎች ጉብኝት ላይ ከተናገሩት:-
👍19👏4
በማዕከል የተጀመረውን የሪፎርም ጉዞ ለማስቀጠል በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን የቦሌ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ገለጸ
24/08/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የቦሌ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በከተማ እናት መስሪያቤቱ የተጀመረው የሪፎርም፣ የተቋም ግንባታ እና ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት የመስጠት ተግባር አጠናክሮ ለማስቀጠል የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች አስቀመጠ ::
ጽ/ቤቱ የትኩረት አቅጣጫዎች ያስቀመጠው በክፍለ ከተማው ተቋም በመምራት የላቀ አስተዎጽኦ ላበረከቱ የቀድሞ አመራሮች እውቅና ምስጋና በሰጠበት መድረክ ሲሆን ይህም በቀጣይ ተግተው ለሚሰሩ አመራሮች እና ኦፊሰሮች የበለጠ የሚያበረታታ መሆኑ የቦሌ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቸሩ ጌታቸው ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጁ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተቋም ግንባታ ስራ በማከናወን ከህብረተሰብ የሚነሳውን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ለዜጎች ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ተግባሩ ወደ ዲጂታል መቀየሩ ገልፀዋል።
ደንብ ማስከበር የቀድሞ ስሙን በመቀየር አሁን ላይ ራሱን በማዘመን የደንብ መተላለፎችን በመቆጣጠር የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤት በመፈጸምና በኃላፊነት በመወጣት እና የአደባባይ ፕሮግራሞች እና በአደባባይ የሚከበሩ ኃይማኖታዊ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የቦሌ ክ/ከተማ ምክትል ስራ አስፈጸሚ ወ/ሮ አንቺነሽ ተስፋዬ ተናግረዋል።
ምክትል ስራ አስፈጸሚዋ የቦሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በማዕከል ተቋሙ የተጀመረው የሪፎርምና የተቋም ግንባታስራ ለማስቀጠል ክፍለ ከተማው በሙሉ አቅሙ ለማገዝና ለማስተግበር ቃል ገብተዋል።
በመጨረሻም በክፍለ ከተማው በአመራርነት ያገለገሉ የቀድም የክፍለ ከተማ ሀላፊው ኮ/ር አሰፋው የሺዳኜ እና ሌሎች የወረዳ አመራሮቹ በክብር ሸኝቷል።
መረጃው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
24/08/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የቦሌ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በከተማ እናት መስሪያቤቱ የተጀመረው የሪፎርም፣ የተቋም ግንባታ እና ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት የመስጠት ተግባር አጠናክሮ ለማስቀጠል የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች አስቀመጠ ::
ጽ/ቤቱ የትኩረት አቅጣጫዎች ያስቀመጠው በክፍለ ከተማው ተቋም በመምራት የላቀ አስተዎጽኦ ላበረከቱ የቀድሞ አመራሮች እውቅና ምስጋና በሰጠበት መድረክ ሲሆን ይህም በቀጣይ ተግተው ለሚሰሩ አመራሮች እና ኦፊሰሮች የበለጠ የሚያበረታታ መሆኑ የቦሌ ክ/ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቸሩ ጌታቸው ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጁ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተቋም ግንባታ ስራ በማከናወን ከህብረተሰብ የሚነሳውን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ ለዜጎች ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ተግባሩ ወደ ዲጂታል መቀየሩ ገልፀዋል።
ደንብ ማስከበር የቀድሞ ስሙን በመቀየር አሁን ላይ ራሱን በማዘመን የደንብ መተላለፎችን በመቆጣጠር የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤት በመፈጸምና በኃላፊነት በመወጣት እና የአደባባይ ፕሮግራሞች እና በአደባባይ የሚከበሩ ኃይማኖታዊ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የቦሌ ክ/ከተማ ምክትል ስራ አስፈጸሚ ወ/ሮ አንቺነሽ ተስፋዬ ተናግረዋል።
ምክትል ስራ አስፈጸሚዋ የቦሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በማዕከል ተቋሙ የተጀመረው የሪፎርምና የተቋም ግንባታስራ ለማስቀጠል ክፍለ ከተማው በሙሉ አቅሙ ለማገዝና ለማስተግበር ቃል ገብተዋል።
በመጨረሻም በክፍለ ከተማው በአመራርነት ያገለገሉ የቀድም የክፍለ ከተማ ሀላፊው ኮ/ር አሰፋው የሺዳኜ እና ሌሎች የወረዳ አመራሮቹ በክብር ሸኝቷል።
መረጃው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው
❤4👏1